text
stringlengths
2
383k
ያኮረፈ ሁሉ ይቅር ይበሉኝ ጃንሆይ እያለ እሳቸውም ምሬሃለሁ እያሉ ...ባሕር ዳር የካቲት 212011 ዓ.ምአብመድ መላው አፍሪካውያን በባርነት ረግረግ በሚዳክሩበት በዚያ ወቅት የአፍሪካውያን አባቶች በልጆቻቸው ፊት ክብራቸው እንዳደፈ ሸማ በነተበበት በዚያ ዘመን ሀገር በጭቆና ማቅ የጣር ድምፆች በረክተውባት ነበር ጀርባዋ ሲናጥ ወኔዋ ሲኮሰምን ቅስሟ ሲሰበር የተጎሰመው ነጋሪት የተነፋው ጡሩንባ የተነገረው ዓዋጅ በዓለም ታሪክ የፋሺስቶች ድንበር የለሽ የትዕቢት ዘረኝነት ቅኝ ግዛት የማያንበረክካት የጥቁር ሕዝቦች ቀንዲል ሀገር እንድትፈጠር ምክንያት ሁኗል በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት የተፈጠረችው ኅብረ ብሔራዊቷ ኢትዮጵያ እና የዓድዋ ድል ምስጢር ምንድን ነው? በየአከባቢው ዓፄ ምኒልክ ላይ አኩርፈው ፊናቸውን ይዘው በዱር በገደሉ የነበሩ መኳንንት የክተት ዓዋጅ በመላው ሀገሬቱ ከተነገረ ወዲህ ሀገሬ ካንቺ በፊት እኔ ብለው በአንድነት ያለምንም ልዩነት ዘምተው ድል ያደረጉ አባቶች መነሻ ምንድን ነው? ለእነዚህ ሁሉ መነሻው የሠመረው የክተት ዓዋጅ እና በሀገር ፍቅር የነደዱ ሕይወታቸውን ያለስስት የገበሩ ጀግኖችን ያነሳሳው የክተት አዋጅ ነው ብለውናል የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህሩ ዶክተር አየነው ማሞታሪካዊው የክተት አዋጅ-እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ ከእንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ስለእኔ ሞት አላዝንም ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም አሁንም አገር የሚያጠፋ ሃይማኖትን የሚለውጥ በፊት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባሕር አልፎ መጥቷል እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድከም ዓይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም የአገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በጸሎትህ እርዳኝ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልምርህም ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም... አሉ አፄ ምኒልክና የኢትዮጵያ አንድነት በተክለ ጻዲቅ መኩሪያ ገጽ 226የክተት አዋጁ በዘመኑ በኢትዮጵያውያን ያሳደረው ስሜት እና የፈጠረው አንድነት ከባድ መሣርያዎችን የታጠቀው የጣሊያንን ጦር ባሕላዊው የኢትዮጵያ ጦር በስድስት ስዓት ውስጥ ድል እንዲያደርግ አስችሏል አንድነት ለኢትዮጵያውያን በጋራ የመኖር ብቻ ሳይሆን የጋራ ችግርን በተሳለጠ መንገድ ለማስወገድ ዓይነተኛ ባሕሪ ነበረየታሪክ ምሁሩ ዶክተር አየነው ማሞ የክተት አዋጁ ሁሌም ትኩስ ስሜትን የሚፈጥር እና ሳትሰስት ሕይወትን እንድትሰጥ የማድረግ ኃይል አለው ዓፄ ምኒልክ በግድ ተነሱ አላሉም ጠላት ወሮናል ሁልህም ተነስ አላሉም ከዚያ ይልቅ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በጸሎትህ እርዳኝ ብለው በፍቅር ነው የተማፀኑት በማለት የዓዋጁን ኮርኳሪነት አብራርተዋልዶክተር አየነው ይህ የክተት ዓዋጅ አይደለም ሀገር አማን ብሎ በየቤቱ የተቀመጠ ሕዝብ በዱር በገደሉ አሻፈረኝ ብሎ ያኮረፈ ሁሉ ይቅር ይበሉኝ ጃንሆይ እያለ እሳቸውም ምሬሃለሁ እያሉ ሀገራዊ አንድነት ታጥቀው ጣልያንን በስድስት ስዓት ውስጥ እንዲያንበረክኩ መሠረት የነበረ ነው ብለዋልየታሪክ ምሁሩ እንዳብራሩትም በርካታ የአፍሪካ ሀገሮች ከቅኝ ግዛት ቀንበር ለመውጣት በርካታ ሙከራዎችን አድርገው አይቀጡ ቅጣት ተከናንበዋል ኢትዮጵያን ለቅኝ ግዛት እንዳትንበረከክ ያደረገው ሀገራዊ አንድነት ያለው ሕዝብ በወቅቱ በመፈጠሩ ነው የሁሉም ዜጎቹ ትኩረት የጋራ ጠላት ላይ ብቻ ስለነበር በበርካታ ሐሳቦች ተደግፈው እጅግ ባሕላዊ በሆነ የጦር ስልት ታግዘው ለዓለም ሕዝብ አዲስ ምዕራፍን አስተዋውቀዋል በዓድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ለመላው ጥቁር ሕዝብ አንገቱን ቀና አድርጎ እንዲጓዝ ምክንያት ሆነዋል ዓድዋ ለነፃነት ትግሎች ዓርማ ሆኗል ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጠላትን ድል ማድረግ ያልቻሉት በውስጣቸው አንድነት ባለመኖሩ እና ጎታች ሐሳቦች በመኖራቸው መሆኑንም ዶክተር አየነው ገልጸዋል ይህም ለዓለም ታሪክ አንድነት የሚፈጥረውን ኃይል ማስተማርያ ነው አንድነቱ የፈጠረው ድልም የሰው ልጆች እኩልነት የተጠነሰሰበት እና ጥቁሮች እችላለሁ የሚል ስሜትን ያስታጠቀ ነበር የግል ጥቅምን ለማስጠበቅ ሳይሆን ለሀገራዊ አንድነት ሲሉ በነፃ ከተለገሱ ሕይወቶች የተፈጠረው አዲስ የዓለም ክስተት ለሦስተኛው ዓለም ልጆች ታሪክ ዓይነተኛ ሚና ተጫውቷል ዛሬም ትውልዱ ሀገራዊ አንድነት መኖር የሚያስገኘውን የጋራ ጥቅም በመረዳት ከግል እና ከቡድን ጥቅም ይልቅ ለሀገር ግንባታ በማሰብ የጋራ ታሪክ ኑሮን በዓለም ፊት በአብነት እንድንጠቀስ ሊሠራ የሚገባ ወቅት ነው ብለዋል ዶክተር አየነው
123ኛ የአደዋ ድል በአል በአጼ ምኒልክ የትውልድ ቦታ በአንጎለላ ኪዳነ ምህረት እየተከበረ ነውባሕር ዳር የካቲት 182011 ዓ.ምአብመድ 123ኛዉ የአደዋ ድል በአል በሰሜን ሸዋ ዞን በአጼ ሚኒሊክ የትውልድ ቦታ አንጎለላ ኪዳነ ምህረት ላይ እየተከበረ ነውበበዓሉ የአካባቢው ፈረሰኞች እና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋልአዘጋጆቹ የደብረብርሀን ዩንቨርሲቲ እና የሰሜን ሽዋ ዞን ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ ናቸውየድል በዓሉ እስከ የካቲት 232011 ዓ.ም ድረስ በፓናል ውይይት በታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝትና በአደባባይ ትርዒቶች በደብረብርሀን ከተማ ላይ ይከበራል
የዓድዋ ድል በዓል በጎንደር ዩኒቨርሲቲ እየተከበረ ነውባሕር ዳር የካቲት 222011 ዓ.ምአብመድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ኮሌጅ 123ኛውን የዓድዋ ድል በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ነውበበዓሉ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁሩ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ፋንታሁን አየለ የዓድዋ ጦርነትን የተመለከተ ጽሑፍ አቅርበዋል ከክተት ዓዋጁ እስከ ጦርነቱ ፍጻሜ የኢትዮጵያውያን አርበኞች ወኔና አንድነት ምን ይመስል እንደነበር በጽሑፋቸው ተንትነዋልበዘመር መከፋፈል ያመጣውን አስከፊ ሁኔታ ጠቅሰው ትውልዱ ከዓድዋ ትምህርት ወስዶ ለሀገሪቱ ዕድገት በአንድነት እንዲረባረብም ተባባሪ ፕሮፌሰሩ አሳስበዋልደራሲና ከያኒ ጌትነት እንየው ደግሞ በዓድዋ ጀግኖች ላይ ያተኮረ ግጥም አቅርበዋል ደራሲና ከያኒ ጌትነት እንየው የዓድዋ ድል ትልቁ ሚስጥራችን አንድነታችን ነው ሁሉም አርበኞች ከአራቱም አቅጣጫ ተሰባስበው በዘመናዊ ትጥቅ የተደራጀውን ጠላት አሸንፈዋል ይህም የኢትዮጵያዊነትንና አንድነት ጉልበትን ማሳያ ምሥክር ነው ብለዋልበጎንደር ዩኒቨርሲቲ እየተከበረ በሚገኘው የዓድዋ ድል 123ኛ ዓመት በዓል ምሁራን አርቲስቶችና ሌሎችም የኅብረተሰብ ክፍሎች እየታደሙ ነው
121ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በዳላስ ቴክሳስ በደማቅ ሁኔታ ተከበረየመላው ጥቁር ኩራት የሆነውን የአድዋ ድል 121ኛውን መታሰቢያ በዓል በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በዳላስ ቴክሳስ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓሉን ያዘጋጀው በዳላስና ፎርትወርዝ የኢትዮጵያውያን ጉዳዮች የውይይት መድረክ ሲሆን ዘንድሮ ሲያዘጋጅ ለሦስተኛ ጊዜ ነውስብሰባው በዳላስ ቴክሳስ የሰዓት አቆጣጠር 4 ሰዓት የተጀመረ ሲሆን ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ኢትዮጵያዊነት ወኔ የተሞላበትና ድል ድል የሚሸት ነበር የዝግጅቱ መድረክ መሪ አቶ መንግስቱ ሙሴ ስብሰባውን በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ ኮልፌ ቀራንዮ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው እልቂት ህይወታቸው ያጡትንና የተጎዱትን እንዲሁም አጥንታቸው ከስክሰውና ደማቸውን አፍሰው ለአድዋ ድል ላበቁን ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችንን በማሰብ አስጀምረውታል በመቀጠልም በዓሉ አዘጋጅ የሆነውን በዳላስና ፎርትወርዝ የኢትዮጵያውያን ጉዳዮች የውይይት መድረክ ሰብሰቢ አቶ ኃይሌ በመጋበዝ የእንኳን አደረሳችሁና እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው የማህበሩን ተግባራት አብራርተዋልበዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር የቦርድ ተወካይ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ቦርዱን ወክለው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ይህን ትልቅ በዓል ያዘጋጀውን የውይይት መድረክ አመስግነው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትኩረት እየተሰጠው መምጣቱ እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል በመቀጠልም ወሮ ራሔልና ልጆቿናሆምና መቅደስ የአድዋ ድል የተሰኘ ግጥም አቅርበዋልበዝግጅቱ መካከል ላይ ተጨማሪ ንግግሮችና ድል ድል የሚሸቱ አገራዊ ዘፈኖች የቀረቡ ሲሆን የዝግጅቱ እንግዳ ሆነው የተጋበዙት ዶር ማስፍን ገናናውና ፕር ኃይሌ ላሬቦ የአድዋ ድል የተመለከተ ሰፊ የሆነ ትምህርታዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል ሁለቱም የዝግጅቱ እንግዶች ያደረጉትን ንግግር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ሰጪ በመሆናቸው በቅርቡ ለሁሉም እንዲደርስ እናደርጋለንሌላው የፕር ኃይሌ ላሬቦ ባለቤት ወሮ እስከዳር ባለቤታቸው ለአገራቸዉ ያላቸውን ፍቅር የሚያደርጉት ትግል አድንቀው ለቤታቸውም ፍቅር የሆኑ ጥሩ አባወራ መሆናቸውን ገልፀዋል በቅርቡ በኢሳትና ዶቼቤላ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃለመጠይቅ ያልተደሰቱ ግለሰቦችና ቡድኖች ግን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በጎደለው መልኩ በቤተሰቦቻቸው ላይ ከፍተኛ ዛቻ ከማቅረባቸውም በላይ ባለቤታቸው ከስራ እንዲባረሩ ለማድረግ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ እንደነበር ያስረዱ ሲሆን ፕር ኃይሌ ላሬቦ ላይ የሚደርሰው በደም የኛም በደል ነው በማለት ከጎናቸው ለቆሙት ሁሉም ምስጋናቸውን አቅርበዋልበመጨረሻም ዝግጅቱን በተመለከተ የተዘጋጀውን ኬክ የእለቱ እንግዶች በአንድ ላይ ቆርሰው የፕሮግራሙ ፍፃሜ ሆኗል
ያልተዘመረላቸው ዘማሪዎችባሕር ዳር የካቲት 202011 ዓ.ምአብመድ ኢትዮጵያዊነትን በሙዚቃ መገንባት እንደሚቻል አዝማሪዎች በዓድዋ ጦርነት ወቅት በተግባር አሳይተዋል ኢትዮጵያን ከገጥሟት ከባድ የውጭ ኃይል ፈተናዎች መካከል የ1880ዎቹ መጨረሻ የጣልያን ወረራ አንዱ ነበር ይህንን ወረራ ግን ኢትዮጵያውያን በአንድነት በዓድዋ ግንባር በድል አጠናቅቀውታል ለድሉ ተዋጊዎችን ሞርዶ በመሳል በኩል ደግሞ ኪነ-ጥበብ በአዝማሪዎች በኩል ጉልህ ሚና ተጫውታለችበጣልያን በኩል የዓድዋን ጦርነት ሊዘግብ የመጣው ጆርጅ በርክሌይ የአዝማሪዎቹን ታሪክ ማጉደፍ ስላልፈለገ የታዘዘውን ትቶ ያስገረመውን የኢትዮጵያ ታሪክ ዘግቦ ተመልሷል:: ጦርነቱ እጅግ አስፈሪ ከመሆኑ የተነሳ ወታደሮች ወደኋላ መሸሽ ቢፈልጉ እንኳን አዝማሪዎች ምን ሊሏቸው እንደሚችሉ እያሰቡ በወኔ ወደ ጦርነቱ ይገቡ እንደነበረ ከትቧል::እቴጌ ጣይቱ በደህናው ጊዜ አዝማሪ ወዳድ ነበሩ በጦርነቱ ጊዜ ደግሞ ወታደር ብቻውን ሄዶ በድል እንደማይወጣ ተረድተው ለሠራዊቱ የወኔ ስንቅ የሚያቀብሉ አዝማሪዎችን አዘጋጅተዋል:: የሙዚቃ ሀያሲው ሰርፀ ፍሬሐብሃት በጥናታቸው እንዳረጋገጡት በእንደነ አዝማሪ ፃዲቄንና አዝማሪ ሐሰን አማኑን የመሳሰሉ አዝማሪዎች መሪነት 150 የሚሆኑ አዝማሪዎች በዓድዋ ጦርነት ተሰልፈው ወታደሩን ለድል አብቅተዋል::በዚህ ጊዜ የሀገር ጦረኞችን የሚያበረታታ እና የጠላት ጦርን የሚያጥላላ ግጥም በቀረርቶ ሽለላ እና ፉከራቸው ያቀርቡ ነበር ከተገጠሙት ስንኞች መካከልኧረ ጉዱ በዛ ኧረ ጉዱ በዛ በጀልባ ተሻግሮ አበሻን ሊገዛ ተብሏል ለአዝማቾችም ማንቂያ ተገጥሟል ክፉ አረም በቀለ በምጥዋ ቆላ አሁን ሳይበረክት አርመው አሉላ እነዚያ ጣሊያኖች ሙግት አይገባቸው አሉላ አነጣጥረህ ቶሎ አወራርዳቸው ዳኛው ወዴት ሄዷል እስኪ ወጥተህ እይአክሱም መንገሻዬ እስኪያዝ ነወይ ዓድዋ ላይ ጣሊያኖች የዘፈኑለትምኒልክ ጎራዴህ ወረደ ባንገት የሚሉት እና ሌሎችም በዓድዋ ጦርነት ወቅት በአዝማሪዎች የተገጠሙ የአዝማሪዎች የጀግና ሞረዶች ናቸውለፊት አውራሪ ገበየሁም በዓድዋ እንዲህ ተገጥሞላቸዋል-ዓድዋ ሥላሴን ጥሊያን አረከሰውገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሰው ተብሎ እነዚህ ግጥች በዜማ እየተገሩ ባሲንቆ እየታጀቡ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችን ወደፊት እንደ ቀስት ይወረውሩ ነበር የሚገጠምቸውን እየሰሙ ወደኋላ ማለት አልፈለጉም ይልቁንም ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደተጣለባቸው በመረዳት እሳት ጎርሰው እስከ ፈረሳቸው ጣልያን ጦር ውስጥ ገብተዋል ለድልም በቅተዋልጀግናው አባተ ቧያለው የጣልያንን መድፍ በመድፍ መልሰው ድራሹን እንዳጠፉት በዓይኑ የተመለከተ የዓድዋ ዘማች አዝማሪም-አባተ ቧያለው ምኑ ክፉ ነውይኼን መድፍ ከዚያ መድፍ አቆራረጠው ብሎ ገጥሞላቸዋል:: ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ የሚለው ስንኝም የተከተበው በኢትዮጵያዊ አዝማሪዎች የዓድዋ ዘመቻ ነውየዓድዋ ጦርነት የተካሄደበት ዕለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያናት የበዓላት ትውፊት መሠረት የቅዱስ ጊዮርጊስ መታሰቢያ ቀን ነበር ይህንንም በዝማሬየዓድዋ አርበኛ ቅዱስ ጊዮርጊስከምኒልክ ጋር አብሮ ሲቀድስምኒልክ በጦሩ ጎርጊስ በፈረሱጣልያንን ድል አደረጉ ደም እያፈሰሱ እየተባለ ተዘምሯል ግጥሙ እስካሁንም በየዓመቱ ይዘመራል የሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረ ስብከትም በዕለቱ የሰማዕቱ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል የአደባባይ በዓል እንዲሆን ወስነዋልየጣልያን መንግሥትም አዝማሪዎች በዚህ መልኩ ጀግና እየፈጠሩ መሆናቸውን ስለተረዳ 40 አዝማሪዎችን ሰብስቦ እንዲገደሉ አድርጓል:: ሞሶሎኒ አዝማሪዎቹን ለይታችሁ ግደሏቸው ብሎ ያዘዘበትን የደብዳቤ ቅጂ ሲልቪያ ፓንክረስት ኢትዮጵያ ኤ ካልቸራል ሂስትሪ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ አስቀምጠውታል::በሀገራችን ለጀግና የሚሰጠው ክብር ከፍተኛ ነው:: የውጭ ኃይልን በጀግንነት ለመመከት ፉከራ ሽለላ ቀረርቶ የመሳሰሉት የኢትዮጵያ ባሕላዊ ሙዚቃዎች የጀግና መሞረጃ ሆነው አገልግለዋል:: ነገር ግን ከዘመቻው መልስ አዝማሪዎቹ የተደረገላቸው ነገር ስለመኖሩ የሚያስረዳ የታሪክ አሻራ የለም::በዓድዋው ጦርነት ብቻም ሳይሆን በ1928ዓ.ም ጣልያን ዳግም ለመውረር ስትመጣ እነባላምባራስ ገሰሰ ፍቅረማርያም አየለ ሜሪ አርምዴ እና ሌሎች አዝማሪዎችም በማይጨው ጦርነት ዘምተዋል ሚናቸው ግን ጎልቶ በታሪክ አልተጻፈም::
አድዋእጅጋየሁ ሽባባው ጂጂየሰው ልጅ ክቡርሰው መሆን ክቡርሰው ሞቷል ሰው ሊያድን ሰውን ሲያከብርበደግነት በፍቅር በክብር ተጠርቶበክብር ይሄዳል ሰው ሊኖር ሰው ሞቶየተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነጻነትሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንትስንቱ ወገን ወደቀ በነጻነት ምድርትናገር አድዋ ትናገር ትመስክርትናገር አድዋ ትናገር ሀገሬእንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬበኩራት በክብር በደስታ በፍቅርበድል እኖራለሁ ይኸው በቀን በቀን በቀን በቀንደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀንአድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትላንትመቼ ተነሱና የወዳደቁትምስጋና ለነሱ ለአድዋ ጀግኖችለዛሬ ነጻነት ላበቁን ወገኖችየጥቁር ድል አምባ አድዋ አፍሪካ እምዬ ኢትዮጲያተናገሪ ተናገሪ የድል ታሪክሽን አውሪ
አድዋ ዳግም የተወለድንበት ቀን ነው ነጻነትን ለሚያውቁ ሰዎች ሁሉ ነጻነትም ነው የአድዋ ድልን ያከበሩ የጎንደር ከተማ ወጣቶች123ኛው የአድዋ ድል በዓል በጎንደር ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯልመርሀ ግብሩን የጎንደር ከተማ አማራ ወጣቶች ማህበር የከተማው የባህል ማዕከል ሸዋ ኢንተርቴይመንት እና አቦል መልቲ ሚዲያ አዘጋጅተውታልህጻናት እና ወጣቶች በበዓሉ አከባበር ላሳዩት ተሳትፎ እና መልካም ተግባር አባት አርበኞች ምስጋና አቅርበዋልወጣቶች ከአያት ቅድመ አያቶቻቸው የወረሱትን ንጹህ ሰንደቅ ዓላማ ጠብቀው አዲስ ታሪክ ሰሪ መሆን እንደሚገባቸውም መክረዋልበጎንደር የአማራ ወጣቶች ማህበር ማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ የሚሰራዉ በሪሁን አሰፋ አድዋ ዳግም የተወለድንበት ነው ነጻነት ለሚያውቁ ሰዎች ሁሉ ደግሞ ነጻነት ነው ብሏልማንኛውም ኢትዮጵያዊ ከዘረኝነት አስተሳሰብ ነፃ ሆኖ በዓሉን እንዲያከብርም አስተያዬቱን አቅርቧልአስተያዬታቸውን ለአብመድ የሰጡ የበዓሉ ተሳታፊዎች በአጼ ቴዎድሮስ የተጀመረው ኢትዮጵያን የማዘመንና አንዲት ጠንካራ ሀገር የማድረግ ራዕይ በእምዬ ምኒልክ እውን መሆኑን ተናግረዋልበጎሳ ተከፋፍሎ አንድነትን ከመሸርሸር ይልቅ በተባበረ ክንድ ታሪካዊ ጠላታችን የሆነዉን ድህነት ልንጋፈጥ ይገባል ነው ያሉትዘጋቢ ደጀኔ በቀለ- ከጎንደር
ከአድዋ ጦርነት ቡኃላ እራሱን ያጠፋው ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬአፄ ሚኒሊክ የጣሊያንን ጦር ለመጋፍጥ ሲወስኑ የጣሊያንን ጦር እየመሩ ከመጡት ጀነራሎች ዋነኛው ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ ነበር ጄኔራል ባራቴሬ የአፄ ሚኒሊክን ከዚህ ቀደም ይከተሉት የነበርን የጦር ስትራቴጂ አጥንቶ ስለነበር የአድዋን ጦርነትም በድል እንደሚወጣው እርግጠኛ ነበር አፄ ሚኒሊክ ቀደም በአብዛኛው ይከተሉት የነበርው የጦር ስትራቴጂ ፈረንጆቹBattle of annihilation የሚሉት ወይም ሙሉ ሃይልን በመጠቀም ጠላትን ነጥሎ መደምሰስ ነበር በአድዋ ጦርነት ላይ ግን ስልታቸውን ቀይረው በተለያየ ግንባር ጀነራሎቻቸውን አሰልፈው ስለነበር የጣሊያን ጦርን በመበተን ታሪካዊ ድል ተጎናፅፈዋል ጄኔራል ባራቴሬም የአፄ ሚኒሊክን የጦር አሰላለፍ ባለመረዳት አሳፋሪ ሽንፈትን ቀምሷልጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ በአድዋ ጦርነት በደረሰበት አስከፊ ውርደት እና አሳፋሪ ሽንፈት ተሸማቆ ስልጣኑን ለቆ ቡኃላ እራሱን የገደለ ቢሆንም አንዳንድ የስውስጥ አዋቂዎች ግን አምልጦ በፀፀት እና በሀፍረት ከጣሊያን አገሩ ተሸሽጎ በ ኦስትሪያ እስከለተ ሞቱ ድረስ እንደኖረ ይናገራሉመጋቢት 4 ቀን 1896 ዓም አትላንታ ኮንስቲቱሽን የተባለው ጋዜጣ በአሜሪካን ሃገር የጣሊያን ክፉ እጣ በሚል አርዕስት የኢትዮዽያ ህዝቦች ጣሊያንን ማዋረዳቸውን አትቶ: ጄኔራል ኦሬስቴ ባራቴሬ በከፍተኛ ውርደት ራሱን ማጥፋቱን ገልፆ ፅፏልአባቶቻችን እና እናቶቻችን በአጥንት እና ደማችው ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ተምሳሌት የሆነችውን አገራችንን ኢትዮዽያን ባህሏን እና ኃይማኖቶቿን ጠብቀው አውርሰውናል ክብር ለቆራጥ እና ጀግኖች አባቶቻች እና እናቶቻችን!!ተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነጻነትሰው ተከፍሎበታል ከደም እና ከአጥንትስንት ወገን ወደቀ በነጻነት ምድርትናገር አድዋ ትናገር ትመስክርትናገር አ ድ ዋ ትናገር አገሬእንዴት እንደ ቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬአድዋ ዛሬ ናት ..አድዋ ትናንትመቸ ተረሱና የወዳደቁትምስጋና ለአድዋ ..ምስጋና ለጀግኖች ለዛሬ ነጻነት ላበቁን ወገኖችየጥቁር ድል አምባ...አፍሪካ ..እምዬ ኢትዮጵያ
አድዋ መታወቂያችን ምኒልክ ታዳጊያችን ኃይሌ ላሬቦየአድዋ ጦርነት በኢትዮጵያውያን እይታከኃይሌ ላሬቦበዚህ ወር መግቢያ ላይ ኢትዮጵያዉያን የአድዋን መቶ ኻያኛውን ያመት በዓል በያሉበት በአድናቆት አክብረውታል በየሬድዮ ጣቢያዎቹ በየፓልቶኮቹ በየማኅበራዊ ድርጅቶችና ኢትዮጵያውያን በየተሰበሰቡበት ሁሉ ስለአድዋ ያልተናገረ ያላሰበ ወኔው ያልተቀሰቀሰ የለም ማለት ይቻላልእንደታላቅነቱና ታሪክነቱ ከሆነ የአድዋ ድል ያንድ ቀን ብቻ በዓል መሆን የለበትም የትም አገር ሂደን ታሪክ ብንመረምር መዛግብታቸውን ብንገለባብጥ የአድዋን ዐይነት ታሪክ የሠራ ሕዝብም አገርም የለምና የአድዋ ድል አሜሪቃ ነፃነቷን ካገኘችበት ድል ከፈረንሳይና ከሩሲያ አብዮት የደቡብ አፍሪቃ ጥቊሮች በጨቋኞቻቸው ነጮች ላይ ካገኙት የእሪና ድል እጅግ ይበልጣል ጦርነቱ ከውጩ ሲታይ በሁለት ራሳቸውን በቻሉ ነፃና ልዑላን በሆኑ አገሮች መካክል ቢሆንም ጥያቄው ቀጥለን እንደምናየው ስለሰው ዘር መብትና እኩልነት ነውለኢትዮጵያውያን የአድዋ ድል የማንነታቸው መግለጫየልዕልናቸውና የነጻነታቸው ማረጋገጫ ነው ሊባል ይገበዋል ግን እንደአብዛኛው ድል ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ብቻ አይመለከትም ለሌላውም ዓለም ሁሉ ይትረፈርፋል በዚያን ዘመን ጨቋኝ ለነበረው ለነጩ ዘርም ሆነ ለተጨቋኙ ያለም ሕዝብ የነፃነት ፋና ነበር ድሉን ተከትሎ ጥቁር ሕዝብ በያለበት ሁሉ ኢትዮጵያዊነት ለተባለ ለብርቱ የሃይማኖትና የፖሊትካ እንቅስቃሴ መሠረት ሁኖ አገልግሏል ለነጩ ከኢስብአዊነቱ ጭካኔ ነጭ ላልሆነው ዘር ደግሞ ከሚማቅቅበት ከነጭ የባርነት ቀንበር ሁለቱም ነፃ የሚወጡበት ጊዜ ሩቅ እንዳልሆነ ያበሠረ ድል ነው የድሉ ወሬ እንደደረስው በእንግሊዝ መናገሻ በሆነችው በለንደን ከተማ የሚታተመው ዘታይምስ ጋዜጣ ይኸንን በማያወዛግብ ሁኔታ ጥርት አድርጎ እንዲህ ሲል አስቀምጦታልኢጣልያኖች በጀብድነትም ሆነ በጦር ስልት ከሌሎቹ አውሮጳውያን አያንሱም .. ድሉ የመላ ጥቊር አፍሪቃ ድል መሆኑ አይካድም ይኸም አስተያየት ወደፊት እያየለ ሄዶ በግልጽ የሚታይ ነው ወሬው በነፋስ ክንፍ በረኻውን አቋርጦ እየበረረ በመጓዝ በነዚህ አገሮች ከጫፍ እስከጫፍ ተዛምቶ ሲያበቃ አፍሪቃውያን አውሮጳውያንን ማሸነፋቸው አይቀርም የሚለውን ስሜት አነቃቅቷል ነገሩ አስጊ በመሆኑ በኢጣልያኖች መሸነፍ መደሰት ለነጮች ተገቢ አይደለም ሽንፈቱ የሁላችንና የሌሎችም ጭምር ሽንፈት ነው ዛሬ ቅኝ ገዢ የሆነችውና ከዚያም ባሻገር የነገይቱ አውሮጳ ሽንፈት ነውዘታይምስ ግልጽ ያላደረገው ነገር ቢኖር በአድዋ የተዋጋው የኢጣልያን ጦር በቊጥር ብዛትም ሆነ በዘመናዊ የጦር መሣርያውና የወታደሩ ጥራት ባፍሪቃ ምድር ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ ማንም የአፍሪቃ አገር ያልተጋፈጠው የጦር ዐይነት መሆኑን ነው ሌላው መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ደግሞ የአውሮጳውያንን ጦር ያሸነፈችው ኢትዮጵያ ብቻ አልነበረችም በ፲፰፻፳፫ ዓ.ም. አሁን የጋና መንግሥት አካል የሆነው አሻንቴ በመባል ይታወቅ የነበረው አገር ዓለምን ከጫፍ እስከጫፍ ድረስ ከመቈጣጠርዋ የተነሣ ፀሐይ የማይጠልቅበት መንግሥት እየተባለ የሚነገርላትን የእንግሊዝን ጦር ደምሰሶ የጦር መሪዎቹን ቸብቸቦ ለሰለባ ዳርጓል እንዲሁም በጥር ፲፰፻፸፰ ዓ.ም. የዙሉ ንጉሥ ሴትዋዮ የእንግሊዝን ወራሪ ጦር በእስንድህልዋና ጦርነት ድል አድርጎ ለወሬ እንኳን የሚሆን ሳያስቀር ድምጥማጡን አጥፍቶታል ሁኖም ብዙም ጊዜ ሳይቈይ ባላንጣቸው በተከታታዩ ጦርነት ነፍስ ዘርቶ ተደራጅቶ ሲመለስ አሸናፊዎቹ የተቀዳጁት አኩሪው ድል ከንቱ ሁኖ ቀረ በአንጻሩ የአድዋ ድል ከመጀመርያውኑ የለየለት ነበር ይኸ ድል አውሮጳውያን በዕውቀት አቻ የሌላቸው በትምህርት የተራቀቁ በሀብት የበለጸጉ በመሆናቸው በጥቁርና በብጫ ሕዝብ በፍጹም ሊሸነፉ አይችሉም የሚለውን ዘመናት ያስቈጠረውን እምነትና አስተሳሰብ ውድቅ ስላደረገው በመላው ነጭ ዘር ላይ ከፍተኛ ራስ ምታት እንዳሳደረ ጥርጥር አልነበረም ስለዚም ነው ከላይ የተጠቀሰው ዘታይምስም ሆነ በዘመኑ በጋዜጣነቱ የታወቀውን ሞርቶን እስታንለይን የመሳሰሉ ጸሓፊዎች ኢጣሊያ በጥቁር ሕዝብ ተሸንፋ ራሷ ኀፍረትን ተከናንባ ነጭንም ዘር አስዋርዳ መቅረት የለባትምና በርካታ ጦር ልካ ብልሃቷን አሻሽላ እንደገና ተመልሳ እንዲትዋጋ እያበረታቱ የጻፉትና ጩኸታቸውንም ያስተጋቡ የነበሩት ግን ሁሉም ከንቱ ሆነባቸው ሽንፈት ዕጣዋ የሆነባት ኢጣልያን እንኳን ነፍስ ዘርታ ተነሥታ ተመልሳ ባዲስ ኀይልና ብልሃት ሊትዋጋ ይቅርና ያገሯ መንግሥት ራሱ ከሥልጣኑ ወድቆ ከሥራው መባረር ጽዋው ሆኖ ቀረየአድዋ ድል የኢትዮጵያን ህልውናዋንና ነፃነቷን ባለም መድረክ ላይ በግሁድ ለማረጋገጥ በቃ ከአድዋ በፊት የተለያዩ ቄሳራውያን አገሯን ሊቦጫጭቋትና ሊቈራርሷት ሲሉ ለኻያ አምስት ዓመታት ያህል ሳያቋርጡ ወሯታል ግብጾች በማያዳግም ሁናቴ በጉንዴት በጒራዕ ባፄ ዮሐንስ እንደተመቱ ኢጣልያኖች ብቅ አሉ እነሱም በጉልበታቸው በብልሃታቸውና በመሣርያቸው ተማምነው በዲፕሎማሲ ሊበገሩ በልመና ሊታገቱ አልፈለጉም ለነገሩማ የእነሱንም ጦር ቢሆን በዶጋሌ ለወሬ እንኳን የሚሆን እስከማይቀር ድረስ ታላቁ ጀግና ራስ አሉላ ደምስሰዋቸው ነበር የኋላ ኋላ ግን ቈይተን እንደምናየው አፄ ዮሐንስ አርቀው ካለማሰብም ይሁን ሳይገነዘቡም ቀርተው ወይንም በመዘንጋት ደጋግመው በሠሩት ስሕተት እሳቸው በድንገት እንዳረፉ ከዚያ ተወስነው ከሚኖሩበት ከባሕር ጠረፍ አገግመው ተነሥተው ልጃቸውን ባንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ሦስቴ አከታትለው ሲያሸንፉ ተቈርጦ የነበር ወሽመጣቸው ታድሶ የልብ ልብ ተሰማቸው ከዚያ ወዲያ ማን ያቁማቸው እነሱ የፈለጉትን ካላገኙ ማለትም ኢትዮጵያን ጥገኛቸው ካላደረጉ ይኸም ካልሆነ ደግሞ ቢያንስ ከመሬቷ ሰፊ ይዞታ ተቈርሶ ካልተሰጣቸው ለጦርነት እንጂ ለድርድር እንዳልተዘጋጁ ደጋግመው አስታወቁ ለማሸነፉ ምንም ጥርጥር አልነበራቸውም ጦርነቱን በብልሃትና በጀግንነት እንዲመራ የተላከው አዲሱ የጦር መኰንንና የኤርትራ ገዢ የነበረው ጀኔራሉ ባራቲየሪ ወደኢጣልያን አገር ተመልሶ በሄደ ጊዜ ይኸንን ቊልጭ አድርጎ አስቀምጦታል የኢትዮጵያን ጦር ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ምኒልክን ራሱን በቀፎ ውስጥ ይዤው አመጣዋለሁ እያለ በየቦታው እየዞረ ሲፎክርና ሲደነፋ ሕዝቡም አምኖት በየደረሰበት በእልልታ በሆታ በዘፈንና በጭብጨባ እየተቀባበለ ሲያጅበውና ሲሸነው ሰነበተ ሐቁ ግን እሱ እንደሰበከው ስብከት እንደነዛው ጒራ አልሆነም ይልቅስ የጓዶቹ እንደነአልበርቶነና ዳቦርሚዳ የመሳሰሉት ጄኔራሎች ሕይወታቸው በጦር ሜዳ የሰማይ አሞራና የዱር አውሬ ሲሳይ ሁኖ ሲቀር እሱ ግን ያንን ሁሉ ጒራና ድንፋታ ረስቶ እሾህና ጒድጓድ ሳይለይ እግሬ አውጭኝ እያለ ወታደሩን ጥሎ በመሸሽ አመለጠ ለኢጣልያን ሕዝብ ምኒልክን በቀፎ ውስጥ ይዤላችሁ እመጣለሁ ብሎ ቃል የገባው ታላቁ የጦር መኰንን ብዙም ሳይቈይ ከሥልጣኑ ተሽሮ ወዳገሩ ተጠርቶ እግሩ እንደገባ የጠበቀው ክስና ፍርድ ቤት ነበርየአድዋን ድል ወደጦርነት ከመሩት ቅድመ ሁናቴዎች ትይዩ ብናይ የድሉን ምንነትና ታላቅነት ባገርም ሆነ ባለም አቀፍ ደረጃ በደምብ እንድንገነዘብ ይረዱናል አንድ ኤድዋርድ ግበን የተባለ ገናና እንግሊዛዊ ታሪክ ጸሓፊ ስለኢትዮጵያ ሲናገር ካለው ልጀምር ግበንኢትዮጵያውያንን ዓለም ረስቷአቸው እነሱም ዓለምን ረስተውት ላንድ ሺ ዓመት እያንቀላፉ ቈዩ ይላል ግበን እንደዚህ ሲል ኢትዮጵያ የሚትባል አገር በካርታ ላይ አልነበረችም ወይንም አንዳንድ ኢትዮጵያውያን አልፈው አልፈው ባለም መድረክ ላይ ብቅ ጥልቅ ማለት እንኳን አቆሙ ማለቱ አይደለም ሊል የፈለገው በአክሱማውያን ዘመን ባለም መድረክ ላይ በከፍተኛ ደረጃ የተጫወቱትን ሚና ረስተው የዓለምን ታሪክ ሂደት በመልካቸው ከመቅረፅም ሆነ በእምነታቸው ከመምራት ራሳቸውን አገልለው በትንሽቷ በገዛ ራሳቸው ዓለም ውዝግብ ውስጥ ተወጥረው የውስጥ ቤታቸውን ሥራ ከመሥራት አላለፉም ማለቱ ነው ከአክሱም ውድቀት በኋላ ኢትዮጵያውያን በየጊዜው የውጩን ዓለም ከመጐብኘትም ሆነ ከመጐበኘት አቋርጠው አያውቁም ቢባል ሐሰት አይደለም ጒብኝቶቹም በአገሩ ውስጥ አንዳንድ አዳዲስ አሳቦች እንዲገቡበት ቢረዱም በዚያው ልክ ደግሞ ጉዳትንም አላመጡም ማለት አይቻልም ብዙም ሳንራቀቅና ረጅም ዘመን ሳንሄድ በዐሥራ-ሰባተኛው ዘመን ጶርቱጌዞች ያመጡትን መዘዝ ማየት ይበቃል እንደመሰለኝ ይኸን ብቻ አይደለም ግበን ሊል የፈለገው ጥንት ባለም መድረክ ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳልተጫወተች ሁሉ አገሯ ምንነቷ እንኳን እስከመጥፋት የቈዳዋ ስፋት እስከመመንመን ገጽታዋ እስከመደብዘዝ ደርሶ ነበር ማለቱም ሳይሆን አይቀርም አገር ማለት ሰንደቅ ዓላማ ማንጠልጠል ብሔራዊ ባንክ ባለቤት መሆን ብቻ አይደለም ባለም ደረጃም በተለያየ መልክ ተከብሮና ተፈርቶ መኖርንም በተለያየ መስክ ሚና መጫወትንም ይጠይቃል ከአክሱማያን ወዲያ ኢትዮጵያውያን ለዚህ አልታደሉም ነበር የአድዋ ድል ለዚህ በሩን በርገግ አድርጎ ከፈተ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የተውትን የክብር ቦታ ባለም መድረክ ያዙብዙ ሕዝብ የመንግሥት ባለሥልጣኖችን ጭምር ከተለያየ ዓለም ወደአገሪቷ ጐረፈእንግዴህ የአድዋ ድል መታየት ያለበት ግበን በሚሰጠው አሳብ አንፃር ከሆነ ድሉ ለብዙ ዘመናት ትተኛ የነበረችውን አገር ከእንቅልፏ አነቃት ሲትነቃም ያስተጋባችው ድምፅ ከፍተኛና ወደር የሌለው ከመሆኑ የተነሣ በየተደመጠበት መላው የዓለም ሕዝብ ባግራሞትና ባድናቂት ተውጦ አብዛኛው በእልልታ ጥቂቱ ደግሞ በወዮታ ተቀበለው አገሪቷ ከአድዋ ተራራ ሁና እንዳንበሳ ግሣት ያስተጋባችው ጩኸት የማትደፈር ልዑልና ራሷን የቻለች ነፃ አገር መሆኗን በይፋ ከማስታወቅ አልፎ ያኔ ባለም ላይ ሰፍኖ የነበረውን የነጮችን ሥርዐት አርበደበደው አድዋ ለኢትዮጵያም ሆነ ለዓለም በሙሉ አዲስ ምዕራፍ ከፈተች የራሷን የአገሯን ብቻ ሳይሆን የመላውንም ዓለም ታሪክ ባዲስ መልክና ቅርፅ ሂደቱን እንዲትተልም አዲስ የታሪክ ንድፍ ተነደፈ አድዋ ለጨቋኞቹ ነጮች ያምባገንነታቸው ዘመን እንዳከተመ ከሥራቸው ሁኖ እየተገፋ ለሚኖረው ላለም ሕዝብ ደግሞ የነፃነታቸው ዕድሜ እንደተቃረበ አበሠረ እስከዚያም ድረስ ኢትዮጵያ በአድዋ በሠራችው ሥራ ለተጨቋኞቹ የነፃነት ጩራ የቅኝ ግዛት ተስፋ ላስቈረጣቸው እንዲሁም የነጮች አምባገንነት ለመረራቸውና ላስፈራራቸው የድላቸውና የአርነታቸው ዕርቡንና አለኝታ ሁና ቈየች የአውሮጳውያን ዕብሪት ያንገፈገፋቸው ጃፓኖች ለምሳሌ የአድዋን ድል ባለም ታሪክ በነጮች ዘር ላይ ደርሶ የማያውቅ ውርደት አድርገው አዩት በሺ ዘጠኝ መቶ ዐራት ዓመተ እግዚእ ዓ. እ. ላይ እነሱ ራሳቸው የአድዋን አብነት በመከተል በታሪክ ሁለተኛውን ቦታ ለመያዝ በቁ ቈይተው የኢትዮጵያ ሊቃውንትም በበኩላቸው የጃፓንን ሥልጣኔ ለመቅዳት ትኩረታቸውን ከአውሮጳ ይልቅ ወደጃፓን ማዞር ጀመሩ የነዚህ ሁለት ኀይለኞች የሆኑ የጥቊር ዘርና የብጫ ዘር መቀራረብና መፈቃቀር ወደሺ ዘጠኝ መቶ ሠላሳዎቹ ላይ እየተጠናከረ መሄዱ በአውሮጳውያን ጓሮ በጣም አስጊ ሁኖ በመታየቱ በጣምም አከራከራቸው ኢጣሊያንም ለሁለተኛ ጊዜ ኢትዮጵያን እንዲትወርር ካነሣሧት ውዝግቦችና ሰበቦች አንዱ ይኸው ወዳጅነትና መቀራርብ ሳይሆን አልቀረም ተብሎ በጽኑ ይታመናልኢትዮጵያ በአክሱማውያን ዘመን ካለም መሪነት ሲትወጣ በጽሙናና በጽማዌ ሲሆን ተመልሳ የገባችው ግን በአድዋ በተጐናፀፈችው ድል ምክንያት በታላቅ ጫጫታና ሁካታ ግርማ ሞገስና ዝና ተጐናጽፋ ነው ቢባል እውነትነት አለው በድሉ ማለዳ ከዚህ በፊት በንቀትና በትዕቢት እንዳንድ ነፃ አገር ሊያዩዋትና ሊደራደሩ ዝግጁ ያልነበሩ የአውርጳ ታላላቅ መንግሥታት ነን ባዮች አላንዳች እፍረት ወደመናገሻ ከተማዋ እየተሽቀዳደሙ መጒረፍ ጀመሩ ካድዋ በፊት አገሪቷ የልማት ሥራ እንዳትጀምር የተለያየ ምክንያት በመፍጠር ዕንቅፋት ሁነው የነበሩትም የግንባታ ተግባር ላንዱ አውሮጳዊ አገር ተሰጥቶ ሌሉቹ ብዶ እጃቸውን እንዳይቀሩና ሌላው ቢቀር ትራፊ እንኳን እንዳያመልጥባቸው ለመሰብሰብ ሲሉ በለማኞች ወኪሎቻቸው የአፄ ምኒልክን ግቢ አጥለቀለቁትየአድዋ ድል ታላቅነቱ ይበልጥ የሚገለጠው ከጊዜው ጭብጥ ያለም ታሪክ ሁናቴ ሲታይ ነው አሜሪቃ ታስሳ ተገኘች ከተባለበት ከዐሥራ ስድስተኛው ዘመን ጀምሮ አውሮጳውያን ራሳቸውን ከሌላው የሰው ዘር የተሻሉና የበለጡ ብቻ ሳይሆን የበላይም እንደሆኑ በጡንቻቸው ለማረጋገጥ በቅተዋል ደካማነትንና በዘመናዊ ሥልጣኔ ወደኋላ ቀርነትን ከአውሬነት እስከማመሳስል ደርሰው ነበር ከዚህም የተነሣ የክፍለ-አህጉሮቹን ነዋሪዎችታሪክ ለዕልቂት ዳርጓቸዋል በማለት የአሜሪቃን የአውስትራሊያንና የሌላውንም አገር ተወላጅ በጦር ሜዳና በፍልሚያ ካሸነፉት በኋላ በተለያየ መንገድና ዘዴ ገድለው እስከመጨረስ ሲደርሱ ትኩረታቸውን ወደእስያ ከዚያም ወዳፍሪቃ አዞሩ አፍሪቃን በተመለከተ አንድ ከፍተኛ ስጋት ያሳደረባቸው ነገር ቢኖር ክፍለ-አገሩን ሲቀራመቱት የርስ በርስ ጥል የሚጭር አለመግባባት ተፈጥሮ ራሳቸው እንዳይተላለቁ ነበር ዋናው ይኸ ይሁን እንጂ ሌላም ተጨማሪ ፍራቻ ነበራቸው ይኸውም ከዚህ በፊት በአሜሪቃና በአውስትራሊያ እንደሆነ ሁሉ የአፍሪቃም ክፍለ አገር በተወሰኑ በሁለትና በሦስት የአውሮጳውያን መንግሥታት እጅ ብቻ ወድቆ እንዳይቀር የሚል ነበር እንግዴህ ለእነዚህ አስጊ ውዝግቦች እልባት ሊሰጥ ሲል ነው ያነ የጀርመኑ መንግሥት መሪ የነበረው ኦቶ ቮን ቢስማርክ በአውሮጳ አቈጣጠር በ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ታላላቆች ናቸው የተባሉትን የአውሮጳውያንን መንግሥታት ስብሰባ በበርሊን ከተማ የጠራው ኢጣልያም ኢትዮጵያን እንዲትከጅልና በማጭበርበርም ሆነ በጉልበት በመሬቷ እግሯን እንዲታስገባ ከዚያም ወደአድዋ እንዲታመራ ያበቃትም ይኸው የበርሊኑ ጉባኤ ነው ጉባኤው አፍሪቃን በሚመለከት አያሌ ውሳኔዎች ያስተላለፈ ቢሆንም አንኳር ሁኖ የሚታየው ግን አውሮጳውያን በአፍሪቃ ውስጥ ያካሄዱ የነበሩትን የመሬትን ቅርጫ ካጸደቀውና ከባረከው በኋላ በተሻሚዎቹ መንግሥታት መካከል አለመግባባትን በማይፈጥርበት መልኩ እንዲካሄድ ሲል ሦስት ቀንድ የሆኑ ውሳኔዎችን አስተላለፈ ከነዚህም አንደኛው ያፍሪቃን መሬት ለመቈጣጠር የሚፈልግ አውሮጳዊ መንግሥት በመጀመርያ ደረጃ ከአፍሪቃዊው ገዢ ካልሆነም ይኸም ማለት አገሩ መንግሥት-አልባ ከሆነ ደግሞ ከሕዝቡ ጋር የንግድ ውል መዋዋል ይኖርበታል ይላል ከዚህም ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ተዋዋዩ አውሮጳዊ መንግሥት ድርድሩ እንዲጸናለትና እንዲታወቅለት ከፈለገ በበርሊን ጉባኤ ለተፈራረሙት ታላላቅ መንግሥታት ስምምነቱን እንዲያስታውቅ ያስገድዳል ይሁንና ይኸው ተፈራራሚው አውሮጳዊ መንግሥት ከተቻለ በሰላማዊ መንገድ ካስፈለገም ደግሞ በጉልበቱ አገሩን እቊጥጥሩ ሥር እስካላደረገ ድረስ የውሉ መሬት ለማንም ሊይዘው ለፈለገ የአውሮጳ ኀይል ክፍት እንደሆነ ይገልጣልየበርሊን ጉባኤ የነጭ ዘር አፍሪቃን እንዴት መቀራመት እንደሚገባ ውሳኔውን በወረቀት እንዳሰፈረ አውሮጳውያን በተወላጆቻቸውና በምንዶቻቸው ያፍሪቃን ገዢዎችንና ሕዝብን በማታለል የንግድና ጥበቃ የመስጠት ውል ማስፈራረም ተያያዙበት አስፈራራሚዎቹ ጀሌዎች ብዙውን ጊዜ የሃይማኖት ሰባኪዎችንና ዘመዶቻቸውን የንግድ ድርጅቶችንና ነጋዴዎችን የመልክዐ-ምድር አሳሾችንና አስመሳይ የዕውቀት ተመርማሪዎች ነን ባዮችን ያጠቃልላል ማለት ይቻላል ለምሳሌ ያህል መንግሥተ-አልባ በሆኑት የሱማሌ ባላባቶች ግዛቶች የምሥራቅ አፍሪቃዊው የእንግሊዝ የንግድ ኩባንያ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ካሥራ ስድስት በላይ ከሆኑ የተለያዩ የጐሦች መሪዎች በቀኝ ጣታቸው እያስፈረመ ውል ተዋዋለ1 ከነዚህም ያገኛቸውን መሬቶች አጠራቅሞ ሲያበቃ የሱማሌ ምድር ሱማሌላንድ የሚባል ስም ሰጥቷቸው አንድ በታሪክ ያልነበረ አገር ፈጠረ ፈረንሳዮችም በዚሁ መልክ በኦቦክ በታጁራና በጂቡቲ የነበሩትን የጐሦች መሪዎች በገንዘብም በእህልም እያታለሉ በማስፈራረም የዛሬዋ ጂቡቲ እንዲትወለድ አበቁ ኢትዮጵያም የጨለማና የድብልቅልቅ የነበረውን ዘመነ መሳፍንትን ከታሪኳ ነጥላ ጥላ ያንድነቷን የሕዳሴ መሠረት ሊትጥል ታጣጥር በነበረችበት ወቅት አንድ አባ ዮሴፍ ሳፔቶ የተባለ የካቶሊክ ቄስ በሺ ስምንት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ዓ.እ አንዲት ብጣሽ መሬት ካንድ የእስላም ባላባት ገዝቶ ለኢጣልያን የንግድ ኩባንያ ሰጠ በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ ሌላ ጨምሮ ገዛና ቀናትም ሳይቈይ እሱ ራሱ የኢጣሊያንን ሰንደቅ ዓላማ ስቅሎ በተገዙት መሬቶቹ ላይ አውለበለበበት እንግዴህ በአብዛኞቹ የአፍሪቃ ክፍለ አገሮች እንደተደረገ ሁሉ በኢትዮጵያም የባሕሯን ጠረፍ ለመያዝ ፊታውራሪዎቻቸው ሁነው የአውሮጳን ቅኝ ገዢዎች እየመሩ የመጡት የየአገራቸው ቀሳውስትና ነጋዴዎች ነበሩ የተገዙት መሬቶች ምንም ቅንጣቢ ቢሆኑም ያገራችን ምሳሌዊ አነጋገር ፈረንጆች እንደመርፌ ይገቡ እንደዋርካ ይሰፉ እንደሚለው ቀስ በቀስ አካባቢውን ገፍተው እየያዙ በመንሰራራት በአድዋ ጦርነት የራሷን የኢትዮጵያን የልዕልናዋንና የነፃነቷን ህልውና እስከመፈታተን በቁኢጣልያኖችንም ከአፄ ምኒልክ ጋር በውጫሌ እንዲደራደሩ ያነሣሣቸው የበርሊኑ ጉባኤ ውሳኔ እንደነበር ከቶውኑ አያጠራጥርም ውሉንም ያካሄደው አንቶኔሊንጉሡ እንደቅርብ ወዳጃቸውና አማካሪያቸው ያዩት የነበረው የካቶሊኩ የአቡነ ማስያስ የቅርብ ዘመዳቸው ነበር አፄ ምኒልክ ከዚህ ዕውቅናና ቅርበት የተነሣ ያታልለኛል ብለው እንዳላሰቡ የሚያጠራጥር አይመስለኝም በአንቶነሊ እምነት መሠረት የውጫሌ ውል ለኢጣልያን የበርሊኑን ጉባኤ የመጀመርያውን ውሳኔ አሟልቶላታል የሁለተኛውን ውሳኔ ግብ ለመምታት ግን የውሉን አንቀጽ ዐሥራ ሰባት ትርጒም ማወዛገብ ግድ ሆነበት አለበለዚያማ ኢጣሊያን ምኑን ይዛ ናት ኢትዮጵያ የኢጣሊያን መንግሥት ጥገኛ ግዛት ናት ብላ የበርሊኑ ውሳኔ በሚጠይቀው መሠረት ለታላላቆቹ የአውሮጳ መንግሥታት የሚታስታውቀው ኢጣልያኖች ልበቅኑ ቢሆኑማ ኖሮ የዉሉ አንቀጽ ዐሥራ ዘጠኝ የተደረገው ውል በአምሐርኛና በኢጣልያንኝ ቋንቋ ትክክል ሁኖ መገልበጥ አለበት ይል የለም እንዴ ትክክል ካልሆነ ማስተካከል እንጂ ምን ያነታርካል ለምንስ ወደጦርነት ይኬዳል በዚህ ረገድ አፄ ምኒልክም ቢሆኑ ሊፈራረሙ የወሰኑት በንጹሕ ልባቸው ነው ብሎ ማሰቡ የሚያዋጣ አይመስልም ንጉሡ ገር ቢመስሉም አርቆ የማስብና ነገርን በሰፊው አጥልቆ የማመዛዘን የሚያዋጣቸውንና የማያዋጣቸውንም አቅርቦ የማየት ከፍተኛ ስጦታ ያላቸው መሆኑን በጊዜአቸው የነበሩት የውጭ አገርም ሆኑ ያገር ውስጥ ጸሐፊዎች ይመሰክራሉ በዚህ አንጻር ሰንመለከት ውሉ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ከፍተኛ የተቀነባበረ ሤራ በየአቅጣጫው በኢጣሊያንና በሌሎች አውሮጳውያን እየተሰነዘረ መሆኑን ተገርመው አይተው በመገንዘብ አደጋውን ለመጋፈጥ እስኪዘጋጁ ድረስ ጊዜ ለማግኘት ያህል ብቻ ብለው ያደረጉት ሊሆንም ይችላል ማለቱ ከሐቅ የራቀ አይመስልም የአድዋ የክተት አዋጃቸውም ሆነ ከዚያም በፊት ለአውሮጳ መንግሥታት የአገራቸውን የድንበር ወሰን እየዘረዘሩት የላኩት ደብዳቤ ግባቸው ይኸ መሆኑን ያሳያል ከላይ የተጠቀሰው ዘታይምስ ጋዜጣም ኢጣሊያኖች ያሳመኑት መስሏቸው ሲታለሉ ምኒልክ ግን ተገቢውን ዝግጅት ያደርግ ነበር ሲል ይኸንኑ አሳብ ያጠናክራል የማታ ማታ ግን ከሳቸው በፊት አፄ ዮሐንስ የሂወት ውል በመባል የሚታወቀውን ስምምነት በመፈረም የእንግሊዞች የተንኰል ሰለባ እንደሆኑ ሁሉ አፄ ምኒልክም በውጫሌ ውል ኢጣሊያኖች ያታልሉኛል ብለው የተጠባበቁ አይመስልም ልክ እንዳፄ ዮሐንስ ጉዱን ያወቁት ቈይተው ነው ማለት ይቻላልበአፄ ምኒልክ አሻፈረኝነት ኢጣሊያኖች በሰላም ሊፈጽሙት የፈለጉት ኢትዮጵያን ግዛታቸው የማድረግ ተግባር ለመጨናገፍ ስለደረሰ ሦስተኛውን የቤርሊንን ጉባኤ ውሳኔ በግብር ለማዋል ኀይል መጠቀምና ወደጦርነት መሄድ የግድ ሆነባቸው አንቶነሊ ኢቴጌ ጣይቱን አማርኛውን ትተው በፈረንሳይኛ የተጻፈውን ውል ይመልከቱ ቢላቸው ኀይለኛዋ ንግሥቲቷም እኛ እምናውቀው በአማርኛ የተጻፈውን ነው እንጂ የፈረንጅ ቋንቋ አናውቅም አንተ ግን ቋንቋችንን ስለምታውቅ እየው ቢለው ቢመልሱለት የዉሉን ወረቀት ቀዶ ሲያበቃ የኢጣሊያ መንግሥት ውሉን በጦር ኀይል ታስከብራለች አላቸው በኢጣሊያኖች እይታ ኢትዮጵያ እንደተረዳችው ዉጫሌ የወዳጅነትና የንግድ ስምምነት ሳይሆን የአገርን ልዕልናና ነፃነት በሰላም አሳልፎ የመስጠት ነበር ማለት ይቻላል በኢጣሊያኖች አስተያየት ይኸ ካልሆነ ደግሞ ለኢትዮጵያ መዘዙ ጦርነትና ተሸንፎ መዋረድ ነበር ነገሩ እንዴት ጥቊር ዘር ለነጭ ዘር አልገዛም ይላል ነው በዘመኑ የነበሩትን የነጮችን አስተሳሰብ እጭንቅላታቸው ውስጥ ገብተን እንደነሱ ማሰብ ከቻልን በኢትዮጵያ እምቢተኝነት ኢጣሊያኖች በጣም ሳይገረሙ አልቀሩም ስለዚህም ነው ሌሎቹ አውሮጳውያኖች በኻያ አምስት ዓመት ውስጥ መላዪቷን አፍሪቃን ለመያዝ እንደበቁ ሁሉ እነሱም ኢትዮጵያን በጥቂት ሰዓታት ገፋ ቢልም ደግሞ በቀናት ውስጥ ከሥራችን እናደርጋታለን ብለው በማሰብ የተነሡት ግን አልሆነላቸውም ኢትዮጵያውያን ለመጀመርያ ጊዜ እስከአፍንጫቸው ድረስ ታጥቀው የመጡባቸውን ነጮች ራሳቸው በሠሩት ጠመንጃና ጦር አወደሟቸውና አሳፍረው ሸኟቸውፈረንጆች በአድዋ በጥቊር ሕዝብ መሸነፍ ዱብ ዕዳ ሁኖባቸው ያልታሰበ ከፍተኛ ራስ ምታት ፈጠረባቸው የተለያየ ማደንዘዣም ሆነ ማስታገሻ ፈልገው ሊታከሙና ከበሽታው ሊገላገሉ ይኸም ካልሆነ ደግሞ በሽንገላም ቢሆን ሊፈወሱ ሞክረዋል ከዚህም የተነሣ ለአድዋ ድል የተለያየ ትርጒም እየሰጡ በጥቁር ኀይል እንዳልተሸነፉ ለማስረዳት ታጥቀው ተነሡ አንዳንዱ የአድዋ ድል የሚያሳየን የኢጣልያኖችን አለመታደል እንጂ እንደሽንፈት መቈጠር የለበትም አለ አንዳንዱ ደግሞ ጥፋቱን በመሪው በጦር መኰንኑ ጀኔራል ባራቴሪ ችሎታ ማጣትና በኤርትራ ባንዳዎች በተለይም የኢጣልያን ሰላይ በነበረው በአቶ አውዓሎም ክሕደት ጫንቃ ላይ ጫነ ሌሉቹ ደግሞ ኢጣልያኖች አካባቢውን በደምብ ካለማወቃቸው የተነሣ ግር ስላላቸውና የጦር ሜዳው ጐጣጐጥነትና ኰረኰንችነት ለኢትዮጵያውያን አመቺ ስለነበር ነው አሉ ገለልተኛ ሁኖ ለሚሰማ እነዚህ ሁሉ ምክንያቶች በግልጥ የሚያሳዩት ኢትዮጵያውያን ጣልያንን ያሸነፉት በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በጥበብም በብልሃትም ጭምር መሆኑን ነው ፈረንጆች ግን የነጭ ዘር በእውነት አልተሸነፈም ለማለት ይኸን ሁሉ ምክንያት ሲፈጥሩና ሲክቡ ንግግራቸው የግርምቢጦሽ መሆኑ የታየላቸው አይመስልም የኢትዮጵያውያን የጦር መሪዎችና ወታደሮቻቸው መማር ቀርቶ የጦር ትምህርት ገበታ ምን እንደሆነ እንኳን ሰምተውም አይተውም አያውቁም ያሸነፉት ጦር ግን ባለም ከፍተኛ ናቸው በሚባሉት የጦር ትምህርት ቤቶቻቸው ገብተው ተምረው በተመረቁት እንደነጄኔራል ባራቴሪና ኤሌና በመሳሰሉት ከፍተኞች የኢጣሊያን ጦር መኰንኖቻቸው የሚመራውን ጦር እንደሆነ ተረሳ ምንም የስለላ ምርምርና ጥናት ያልቀሰሙት ኢትዮጵያውያን በስለላ ተግባር ከፍ ያለ ዕውቀትና ትምህርት ያመረቱትና እሳት የላሱት ኢጣልያኖች ለራሳቸው እንዲሰልሉላቸው ብለው የቀጠሯቸውን ሰላዮችንና አስተርጓሚዎቻቸውን ራሳቸውን መልሰው በቀጣሪዎቻቸው ላይ ተጠቀሙባቸው እንግዴህ እነዚህ በነጮች ልዕልና አንጐላቸው የተበረዙት አውሮጳውያን ለኢጣልያን ሽንፈት ምክንያት ነው ብለው የሚቀባጥሩት ምክንያቶች የሚያስረዱን ምን ያህል ኢጣልያንን የሚያዋርዱ የኢትዮጵያውያንን ችሎታና ዕውቀት የሚያሞግሱ መሆኑን የተገነዘቡት አይመስልም የአካባቢውን ዕውቀት በተመለከተ የኢትዮጵያስ ጦር ቢሆን ጭብጥ እንኳን የማይሞላ ካካባቢው ከተመለመለው ጦር ካልሆነ በስተቀር አብዛኛው በጣም ሩቅ ከሆነ ከዳር አገር ማለትም ከደቡብ ከምሥራቅና ምዕራብ ከመስዕና አዜብ ከሊባና ባሕር በክተት የተሰበሰበና ምንም ዐይነት በትምህርት የገበየ የሥነምድር ዕውቀት የሌለው አይደለምን አመካኞቹ ሽፋፍነውና አድበስብሰው ሊያልፉ የሚፈልጉት እኮ ይኸ መሃይምን ጦር ልክ ከኢጣልያኑ እኩል ላካባቢው እንግዳ ለመሬቱ ባዳ ሁኖ ሳለ በመሬት ካርታ ሥራና በምድር አቀማመጥ ጥናትና ምርምር የተራቀቀውን የኢጣሊያንን ጦር በዕውቀትም በብልሃትም በልጦት ተገኘ ነው ታዲያ በተቻላቸው መጠን ሊሸፋፍኑት የሚሞክሩትም በግልጥ እንዲህ መናገሩ ከልክ በላይ የሚያሳፍር እንደሚሆንባቸው ስላወቁ ነው ማለቱ ይቀላል ሐቁ ግን ፍርደ-ገምደልነታቸውን ነው ፍርጥ አድርጎ የሚያሳየውፈረንጆች የሰጡት የኢጣልያን መሸነፍ ምክንያት ከላይ በተጠቀሱት ብቻ አላቆመም ጥቊርነታችንን ክደው ፈረንጆች እስከማድረስም ደርሰዋል በዘር ሐረግ ወንድሞቻቸው እንደሆንን በተራቀቀ ጥናትና ምርምር ለማረጋገጥ በቅተዋል የኒው-ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ በድሉ ማግሥት እጅግ የታደሉ አፍሪቃውያን በሚለው አርእስት ያወጣው የነጭነታችን መሠረትና ከአውሮጳውያንም ጋር ያለንን የዘርማንዘር ዝምድነታችንን እንዴት እንደሆነ እንደሚቀጥለው አድርጎ ይገልጣልኢጣልያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከአበሾች ጋር ያጋጠማቸው ሁናቴ የሚያመለክተው እነዚህ በአፍሪቃዋ እስዊዘርላንድ በሆነችው ተራራማ አገር የሚኖሩት አፍሪቃውያን አውሮጳውያን ቅኝ ግዛት ሲይዙና ሲቀረማመቱ ካጋጠሟቸው ጨለማ በለበሰው በአፍሪቃ ክፍለ አገር ከሚኖረው ከሌላው ጥቊር ሕዝብ የበለጠ ዘር መሆኑ በፍጹም አያጠራጥርም መብለጣቸውም ከጥንተ ትውልዳቸውና ከዘር ሐረጋቸው ጋር የተያያዘ ነው ያሁኑ ዘመን ኢትዮጵያውያን ከጥንት ወግና ታሪክ ሲወርዱ ሲዋረዱ የመጡ መሆናቸው ቢታመንም ሐቁ ግን ከቶውኑ ኢትዮጵያውያኖች1 . እያንዳንዱ ውል እኔ እገሌ የ ጐሣው ስም መሪ ራሴን መሬቴንና በሥሬ ያሉትን ሰዎች በሙሉ ይዤ የብሪታንያው የምሥራቅ አፍሪቃ የንግድ ኩባንያ ጥገኛ ለመሆን ወስኛለሁ በሱም በኩባንያው ግዛትና መንግሥት ሥር እንደመሆኔ ኩባንያው በመሬቴ ባገሬና በሕዝቤ ላይ የበላይ ገዢና አስተዳዳሪ መሆኑን ተቀብያለሁ ይላልማለትም ጥቊሮች አይደሉም ታዲያ በጥራታቸው ልክ ከአንግሎሳክሶኖችና ከኬልቶች በምንም ዐይነት የማይተናነሱ ጥርት ያሉ የነጭ ዘር ናቸው ቋንቋቸውም ሆነ የአካላታቸው ቅርጽ የሴማውያን ዘር አካል ያደርጋቸዋል ማለትም ታሪክ ከሠሩት ከጥንቱ ባቢሎናውያንና አሶርያውያን ሶርያውያንና አይሁዶች ጋር ይዘማመዳሉ በጥቊርነታቸው ላይ ብቻ ተመሥርቶ ኢትዮጵያውያን ብሎ መጥራቱ ትልቅ ስሕተት ነው ስሕተቱ የመነጨው ምናልባት ጥንት በሮማይስጥና በጽርዕ ሥነ-ጽሑፎች ከግብፅ ውጭ የታወቁት የአፍሪቃ ሕዝብ እነሱ ብቻ በመሆናቸው ሲሆን ከዚያ ተነሥቶ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ቀስ በቀስ አፍሪቃውያንን በሙሉ ለማመልከት በጥቅም ላይ መዋል ጀመረ አሁን ግን በመላው የአፍሪቃ ክፍለ-አገር ውስጥ የጥቊር ዘር አካል ያልሆነ ይኸ ሕዝብ ብቻ ቢሆንም ኢትዮጵያ የአገራቸው መጠርያ ስም ሆኖ ቀርቷል እንደሐቁ ከሆነ ግን አበሾች ከጥንት ጀምሮ በፍጹም የአፍሪቃ ዘርነት የላቸውም የጥንት ትውፊታቸውም ቢሆን ከደቡብ ዐረብ እንደመጡ ያመለክታል መልካም አጋጣሚ ሆኖ እስካሁን ድረስ በነጮች ወዳልታሰሰ ወዳንድ የደቡብ ዐረብ አውራጃ ለምርምር ጥናት አራቴ ሄዶ የነበረው የጀርመን መንገደኛ ኤድዋርድ ግላሰር ከክርስቶስ በፊት አበሾች በነዚህ አውራጃዎች ይኖሩ እንደነበረ የሚያመለክት ምንም የማያከራክር ማስረጃ እዚያው አግኝቷልነገሩ ቀልድ ነው እንዳንል አውሮጳውያን በጒሮሯችን ሊወረውሩ የሚፈልጉትን በሙሉ በምርምር አሳብበው እየፈለፈሉ እየሰጡን ሊያሳምኑን ደርሰዋል ጋዜጣው ይኸንን በሚጽፍበት ዘመን ለምሳሌ የሰውን ጠባይ አጥኚ ነን ባዮቹ የዕውቀት ተመራማሪዎቻቸው አንትሮፖሎጂስቶች የጥቊር ሕዝብ ጭንቅላት ከውሻ ጭንቅላት እንደማይበልጥ የጠለቀና የተራቀቀ ምርምር አድርገን በማያወላውል ተጨባጭ ማስረጃ ደርሰንበታል ይሉ አልነበረም ወይ የቅኝ ግዛትም አሳብ የተጠነሰሰውና እንደ መርህ አድርጎ የተከተለው በዚሁ ዐይነት ማስረጃ በመተማመን ነበር ማለት ይቻላል ለትዝብት ያህል ብቻ ላንሣውና የዘር አመጣጣችንን በተመለከተ ሌላ ይበልጥ አስተማማኝ የሚባል አስተያየት እንዳለም አለመርሳት ይገባል በህንድ አገር በጀብዱነታቸውና በአስተዳደር ጥበባቸው የታወቁት ሐቢሽስ የተባሉ ሰዎች በባርነትና በሌላም ረገድ ከአፍሪቃ የሄዱት ሲሆኑ በዘራቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው ይባላሉ የግላሰርን አሳብ ከተከተልን የኢትዮጵያዉያን ዘራቸው ለምን ከነዚሁ ሐቢሽሶች መጣ አንባልም እንዲያውም ግላሰርን በሁለት ሺ ዓመታት ቀድሞት የኖረው አፖሎንዮስ ዘትያኖና እንዲሁም ታላቁ የቤተክርስቲያን ባለታሪኩ ኤውሳብዮስም ጭምር ኢትዮጵያውያን ጥንተ ዘራቸው ከህንድ ፈልሰው ወይንም ተልከው መጥተው በዐባይ ሸለቆ ስፋሪዎች ሲሆኑ በጥበባቸውም የሚከተሉት አባቶቻቸውን ህንዳውያንን ነው በማለት ስለሚደግፉን ከግላሰር ፈጠራ ይልቅ ማስረጃው በትውፊት የተመሠረተ ቢሆንም የነሱ አፈ-ታሪክ የሚሻል ይመስለኛል1ወደዋናው ነገር እንመለስና ነጮች ራሳቸውን ሊያባብሉ ሲሉ በጥቊር ዘር አለመሸነፋቸውን ለማሳየት ያመጡት የአበሻና የኢትዮጵያ ትርጒምና የዘር አመጣጥ መዘዙ ከነሱ አልፎ ለኛም ተርፏል አሁን በሥልጣን ያለው መንግሥትም ሆነ በአውሮጳያን የትምህርት ገበታ ተምረው ሲያበቁ የጐጥና የጐሣ መሪዎች የሆኑ አጃቢዎቹ ፖለቲከኞችም ይኽንን የተረት ታሪክ በሰፊው እየተጠቀሙበት ናቸው ማለት ይቻላል ከነሱም አልፈው አንዳንድ ሁሉን ዐወቅን ባዮች የዩኒቬርሲቲ ምሩቃኖችና ምሁራኖችንም ጭምር እንዲሁም የበላይነት ስሜት አራጋቢዎችና ምናብን ከሐቅ የመለየት ችግር ያላቸው ወሽካቶች ሳይቀሩ ይኸንን ዐይነት አሳብ ያነበንቡታል ፈረንጆች ጥቊሮችን በመናቅ ያመጡት ወጥመድ ላገራችን ተርፎ ምስቅልቅላችንን እያወጣ መሆኑ ለብዙዎቻችን ግልጥ እየሆነ እንዳለ አልጠራጥርም በጦር ሜዳ ማሸነፍ ያቃታቸው ባመጡት ያሳብ መርዛቸው ግን ድል ለማድረግ ምንም አልቀራቸውም ተዘርረን እጃችንን ባንሰጥም ታላቅ ጉዳት አድርሰውብናል እያደረሱብንም ናቸው ማለት ይቻላል ከፈረንጅ ባገኘው ትምህርትና ምርምር መላቅጡ የጠፋበት አእምሮው የዞረበት ተማርሁ ነኝ ባዩ ትውልድ በሃይማኖትና በትውልድ በባህልና በቋንቋ በንግድና በሰፈራ ለዘመነ አዝማናት ተዋሕዶና ተሳስሮ የኖረውን ሕዝብ ሴማውያንና ኩሳውያን መጤና አገር-በቀል አቈርዝቋዥና ተቈርቋዥ እያሉ በመፈረጅ ባገሪቷና በሕዝቧ ከፍተኛ ጥቃት አድርሰዋል እያደረሱም ናቸው አጉል ትምህርትም ማለት ይኸ ነው ቢባል ሐሰት አይሆንምአድዋን ድል በተመለከተ ፈረንጆች ሊቀበሉት ያልፈለጉት ነገር ቢኖር ኢትዮጵያውያን ያሸነፉት በጦርነታቸው ስልትና ቅንጅት ባሳዩት ትብብርና ጀብዱ ካላቸው ያገር ፍቅር ስሜትና ወኔ የተነሣ የሚወዷትን አገራቸውን ከጠላት እጅ ለመከላከል ደማቸውን እስከማፍሰስ አጥንታቸውን እስከመከስከስ ድረስ ቈራጥ ሕዝብ መሆናቸውን ነው እነሱም ሆኑፈረንጅ በተጀነነበት ዘመን የነበረው ያስተሳሰብ ፈሊጥ ጥቊሮችና ሌላውም እነሱን በመሰለ የሥልጣኔ ደረጃ ያለው ሁሉ ሰብአ ትካት እንደመሆናቸው ከበረኻ አውሬ ስለማይለዩ በጐሣና በጐጥ ደረጃ እንጂ እንደሠለጠነው ሕዝብ የተራቀቀና የመጠቀ የአገር ፍቅር ይቅርና ፅንሰ አሳቡም ስሜቱም የላቸውም የሚል ነበር ልክ የዱር ወይንም ያልተገራ አውሬ ቢነካ ማለትም ቢጠቃ ላይሞት ወይንም መኖርያውን ላይለቅ ሲል ዐጸፋውን የሚመልሰው የደመ-ነፍስ ጉዳይ ሁኖበት እንጂ ስለራሱም ሆነ ስለመኖርያው አስቦና አሰላስሎ ጥቅሙንና ጉዳቱን ተረድቶ አይደለም እንደምዕራባውያን አስተሳሰብ ነጮች ያልሆኑትም አገራቸው በነጭ ዘር ሲያዝባቸው የደመ-ነፍስ ጉዳይ ሁኖባቸው ሊከላከሉ ይንፈራገጣሉ ይንፈራፈራሉ እንጂ ላገርና ለነፃነት ብለው አይዋጉም የሚል አሳብ ነው ተጠናውቶባቸው የነበረው ኢትዮጵያውያንም ተፈርጀው የነበሩት በዚሁ መልክ ነበር በነሱ አስተሳሰብ ኢትዮጵያዉያን ከሥልጣን ሽኩቻና ከግል ጥቅም ውጭ ትብብርና አንድነት ምን መሆኑን በማያውቁ ባላባቶች የሚመሩ የጐሦች ጥርቅማጥርቅም ናቸው ባላባቶቹ ከንጉሥ ሥር ቢሆኑም በኀይል ብቻ የሚገዙ ስብስብ እንደመሆናቸው ዕድልና ጉልበት ካገኙ ወዲያውኑ መሸፈትና የራሳቸውን ሥልጣን ማደላደል እንጂ ለከፍተኛ ባለሥልጣን መታዘዝ ለሕግ መገዛት ላገር መቆም ወደሚል ፅንሰ-አሳብ ገና አልደረሱበትም የሚለው ፈሊጥ በጣም ተጠናውቶባቸው ነበር ስለዚህም አፄ ምኒልክን ለመጣልና አገሩን ለመከፋፈል ካቀዱት በርከት ካሉ ዘዴዎች ዋና የነበረው ክርስቲያኑ እስላሙን እንዴት እንደጨቈነ ጋላው በአማራው እንዴት እንደተበዘበዘ ትግሬው በሸዋው ሥልጣኑን እንዴት እንደተቀማ ማጉላት ነበር በአምባላጌ ጦርነት ከተሸነፈ በኋላ እጁን ለጥቊር እንዳይሰጥ ነፍሴ አውጪኝ ብሎ ሲሸሽ በኋላ ኢትዮጵያውያን እያሳደዱት የገደሉት ቶሰሊ የተባለው የጦሩ መሪ መኰንን ወደዚህ ተራራ ሊሄድ የወሰነው ሰሜንንና ደቡብን የሚያገናኝ መንገድ የሚያልፈበት ያገሩ እንብርት መሆኑ ስለታወቀበት ነበር የቶሰሊ ዕቅዱና ምኞቱ እጣሊያን ተራራውን ቢቈጣጠር የትግሬና የበጌምድር ሕዝብ ዐምቆት የያዘው የአፄ ምኒልክ ጥላቻ ፈንድቶ ይነሣና ያካባቢው ባላባቶች ነፃነታቸውን ያውጃሉ ምኒልክም ሊወጋቸው ቢቃጣ የሱ ጦር መክቶ ድራሹን ያጠፋውና ኢጣልያም አገሩን በቀላሉ በእጇ ታስገባለች ብሎ ነበር እንደተጠባበቀው የአፄ ምኒልክ መንግሥትም አልወደቀም ኢትዮጵያም ነፃነቷን አልተገፈፈችም እሱ ራሱ የአካባቢው ሕዝብ በጠላትነት ያየው እጣሊያንን እንጂ አፄ ምኒልክን እንዳልሆነ ብዙም ሳይቈይ ቶሎ ብሎ ተረዳየአድዋ ጦር ባፄ ምኒልክ ባይመራ ኖሮ የአገሪቷ ዕጣ ከሌሉቹ የአፍሪቃ አገሮች ባልተለየም ነበር የሚል ጽኑ እምነት አለኝ ካፄ ምኒልክ በፊት አፄ ዮሐንስ ከሳቸውም ቀጥሎ ልጃቸው ራስ መንገሻ በየጊዜአቸው ጣሊያንን ተጋፍጠዉታል አፄ ዮሐንስ ኢጣልያንን ሲዋጉ ቀርቶ ስማቸው ብቻ ሲጠራ እንኳን የሚያበረግጓቸውና የሚያንቀጠቅጧቸው ራስ አሉላን የመሰሉ ታማኝ የጦር መኰንን ቢኖሯቸውም ልክ አስቀድመዋአቸው እንደነገሡት እንደዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ በብልሃትና ዐሪቆና አራቅቆ በማየት እንደአፄ ምኒልክ አልታደሉም የሦስቱም ጀግንነታቸውም ሆነ አገር-ወዳድነታቸው እንዲሁም ሃይማኖተኝነታቸው በፍጹም የሚያጠያይቅ አይደለም ሁለቱ የፈረንጆችን ተንኰል ዘገይተውም ቢሆን የተረዱት ቢመስሉም እንደአፄ ምኒልክ ግን በዘዴና በብልሃት ጊዜውን ጠብቆ ጠላትን መምታትን ሆነ የኢትዮጵያንም ሕዝብ በፍቅርና በብልሃት ሊያስተዳድሩና ሊመሩ ተቀናቃኞቻቸውንም ባላባቶች በወዳጅነትና በጥበብ ሊይዟቸው አልቻሉም በአድዋ ጦርነት ጊዜ ኢትዮጵያ እንደአፄ ምኒልክ መሪ በማግኘቷ በጣም ዕድለኛ ናት ያሰኛል2 በዚህ አንፃር ሲናይምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻግብሩ ዕንቊላል ነበር ይኸን ጊዜ አበሻየሚለው አነጋገር እውነትነት አለው ማለት ይቻላልአፄ ምኒልክ የኢትዮጵያን ዘመናዊ አንድነቷን ባደላደሉ በሰባት ዓመት ውስጥ ነው እንግዴህ ሕዝቡን በአስገራሚና ሊታመን በማይቻል መንገድ ተባብሮ እንዲዋጋና ድል እንዲቀዳጅ ያደረጉት ሠራዊቱ የተዋጋው ላገሩ ነፃነት ብቻ ሳይሆን በአፄ ምኒልክም ፍቅር ተነሽጦ ነበር ማለት ይቻላል ንጉሠ-ነገሥቱ ባስተላለፉት የክተት ዐዋጅያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ርዳኝ ጉልበት የሌለህ ደግሞ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን ርዳኝሲሉ ሕዝባቸው ያስተዳደራቸውን ቅንነትና ጥሩነት አይቶ ለሳቸውም ሆነ ከልብ ለሚንሰፈሰፍላቸው ነገሮች ማለትም ላገር ለሃይማኖት ለልጅና ለሚስት ፍቅር እስከጦር ሜዳ እንዲከተላቸው ሕይወቱን እስከመስጠት እንዲዋጋላቸው ነው የሚጣሩትና የሚለምኑት ያሉትእስኪ ያለፈውን በጭካኔው የታወቀውን የደርግን መንግሥት በጐን እንተወውና ሕዝብን እወክላለሁ በሕዝብ ተመርጫለሁ እያለ በየጊዜው የሚለፈልፈው ያሁኑ መንግሥት ደፍሮ ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም ሊል ይችላል ወይ ብለን እንጠይቅ በብዙዎቻችን ግምትና እምነት በፍጹም የሚታሰብ አይመስለንም ቢልም ካይነ-አውጣነትና ከትዝብት በስተቀር ሌላ ትርፍ ሊኖረው አይችልም በርግጥ በጭቈና ሥር ያለ ሕዝብ አሳቡን በነፃ ለመግለጥ ባለመታደሉ ምርጫ አጥቶ ዝም ቢልም በሚሰማው በሌላው ዓለም ዘንድ ግን ከትዝብት ውጭ የሚያተርፍ ነገር አይኖርምአፄ ምኒልክ ግን በጥበብና በፍቅር እንደሚያስተዳድሩ ሕዝቡም እንደሚወዳቸው ሌላው ቀርቶ ጠላቶቻቸው በመሆናቸው ስለሳቸው ጥሩነት አይናገሩም የሚንላቸው አውሮጳውያን እንኳን ሳይቀሩ ባድናቆትና በሙገሳ ደጋግመው ይናገራሉ ንጉሠ-ነገሥቱ ደግ ብቻ አይደሉም ብልጥም ነበሩ እሳቸውም መኳንቶቻቸውም የአድዋን ድል ሊቀዳጁ የቻሉት ፈረንጆች በተንኰልና በሽንገላ ቢመጡባቸው ተንኰልን በተንኰል ጦርነትን በጦርነት ዐጸፋውን በመመለስ ነው ከዚህ በላይ እንደተጠቀሰው የለንዶኑ ዘታይምስ ኢጣሊያኖች ንጉሡን ያሳመኑ መስሏቸው ሲታለሉ እርሱ ግን በመሣርያ እየተዘጋጀ ቈይቶ ዐጸፋውን ሰጣቸው ሲል የንጉሠ-ነገሥቱ ሥራቸው በዘዴና በዐሪቆ አሳቢነት የተመራ ነበር የሚለውን አስተያየት ያጠናክራል ጣሊያኖችም ሲጽፉ ምኒልክ ከቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ነገሥታት የሚለየው ነገር ቢኖር ሁካታ ባለበት በድል ሰዓት በተሸናፊዎቹ ላይ አይጨክንም ብቻ ሳይሆን የምሕረት እጁንም ለጠላቱ መዘርጋቱ ነው ብለው ጽፈዋል እንግዴህ ንጉሡ እንደልበ-ስፊ መሪ ተብለው የሚደነቁት በወዳጆቻቸው ዘንድ ብቻ አይደሉም በጠላቶቻቸውም ጭምር እንጂአፄ ምኒልክ ታላቅ መሪ መሆናቸው ቊልጭ ብሎ የሚታየው ከቀደሟቸው መሪያቸው ከአፄ ዮሐንስ ተግባር አንፃር ሲናያቸውም ጭምር ነው ኋላ እንደምናየው ከኢጣልያን ጋር ጦርነት ለመጀመርያ የተፋለሙት አፄ ዮሐንስ እንጂ አፄ ምኒልክ አልነበሩም ንጉሠ-ነገሥቱ ራስ አሉላ ኢጣሊያንን በዶጋሌ ወግተዋቸው ለወሬም ሳያስቀሩ በመደምሰሳቸው እንደመሸለም ፈንታ ገሠጿቸው ብቻ ሳይሆን ቈይተው ከሹመታቸውም እንዳነሧቸው ይታወቃል ጣሊያኖች ያንንእንደቀትር እሳት ቱርክን ገላመጠውጣሊያንም ወደቀ እያንቀጠቀጠውአጭዶና ከምሮ እንደጭድ አሳጣውተብሎ በተቀኘለት ጀግና ላይ አፄው ይኸን በማድረጋቸው ደስታውን አልቻሉትም ተሽቀዳድመው ኻያ ሺ ጦር በመላክ ሰሓቲን ቢይዙና የማይደፈር ምሽግ ሠርተው ቁጭ ቢሉ አፄ ዮሐንስ የአፄ ምኒልክን በሁለት ዕጥፍ ያህል የሚበልጥ ወደሁለት መቶ ሺ ሠራዊት ይዘው ሊዋጉ ብቅ አሉ በለሳቸው ቀንቶ ደግሞ ክደዋቸው ለኢጣልያን አድረው የነበሩ የኢጣሊያንም ታማኝ ባለሟል በመሆናቸው ምሥጢራቸውን ብቻ ሳይሆን ዐቅማቸውንና ዕቅዳቸውን ሁሉ የሚያዉቁ ደጃዝማች ደብብ የተባሉ ዘመዳቸውም በደምብ ከታጠቀ ሠራዊታቸው ጋር ሁነው ሊረዷቸው ገቡላቸው3 አፄ ዮሐንስ ይኸንን ሁሉ ዕድል አግኝተው ኢጣሊያንን ወደምፅዋ ተመልሳችሁ ሂዱ እያሉ ሁለት ደብዳቤዎች ከመጻፍና ለሁለት ወር ያህል ከማፋጠጥ ውጭ ሌላ ምንም የረባ ነገር ሳይሠሩ ተመለሱ ያውም የሆነው እንደአፄ ምኒልክ በረጅም መንገድና ጒዞ ሳይወጠሩ የስንቅና የቀለብ ችግር እምብዛም በማያሳስባቸው በገዛ ግዛታቸውና ቤታቸው ውስጥ ነበር ማለት ይቻላልአፄ ምኒልክ በብልህ መሪነታቸው በአድዋ ለኢትዮጵያ ድል ቢያጐናፅፏትም የተዋጋውና ለድሉ ያበቃው ግን በአዲስ መልክ ያቋቋሙት የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው ድሉም የሕዝቡ የአንድነቱ መግለጫ የማንነቱ ማረጋገጫ ሆነ ሠራዊቱ በጣም ሩቅ ከሆነው አገር ጀምሮ ከተለያየ ኅብረተ-ሰብ ከያንዳንዱ መንደር የተወጣጣ ጦር ነበር በዚህ የመጀመርያው የአንድነቱና የአገሩ ነፃነትና ልዕልና ፈታኝ ጦርነት ያልተሳተፈ አልነበረም ማለት ይቻላል ጐጥና ጐሣ ቋንቋና ሃይማኖት ጨዋና ባለጌ ዕድሜና ፆታ ሳይለይ ወንድና ሴት ልጅና ሽማግሌ ተራና መኰንን ባለዳባና ባለካባ እስላምና ክርስቲያን ሳይባል ከስሜኑና ደቡቡ ከምሥራቁና ምዕራቡ ከመስዑና አዜቡ ከባሕሩና ሊባው ሁሉም ከየመጣበት ቀዬው በኢትዮጵያዊነቱ በአገር ልጅነቱ ብቻ ቁሞ ደረቱን ለጦር እግሩን ለጠጠር በመስጠት በዠግንነት ተዋግቶ አጥንቱን በመከስከስ ደሙን በማፍሰስ ኅብረቱንና አንድነቱን ወንድማማችነቱና ቤተሰብነቱን ያጸደቀበት ድል ነው4 ሕዝቡ ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ በተወለደችበት ማግስት አንድነቱን በደሙ ጥምቀት አጥብቆታል ማለት ይቻላል ለሚወዱት አገርና ሕዝብ የራስን ሕይወት አሳልፎ ከመስጠት የበለጠ ነገር የለም ብቻ ሳይሆን መተግበርም አይቻልምመርሳት የማይገባን ነገር ቢኖር አድዋ መደምደሚያው ይሁን እንጂ ኢትዮጵያውያን ኢጣልያንን ድል ያደረጉት አንዴና ሁለቴ ብቻ ሳይሆን አከታትለው በሦስት በተለያዩ ጦርነቶች ነው መጀመርያ በአምባ አላጌ ሁኖ የሰሜኑን ሕዝብና ባላባቶቻቸውን ካፄ ምኒልክ ጭቈና አገላግላለሁ ብሎ ሊያሳምፅ ተራራውን ይዞ የነበረውን የሕልመኛውን የቶሴሊን ጦር ደምስሰው ብትንትኑን አወጡ ጨቋኙ ጣሊያን እንጂ ምኒልክ እንዳልሆነ ሊያስተምሩት ደግሞ እርሱን ራሱን ነፍሴ አውጭኝ ብሎ ሲሸሽ አሳድደውት ይዘዉት ገደሉት ይኸ ድል የኢትዮጵያዉያኖችን መንፈስ አጠናከረ ወኔአቸውን ይበልጥ ቀሰቀሰ ያ ራስ መንገሻን አከታትሎ ሦስቴ በኰዓቲት በሰንዓፈና በደብረ-ሐይላ በማሸነፉ ምክንያት ኢትዮጵያን በሙሉ ባንዴ እመዳፌ ውስጥ አስገባታለሁ ያለው እብሪተኛ መኰንንንና ጦሩን ኢምንት በማድረጋቸው ታላቅ ኩራትና በራስ መተማመን ተሰማቸውኢጣሊያኖች ግን ከዚህ ድል ጠቃሚ ትምህርት እንደመማር የአዙሮ ማየት እንገት አጥተው ልባቸውን አደንድነው ለሁለተኛው ዙር ጦርነት ተዘጋጁ የአምባላጌ ዐይነት ውድቀት እንዳይገጥመን ብለው በጥቂት ጊዜ ውስጥ የማይደፈር ጠንካራ እርድ በመቀሌ ሠርተው ጠበቁ በምንም መልክ የማይሸነፉ መሰላቸውና ከፍተኛ እብሪት ተሰማቸው በምሽጉ መግቢያ ዙርያውን የጠርሙስ ስብርባሪ ተነሰንሶበታል ከዚያም በማከታተል ወፍ እንኳን የማያሳልፉ ሹል ዕንጨቶችና ድቡልቡል የእሾኽ ሽቦ አጥር ተተክለውበታል ቀጥሎ ደግሞ የሦስት ሜትር ስፋት ያለው ካብ ተገንብቶበታል የኢትዮጵያ ጦር የሚዋጋ አለጫማ በሌጣ እግሩ ቢሆንምጋሻውን እያነጠፈ የጠርሙሱን ስብርባሪ ዐለፈ ግን ወደዕንጨቶቹና ወደእሾኻማ የሽቦ አጥሩ ሲደርስ አብዛኛው በነዚሁ እየተዘነጠለ ከነሱም ያመለጠው የኢጣሊያን መትረየስ እየተርከፈከፈበት እንደወፍ ሬሳ በሹል ዕንጨትና ያን አልፎት የሄደ ደግሞ በድቡልቡሉ የእሾህ ሽቦ እየተንጠለጠለ ቀረ የመቀሌ ምሽግ በሰው ብዛት በወንዶች ጀግንነት ባገር ወኔ በመሣርያ ጥቃት የማይፈታ ሁኖ ተገኘ የኢትዮጵያን ጦር እየለቃቀመ በጭካኔ በላው ወሽመጥ ቈራጭ ወኔ አቅላጭ ሆነ ባለቀው ጀግና ብዛት በሐዘን ተውጠው የነበሩት የኢትዮጵያ ፀሐይ በመባል የሚታወቁት እቴጌ ጣይቱ የወንዶቹን ጀግንነት በሴቶች ብልሃት ባይተኩ ኖሮ ወደአድዋ መጓዙ ሕልም ሆኖ ሊቀርም በቻለ ይሁንና እሳቸው ለሞተ ተዝካሩን ለማዉጣት ልጁን ለማሳደግ ለቀረ ደግሞ ለመሸለም ቃል ገብተው ኢጣልያኖች ለውሃቸው የሚጠቀሙትን ምንጭ ካስያዙ በኋላ ነው ኢትዮጵያኖች ከከፋ ዕልቂትና ከመንፈስ ውድቀት ድነው ወደአድዋ የተጓዙትእቴጌም ለውሃ ጠባቂዎቹጠጅ በብዙ ቀንድ እየተሞላ በማለፊያ ወጥ እንጀራ እየተፈተፈተ በመሶብ ሁኖ ፍሪዳው ታርዶ ሥጋው በእንቅብ እየሆነ ከሌሊቱ በዘጠኝ ሰዓት ይሰዱላቸው ነበር ትጥቃቸውን ሳይፈቱ እንቅልፍ ሳይትኙ ለአንድ ቀን የሚያስመርረውን ጦርነት ዐሥራ-ዐምስት ቀን ሙሉ ሌትና ቀን እየተዋጉ ውሃውን ከልክለው በጭንቅ ኢጣሊያኑን ከዕርዱ እንዲወጣ አደረጉትኢጣሊያኖቹ ከውሃ ጋር ሲጨነቁ ራስ መኰንን ዕድሉን ተጠቅመው ሽቦውን ቈረጡ ከራስ አሉላም ጋር ከካቡ ሁነው ሠራዊታቸውን ቈሉት ያ የተማመኑበት ምሽግ ዋጋ-ቢስ ሆነና እጅ ከመስጠት ሌላ ምርጫ እንደሌላቸው ሲረዱ ሁሉም ተማረኩ እንዴህ ሁኖ በሴቶቹ ጥበብ የተጠናቀቀው የመቀሌ ድል ወደአድዋው መራመምህር አፈ ወርቅ ገብረ ኢየሱስ የአድዋ ድል ምን ያህል የአዲሲቷ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያንድነትና የትብብር ውጤት መሆኑን በሰላ ብዕራቸው ሲገልጡየሸዋ5 ፈረስኛ የጐጃም እግረኛየትግሬ ነፍጠኛ የአማራው ስልተኛ ...ከእንዝርት የቀለለ የጁዬተነብር የፈጠነ በጌምድሬተቋንጣ የደረቀ ትግሬከአሞራ የረበበ ደቡቤከንብ የባሰ ጐጃሜእያባረረ በየጐዳናው ዘለሰው በማለት የያንዳንዱን አካባቢ ሕዝብ ጀብዱነቱንና ጀግንነቱን ንጥር ምጥን አድርገው በጊዜው ቋንቋ ለታሪክ አስፍረውታል1 እንዲያው ለፈገግታ ያህል ላውጋችሁ በነጮች ትምህርት ቤት አስተምር በነበርሁበት ወቅት አንዳንድ በፈተናው ባገኘው ነጥብ የተቈጣው ተማሪ በጽሑፍ ግምገማው ወቅት ቁጭቱን ሲወጣ ይኸ ህንዳዊ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች አንጉል የሚያኦሩ ናቸው ... ይኸንን ዐይነቱን ደደብ ህንድ ለምን ትቀጥራላችሁ በአሜሪቃ ምድረ-ሰማይ ከሱ የተሻለ አስተማሪ ታጣ እንዴ ሲል ተማሪው በአነጋገሩ የሚገልጥልኝ የሰብእናዬ ቅርጽ ዝምድናዬን ከዐረብ ይበልጥ ለህንድ እንደሚያቀርበኝ ይታየው እንደነበር ነው2 . ማስረጃ ካስፈለገ ሩቅ መሄድ አያስፈልገንም እንዲያው ለምሳሌ ያህል ብቻ ልጥቀስ ያፄ ቴዎድሮስ ጨካኝነታቸው ያደባባይ ወሬ ስለሆነ መዘርዘር አያስፈልገውም በአፄ ምኒልክ ዘንድ ግን የተዋጓቸውን ባላንጦቻቸውን ስመውና አቅፈው ሲያበቃ ወደጥንቱ ሹመታቸው ማዕርግና ቦታ መመለስ የተለመደ ሲሆን አፄ ዮሐንስ እንደዚህ ዐይነት ተግባር በመሥራት እምብዛም አይታወቁም ሌላው ቢቀር ርኅሩኅና የእኅታቸው ባል የነበሩትን ባላንጣቸውን አፄ ተክለ-ጊዮርጊስን ከማረኳቸው በኋላ እንኳን እንደመማር ዐይናቸውን በጭካኔ አሳውረው በተራራ አስረውዋቸው ነው የሞቱት3 . ደጃች ደበብ ለአፄ ዮሐንስ የገቡላቸው ኢጣልያን እንደሚሸነፍ ርግጠኛ ስለነበሩ ነበር ይባላል4 አንድ መድፈኛ የኢጣሊያን ጋዜጠኛ በማጋነን መልክም ቢሆን የሕዝቡን ኅብረትና ትብብር ሲገልጥ ሕዝቡ ከሁሉም ብሔረሰብ የተወጣጣ ነው ይዋጋ የነበረው ፈረሱም በቅሎውም አህያውም ባንድነት ከሰው ጋር ሁኖ ነው በጦርነት የገጠመን መደበኛ ወታደር አልነበረም ሴቶች ሽማግሌዎች ቄሶችና ቈማጣዎችም ሳይቀሩ ይዋጉን ነበር ይላል5 . ሸዋ ያኔ የሚያመልክተው የአሁኑን በስሙ የሚጠራውን ጠቅላይ አስተዳደር ብቻ ሳይሆን ከደቡቡ ከምሥራቁና ከምዕራቡ ያለውን አፄ ምኒልክ ንጉሥ በነበሩበት ጊዜ ያስተዳድሩ የነበረውን የመኻሉን አገር በሙሉ ነው በጦርነቱ ጊዜ ኢጣልያን ያዋክቡ የነበሩትና ውሃ የሚመጣባቸውን ምንጮቻቸውን በሙሉ ይዘው የነበሩት የ ኦሮሞ ፈረሰኞች ነበሩየበርሊን ጉባኤበቅርቡ ጊዜ የአድዋን ጦርነትንም ሆነ አፄ ምኒልክን አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በሰጣቸው በጐሣ ክፍፍል በፖሊትካው ቅርጽና ዐይን የሚያዩና የሚተረጒሙ እንዳሸን እየተፈለፈሉ መጥተዋል አብዛኞቹ ግን የገዢው መንግሥት ባለሥልጣኖች ከተወለዱበት አካባቢ የሚመጡና ከነሱም ጋር በሥጋ ወይንም በትግል የተሳሰሩ የትግርኛ ቋንቋ ከሚናገሩ ሰዎች መካከል የወጡ ናቸው ቢባል እውነተኝነት አለው ማለት ይቻላል እያንዳንዳቸው የሚሉትን ለመናገርና ለመተቸት ፍሬም ጥቅምም የለውም እንዲሁምየሁላቸውን ስምና ሥራ መጥቀሱ ዋጋ-ብስ ብቻ ሳይሆን ፍላጎቱም የለኝም ቦታም አይበቃም ለግንዛቤ ያህል ሁለት ብቻ ላነሣ እወዳለሁ በመጀመርያ ደረጃ እምቢታ አንፃር ወረርቲ ታሪኽ ሃፀይ ዮሃንስ 4ይ ንጉሠ ነገሥቲ ዘኢትዮጵያ ባለሰፋፊ ገጾች መጽሐፍ ነው ጸሐፊው የአያሌ የትግርኛ መጻሕፍት ደራሲ ነው በመባል የሚታወቀው መምህር ገብረ-ኪዳን ደስታ ነው መምህር ገብረ-ኪዳን በግእዝና በቤተ-ክርስቲያን ትምህርት ተኰትኲቶ በማደጉ የመጻፍ ችሎታውን እንዲያዳብር የረዳው ይመስላል ካልተሳሳትክሁ የመምህርነት ቅጽልም ያገኘው ከዚያው ከቤተክርስቲያን ትምህርት ሙያ ጋር በተያያዘ ዕውቀቱ ነው ብዬ እገምታለሁ ደራሲው ወያኔ ገና እጫካ እያለ አድሮለት በመጠኑ ካገለገለ በኋላ ከድቶ ወደደርግ መንግሥት ገባ እሱም በሽፍቶቹ አውራጃ እያዞረው ለስብከቱ ሊጠቀመው ቢሞክር ምንም ፋይዳ እንደማያመጣና ጉዱን የሚያውቀው ያገሩ ሕዝብ ደግሞ የውስጥ ስለላ ሊያካሂድ እንጂ በዉኑ አምኖ አልገባም የሚል ወሬ ቢያናፍስ አገለለው ተብሎ ይወራል መጽሐፉ ለደራሲው ያልተጠበቀ ዝና በተለይም የመንደሩ ተወላጆች ከሆኑት ባለሥልጣኖች ዘንድ ዕውቅናና ክብር-ቢጤ ስለሰጠው በየመገናኛውና ባንዳንድ የኢትዮጵያውያን ስብሰባዎች ተጋብዞ ሲደሰኩር ታይቷል ሰፋ ያለ አንባቢና ገቢ እንዲያገኝለት መጽሐፉን ወደብሔራዊ ቋንቋ እያስተረጐመም ነው ይባላልሌላው መጽሐፍ ፍኖተ ገድል ከ1967-19771 በሚል ርእስ በአቶ ብሥራት አማረ የተደረሰ ነው አቶ ብሥራት እንደብዙዎቹ የወያኔ ተከታዮችና ታጋዮች የዐሥራ-ሁለተኛ ክፍል ፈተናውን እንደወደቀ ወደጫካ እንዳመራ ይነገራል ከዚያም በስለላና አፈና ክፍል ሲሠራ ቈይቶ ድርጅቱ በአፄ ምኒልክ ቤተ-መንግሥት ሲገባ እሱም በአዲስ አበባ ከተማ ተቀጥሮ በነበረበት መስክ እንደቀጠለ ይነገራል ከዚያም በሙስና ተከሶ ወደአሜሪቃ አመለጠ እዚያ በፖሊትካ ጥገኝነት ሲኖር ቈይቶ ባንድ ስሙ ካልታወቀ የአሜሪቃ ዩኒቬርሲቲ እያስተማረ እያለ ከላይ የተጠቀሰውን መጽሐፍ ጽፎ ሊያስታውቀው ሲል ተመልሶ አዲስ አበባ ሲገባ ባለሥልጣኖቹ ገመናውን ሁሉ ረስተው የተቀበሉት በታላቅ ክብርና ሆሆታ ነበር ይባላል2በግልጥ እንደሚታየው እነዚህና እነሱን የመሳሰሉ ጸሓፊዎች በሕይወታቸው እንደየጊዜውና ሁናቴው ጐራቸውን እየለወጡ በመንሳፈፍ ከመሄድ ውጭ አቋምም ሆነ ታሪክ-ነክ መጽሐፍም ለመጻፍ ተገቢው ትምህርትና ሥልጠና ዕውቀቱም ጭምር የሌላቸው መሆናቸው ግልጽ ነው በመጻሕፍታቸው መግቢያ ላይ ግባቸው የተጣመመውን የጥንት ታሪክ ማቃናት የተዛባውን ማስተካከል እውነታውን መመዝገብ ነው ማጣመምም ሆነ ማዛባት መወገዝ የሚገባቸው ተግባራት ናቸው ብለው በመናዘዝ ያስተጋባሉ ግን ሥራቸውን ላነበበ እነሱ ራሳቸው የተካኑት እውነትን በማዛነፍና በማቆላመም ስለሆነ የቤተ ክርስቲያን ደወል ይመስል ድምፃቸውን ከማክለልና ከማናር የማያልፉ ፍሬ-ቢሶችና ግብዞች ሰባኪዎች ናቸው ማለቱ አይከፋም ባነሡት በያንዳንዱ ነጥብ ላይ ኂስ እያወጡ መሄድ ተገቢ መስሎ ሊታይ ይችላል ለእንደኔው ግን ጊዜ ማጥፋት እንጂ ሌላ ጥቅም የለውም ሁኖም አንድ እየተመላለሱ የሚነበንቡት ነገር ቢኖር አማርኛ ተናጋሪውን ሕዝብ ማለትም ኢትዮጵያውያንን ማጥላላት አፄ ምኒልክን ማንቋሸሽ በተቃራኒው በዚያው ልክ ደግሞ ከአማራው ጋር በደም በጋብቻ በባህልና ታሪክ በጥብቅ እንዳልተሳሰሩ ይመስል የሰሜኑን በተለይም ደግሞ የትግራይ ትግርኛ ተናጋሪውን ታሪክና ትግል ማጋነን አፄ ዮሐንስንም ማሞገስ እንደሆነ ማሳሰቡ ተገቢ ይመስላልደራሲዎቹ አዲስ መረጃ አገኘን ብለው የሚያመጡት ርግጠኛ ነኝ ብዙዎቻችን ደጋግመን ያነበብነው ስለሆነን አዲስነቱ ከምኑ ላይ እንደሆነ ማወቁ ግር ሳይለን እንደማይቀር እገምታለሁ በጠቅላላ ጥናታቸውና ምርምራቸው ጥርት አድርጎ የሚያሳየው አዲስ ነው የሚሉትን መረጃዎች የታሪክ ትምህርትና አላፊነት እንደሚጠይቀው ሁሉ አበጣጥሮ የማየት ከጊዜውና ከአካባቢው አስተሳሰብና አሠራር አገናዝቦና አመዛዝኖ የማተትና የመተንተን ችሎታቸው የመከነ እንጂ የሰከነ አለመሆኑን ነው መጻሕፍቱ ለፖሊቲካ ወረት ሲባል የተጻፈ የተረትነት እንጂ የታሪክነት ባሕርይና ይዘት ስለሌላቸው ዕውቀትን በማገበየት ደረጃ ዋጋ-ቢስ ናቸው ማለት ተገቢ ፍርድ ይመስለኛል እንደዚህ ዐይነቱን አርቲ-ቡርቲ ርግጠኛ ነኝ ጸሓፊዎቹ የቀሰሙት በትምህርት ገበታ ላይ ሳይሆን በመሸታ ቤትና በጫካ የትግል ሜዳ ውስጥም ነው ብሎ ማመኑ ይሻላል ጽሑፋቸውን ሳነብ አንድ ትዝ ያሰኘኝ ነገር ቢኖር ግን ገና ተማሪ ሳለሁ ያነ በሳቅና በፌዝ ያነበብሁትን ትግሊ ኤርቲራ ካበይ ናበይ በሚል አርእስት ታጋዮቹ አፋቸውን በማሞጥሞጥ ቊንጮ መምህራችን ናቸው በሚሏቸው በአቶ መለስ ዜናዊ የተደረሰውን መጽሐፍ ነበር ልክ እንደዚሁ መጽሐፍ ደራሲዎቹ ከዚህም ከዚያም በቀነጫጨቡትና በዘነጣጠሉት የመረጃ ስብስብ በመደገፍ ፍሬከርሥኪን እየወሸከቱ እንደእውነት ለማቅረብ ይሞክራሉ ተረታቸው ራሳቸውን የሳቱትንና የአድርባዮችን የማወቅ ፍላጉት ሊያረካ ይችላል ከዚያም አልፎ ደግሞ በየቻሉበት ቦታ በድኻው ሕዝብ ገንዘብ ድግሪያቸውን በችርቻሮ ያገኙትን የቀጣሪዎቻቸውን ስሜት ሊያፈነድቅ የጀሌዎቻቸውን ቀልብ ሊስብ ለደራሲዎቻቸው ደግሞ ከልብ የሚጐመጁትን ዕውቅናና መጠነኛ የኪስ ገቢ ለጊዜውም ቢሆን ሊያስገኝላቸው ይችል ይሆናል በታሪክና ባገር አንፃር ሲታይ ግን ከትዝብትና ውርደት በስተቀር ሌላ ርባን ያላቸው አይመስለኝም ጸሓፊዎቹ ቢዋሹም ታሪክ ግን አይዋሽምእንደመሰለኝ አብዛኛው ሕዝብ መሃይምን በሆነበት አገር በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት ያስተሳስብ ትልም ለመከተል ተረትንና ታሪክን ማደበላለቅ እንደዘመናዊነት እየታየ ነው ታዲያ ሰው ቢታጣ ተመለመለ ጐባጣ ነውና ነገሩ የዕውቀት ብቃታቸውን በግዢ እንጂ ከትምህርት ገበታ ተሰማርተው ባልገበዩት ባስተያየታቸው ድንብርብር በመንፈሳቸው ሳባራ በሆኑ የመንግሥት ባለሥልጣኖች ዘንድ እንደነዚህ አሳባቸውን በጽሑፍ አስፍረው መቀባጠር የሚችሉት የለየላቸው ጭንጩ ምሁራን ሁነው መታየታቸው አይቀርም አለበለዚያማ መጻሕፍታቸውን በሆታና በእልልታ መቀበሉ ለምን አስፈለገይኸንን እንደመቅድም ካሳረግሁ ወዲያ እንግዴህ ደራሲዎቹ ያወላገዱትን ለማቃናት ያዛነፉትን ለማስተካከል ስለአድዋም ሆነ ስለአፄ ምኒልክ የሚሉትን እንስማቸውበነዚህ አፈ-ቀላጤዎቹ ደራሲዎች አነጋገር የአድዋ ጦርነት የተካሄደው በኢትዮጵያና በኢጣሊያን መንግሥት መካከል መሆኑ ቀርቶ በነፃው በትግራይ መንግሥትና በኤርትራው የኢጣሊያን መንግሥት መካከል ነው የጠቡም መነሾው የኤርትራው የኢጣሊያን መንግሥት ትግርኛ ተናጋሪውን ሕዝብ በሙሉ አንድ አድርጎ ሊገዛ በመመኘት ትግራይን ሊይዝ ስለፈለገ እንጂ ከልዑላዊው የትግራይ መንግሥት አልፎ የመሄድ አሳብም ፍላጎትም አልነበረውም ጦርነቱ በስሕተት ከኢትዮጵያ ጋር ሊያያዝ የበቃው ደግሞ የትግራይ ገዢ በኢጣሊያን እንደተሸነፈ ከጐረቤት መንግሥት ርዳታ ቢጠይቅ ምኒልክና የሸዋ ጦር በመምጣቱ ነው ረዳቱ የምኒልክና የሸዋ ሠራዊት ከእሪ ባዩ የትግራይ መንግሥት ጋር ጐን ለጉን በመዋጋት ድል ነሥቶ ኢጣሊያንን ካሸነፈ በኋላ ወደመጣበት ወደሸዋ ሰተት ብሎ ተመለሰ እንጂ አልቈየም ስለዚህም ድሉ መከበር ያለበት በትግራይና በአድዋ እንጂ በኢትዮጵያ አይደለም ባዮች ናቸውእኔ እንደማውቀው ትግራይ ከኢትዮጵያ እናቷ ተለይታ ራሷን የቻለች ነፃና ልዑላዊት መንግሥት ሁና ራሷን ያስተዳደረችበት ወቅት በታሪክ የለም ታይቶም አይታወቅም3 እስከአፄ ዮሐንስ ዐራተኛው ዘመን ድረስ መናገሻ ከተማቸው በደቡብ አካባቢ በነበረበት ጊዜ እንኳ ነገሥታቱ አገር አቋርጠው የንግሥናቸውን ሥርዐት ሊያካሂዱ ወደአክሱም ይጓዙ የነበረው ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ቢትሆንና ጥንታዊነቷም ቢታወቅ ከሌላውም የአገሪቷ ክፍሎች ይበልጥ ቢትከበር እንጂ ነፃና ልዑል አገር በመሆኗ አይደለም ምናልባት የጸሓፊዎቹ ስሕተት የኢትዮጵያን ያስተዳደር ታሪክና ሥርዐት ካለማወቅ የመነጨ ይሆናል ብለን መገመቱ የሚበጅ ይመስላል ስሕተቱ ይኸ ከሆነ ደግሞ ለማረም ያህል መታወቅ ያለበት ነገር አለ ይኸውም በጊዜው ያገሩ የአስተዳደር ሥርዐት መሠረት አካባቢውን ከውስጥም ሆነ ከውጭ ጠላት መከላከልም መጠበቅም ሆነ ሕዝቡን በፍትሕና በርትዕ ማስተዳደርን ጭምር ያካባቢው ገዢ ማለትም የባላባቱ አላፊነትና ግዴታ ነበር ንጉሠ ነገሥቱ ጣልቃ የሚገባውና ካስፈለገም ባላባቱን ከሥልጣኑ የሚሸረው እነዚህን ግዴታዎች ሳያሟላ ሲቀር ብቻ ነው ማለት ይቻላል ጠላት ወርሮ ካሸነፈ ወይንም ሕዝቡ በባላባቱ ተበደልሁ ተገፋሁ ካለ አገሩንና ሕዝቡን ማረጋጋቱ የንጉሠ-ነገሥቱ ፈንታ ነበር ያነ የትግራይ ባላባት ማለትም ገዢ በነበሩት በራስ መንገሻ ላይም የደረሰውና የአድዋም ጦርነትና የጦርነቱ ማግስት ሁናቴ የሚያስረዳው ይኸንኑ ነው ኢጣልያን እየተንሰራራ እስከግዛታቸው በመምጣት ራስ መንገሻን ባንድ ዓመት ውስጥ ሦስቴ ቢያሽንፋቸው ኢጣልያን ማርኳቸው ወስዶ ንጉሠ-ነገሥቱንም ሆነ አገሩን እታላቅ ውርደትና ትዝብት ላይ እንዳይጥል በሚል ሥጋት አፄ ምኒልክ ተወጥረው እንደነበር ይታወቃል ከዚህም የተነሣ እኔ እስከሚደርስ ድረስ እንዳትዋጋ ብለው በጽኑ ቢያዟቸው ራሱ እንደተነገራቸው አደረጉ ንጉሠ-ነገሥቱ እንደደረሱም ራሱ ከሠራዊታቸው ጋር አብረው ጐን ለጐን ተሰልፈው በዠግንነት በመዋጋት ኢትዮጵያን ለድል አበቁ ግን ብዙም ሳይቈዩ በንጉሠ-ነገሥቱ ላይ ቢሸፍቱና በአማላጅም በቀጥታም ተለምነው እምቢ አልታዘዝላቸው ቢሉ ጦር ተልኮባቸው ተሸንፈው ከሥልጣናቸው ተሸረው በግዞት ሞቱ ደጋግመን በኢትዮጲያ ታሪክ የምናየው ባላባቶቹ በተቻላቸው መጠን እርስበርስ በንጉሠ-ነገሥቱ ላይ በማሻጠርም ሆነ ካስፈለገ ከውጭ ጠላትም ጋር እንኳን በማበር ለሥልጣን መሻኰት የተለመደ ነው አፄ ዮሐንስ በአፄ ቴዎድሮስ ላይ ሸፍተው ለውድቀታቸው ከእንግሊዞች ጋር እንደተባበሩ ሁሉ አፄ ምኒልክም አልሆነላቸውም እንጂ ልክ እንደዚያው ከኢጣሊያኖች ጋር በመመሳጠር አፄ ዮሐንስን ሊጐዱም ሊጥሉም ሞካክረዋል ይኸ በንጉሠ ነገሥቱና በመኳንንቶቹ መካከል የነበረው የሥልጣን ሽኩቻ የሚገዙትን አገር ነፃና ልዑላዊ አያደርገውም ጉልበት እስካለው ድረስ ንጉሠ-ነገሥቱ ገዢዎቹን መቼም ቢሆን ሊሽራቸውና ግዛታቸውን ለሌላ ሊሰጥ ይችላልጸሓፊዎቹ በአፄ ምኒልክም ላይ የተለያዩ ከባድ ወቀሳዎችን ይሰነዝራሉ ባነጋገራቸው ኢትዮጵያን በቄሳራውያን ዘመን ያጋጠሟትን ችግሮች አብዛኛውን በቀጥታም በአዙሪትም በንጉሠ-ነገሥቱ ደጃፍ ላይ የሚጥሉ ይመስላል ክሶቹ ብዙዎች ቢሆኑም እንዲያው ለናሙና ያህል ከአድዋ ድል ጋር የተያያዘውን ጥቂቱን ላብራራ በደራሲዎቹ አስተያየት አፄ ምኒልክ የማይረካ የሥልጣን ጥም ያላቸው ሰው ነበሩ ሥልጣንም ለመያዝ ሲሉ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር ሲያሻጥሩ ቈይተው በመጨረሻ የዉጫሌ ውል ከኢጣልያን ጋር ተዋዋሉ የዚህ ስምምነት ውጤት ደግሞ ኢትዮጵያን ወደብ-አልባ አድርጎ አስቀራት ብቻ ሳይሆን ኤርትራን ማለትም የባሕረ-ነጋሽ ግዛት በመባል የሚታወቀውን ምድሪ ባሕሪን ለጠላት መሸጥ ሆነ ከዚህም የተነሣ እስከአፄ ዮሐንስ ሞት ድረስ አንድ የነበረውን የትግራይን ትግርኛ ተናጋሪ ኅብረተ-ሰብንም በሁለት ከፋፈሉት የሚል ነውታሪክና ልምድ የብዙዎቻችንም ትዝብት እንደሚነግረን ሥልጣን መቋመጥን በተመለክተ ዝንባሌው በሁሉም ሰው ዘንድ ያለ ስለሆነ ክሱ አገባቢነት የለውም ማለት ይቻላል እስከ አፄ ምኒልክ ጊዜ ድረስ የነበረ አስተሳሰብም ሆነ ሥርዐት ንጉሥ የሚመረጠው በእግዚአብሔር እንጂ በሰው አይደለም ይል ስለነበር ያኔ በኢትዮጵያ ምድር ከመኳንንቱና ከመሳፍንቱ የሚወለድ ይቅርና ያንዲት ዕለት ቀለብ እንኳን የሌለው ቡትቶ ለባሽ ድሃም ቢሆን ሕልሙ አንድ ቀን የእግዜር ፈቃዱ ሁኖ እሱም የንጉሥነት በትር እጨብጥ እሆናሉ ብሎ አያስብም አይባልም በተባበሩት የአሜሪቃ መንግሥታት አገር ያለነውም የምናየው ዕድሉ ሁኖለት ያገሩ ፕሬዚደንት ለመሆን የማይቋምጥ አሜሪቃዊ የለም ማለት የሚቻል አይመስለኝም አፄዎቹ ቴዎድሮስም ሆኑ ዮሐንስ የንጉሥነትን በትር የጨበጡት ካባቶቻችው ወርሰው ወይንም በሕዝቡ ተመርጠው ሳይሆን በጉልበታቸው እንደነበር ክርክር የማያስፈልግ ሐቅ ነው አፄ ምኒልክም ከንጉሣዊ ቤተሰብ በመወለዳቸው ከቀደሟቸው ሁለቱ ነገሥታት ማለትም ካፄዎቹ ቴዎድሮስና ዮሐንስ ይበልጥ የንጉሥነት አልጋ ይገባኛልነት አላቸው ቢባልም የጨበጡት ግን እንደነሱ በሞት ሽረት ፍልሚያ ነው ጉልበትም ብልሃትም ተጠቅመዉበታል ለነገሥታቱ ከዙፋኑ ላይ እንዴት ወጡ የሚለው ጥያቄ ጉዳያቸው አይመስልም አገባብ ያለው ጥያቄና ዋና ጭንቀታቸው ማነጣጠር ያለበት ከነገሡ በኋላ ምን ሠሩ ላይ በሚለው ነው ለነሱ ንጉሥነት መሣርያ እንጂ የዓላማቸው ፍጻሜ አልነበረም ለመረጣቸው ፈጣሪያቸው ተልዕኮውን ማለትም ግዳጃቸውን ለመፈጸም የሚጠቀሙበት መሣርያ በዚህ ዐይነት አስተሳሰብ ተመሥርተው ነው እንግዴህ አፄ ቴዎድሮስ ንጉሥነታቸውን የጨለማና የድብልቅልቅ ጊዜ በመባል የታወቀውን ዘመነ-መሳፍንትን አክትመው የአዲስቷን ኢትዮጵያ መሠረት ሊጥሉ ሲጠቀሙበት አፄ ዮሐንስ ደግሞ ለግንባታው ሊያዉሉ ሞከሩት ሁኖም ሁለቱም እንደፈለጉት አልሆነላቸውም አፄ ቴዎድሮስ ያስተዳደር ብልሃትና አደብ አንሷቸው በመጨረሻ ማጋነን አይሆንብኝና አንዲት እፍኝ እንኳን የማትሞላ አካባቢ ብቻ ንጉሠ-ነገሥት ሁነው በተግባራቸው ከውጭ እያስጐተቱ ባስመጡት በእንግሊዝ ጠላታቸው ወረራ ሰበብ በተስፋ-ቅብጸት ራሳቸውን ሲገድሉ አፄ ዮሐንስ ደግሞ ለንግሥ ላበቃቸውው ለቄሳራዊው ለእንግሊዝ መንግሥት ውለታ ሊመልሱ ሲሉ ባፈሩት ደርቡሾች ጠላቶቻቸው እጅ ሕይወታቸው ዐለፈችየትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪ መከፋፈልን በተመለከተ ግን ተጠያቂው አፄ ዮሐንስና የሰሜኑ አገሮች ተከታዮቻቸውና መኳንቶቻቸው ድርጊቶች እንጂ አፄ ቴዎድሮስም አፄ ምኒልክም አልነበሩም እውነት ነውበአገር-ወዳድነትና በጀግንነት ካስፈለገም በሃይማኖተኝነት አፄ ዮሐንስ በምንም መልክ አይታሙም የሞቱት ላገራቸውና ለሃይማኖታቸው ሲሉ ሰማዕት ሁነው ቢባል ሐቅነቱ አይካድም ላገር መሪነት ግን ብቁ አልነበሩም ብቻ ሳይሆን ጊዜውና አካባቢው ከሚጠብቀው ግዳጅ ጋር የሚመጣጠን ዕውቀቱም ችሎታውም ብስለቱም አልነበራቸውም ማለት ይቻላል እኚህ ንጉሠ-ነገሥት የሚታወቁት በአክራሪነታቸው ቢሆንም ሥራቸውንም ሆነ አስተያየታቸውን ጠባብነትና ገራገርነት ያጠቋቸው ነበሩ ማለቱ የሚቀል ይመሰለኛል ይኸም ሐቅ እንጂ የራሴ ፈጠራ እንዳልሆነ አንዳንድ ጸሓፊዎችም ሆኑ በተከታታይ የሠሩት ሥራቸው ይመሰክራሉ አፄ ዮሐንስን በቅርቡ ያውቃቸው የነበረው እንግሊዛዊው አውጉስቱስ ብላንዲ ዋይልድ ለምሳሌ አፄ ምኒልክ በጣም የሚደነቅ ራዕይ ብቻ ሳይሆን ዐርቆና ሰፋ-አድርጎ የማሰብ ችሎታ አላቸው ብሎ ሲያሟግሳቸው አፄ ዮሐንስን ግን ከሳቸው ቢነፃፀሩ እንደልጅ ናቸው ብሎ ያጣጥላቸዋል አፄ ዮሐንስ እነዚህን ጠባዮች ማንጸባረቅ የጀመሩት ገና ዙፋኑን ከባላንጣቸው ከአፄ ተክለ ጊዮርጊስ በጦር ኀይል እንደተረከቡት ነበር ማለት ይቻላልአለቃ ዐጽሜ እንደሚነግሩን ገና ዘውዳቸውን እንደደፉ ከንጉሥ ሥልጣን ሰገድ ማለትም ከአፄ ሱስንዮስ ዘመን ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ሠላሳ አምስቱን ሹመት የሰጡት የቀድሞ ነገሥታትም ሆኑ ተተኪያቸውና ወራሻቸው አፄ ምኒልክ እንዳደረጉት ሁሉ ከሌላው አካባቢም ለመጣው ጭምር ሳይሆን ለትግራይ ተወላጆች ብቻ ነበር ሥልጣንንና ሹመትን ላገር አስተዳደር ሳይሆን ከጐጥና ከወገን ሽልማት ውጭ እንዳይተላለፍ በማድረጋቸው አፄ ዮሐንስ በአገሪቷ ቋንቋ ቢነጋገሩም የመላዪቷ ኢትዮጲያ ንጉሥ ነገሥት መሆናቸውን የዘነጉ ይመስላል ለነገሩ አሁንም በሥልጣን ያለው ንጉሠ-ነገሥቱ ከተወለዱበት አካባቢ የመጣውና ልክ እንደሳቸው ሥልጣኑን በጦሩ ኀይል ብቻ የያዘው መንግሥትም ቢሆን ያደረገውና እያደረገም ያለው ይኸንኑ ነው ማለት ይቻላል ከዚህም የተነሣ አንዳንድ ልበ-ገርም ሆነ ሁናቴውን ከሩቅ ሁኖ የሚያስተውል ሰሜኖች ባይሆን ገዢዎቻቸው እንደዘመኑ ሰፋ አድርገው በአገርና በሕዝብ ደረጃ ከማሰብ ጐጥነትና ጐሣነት የተጠናወታቸውና የሚቀላቸው ናቸው ስለዚህም የመራቀቅም ሆነ ከጊዜው አብሮ የመራመድ ችግር አለባቸው ሊል ይችላል ከገዢው መደብ ተባርረው ካልሆነም ተሳስተናል በማለት ተገንጥለው የወጡት የዚያው አካባቢ ተወላጆች ኋላ ያቋቋሟቸው ድርጅቶችም ሆኑ ሥራቸው ሲታይ አስተያየቶቹ እውነተኝነት አላቸው የሚያሰኝ ይመስላል ከዋናው አሳቤ ወጣ ብዬ ይኸንንም ያነሣሁት ለትዝብት ቢሆንም መታሰብ ያለበት ቁም ነገርነት የለውም ማለት አይቻልም አስተያየቴን እዚሁ ላቁምና ወደዋናው ነጥቤ ልመልስላችሁ የአፄ ዮሐንስ ስሕተታቸው በንግሣቸው ዕለት ድርጊት ብቻ አላበቃም ልበላችሁ ይልቅስ እየተደራረበና እየተከማመረ በመሄድ ለዉጫሌ ውልም ለአድዋ ጦርነትም ከዚያም አልፎ ለማይጨው መሠረት እስከመጣል ድረስ ተጓዘ እንዴት እንደዚህ ሆነ ተብዬ መጠየቄ ስለማይቀር እስኪ ታገሡኝና ባጭሩ ላብራራየሂወት ወይንም የአድዋ ውል ተብሎ በሚታወቀው በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መንግሥታት መካከል በአድዋ ከተማ በሺ ስምንት መቶ ሰባ ሰባት ዓ. ም. በተፈረመው ስምምነት መሠረት በደርቡሾች ተከበው ለዕልቂት የቀረቡትን የግብፃውያንን ጦር አፄ ዮሐንስ ለመታደግ ከቻሉ እንግሊዝ በግብፆች እጅ የተያዘውን ቦጎስን ለናት አገር ለኢትዮጵያ መልሶ ሊሰጥ እንዲሁም በግብፆች ቊጥጥር ሥር የነበረውን ምፅዋንም ለአገሪቷ ንግድ ነፃ ወደብ ሊያደርግላት ለንጉሠ-ነገሥቱ ቃል ገባላቸው አፄ ዮሐንስ ግዳጃቸውን ከብዙ መሥዋዕት ጋር ቢዋጡም ያተረፉት ግን የደርቡሾች ጥላቻና ጠላትነታቸው ብቻ ሆኖ ቀረ መዘዙም ቈይቶ አላስፈላጊ ጦርነትና ሞታቸው ይሆናል እንግሊዞች ግን ተጠቅመዉባቸው ሲያበቃ ቃላቸውን ባለመጠበቃቸው ይቅርታም አልጠየቁ በሠሩትም ሽንገላ አላፈሩበትም ምክንያቱም ለንጉሠ-ነገሥቱ ቦጎስም አልተሰጣቸውም ምፅዋንም ቢሆን ለሳቸው ሳይሆን ዉሉን ላልተፈረመው ኢጣልያን ነው እንዲይዘው የጋበዙት እውነቱ ግን ንጉሠ ነገሥቱ ግብፆችን ከደርቡሾች እጅ ያስለቀቁበትን ቦታ ለመያዝ በቂ ጉልበትም መሣርያም ነበራቸው ግን አልያዙም ኋላም ግብፆቹ ምፅዋን ለቀው ባዶውን ጥለው ወዳገራቸው ሲገቡ ገሥግሠው ሄደው በእጃቸው ባደረጉ ነበር ይኸንን እንደማድረግ ግን እንግሊዝን እንዳንድ ገባራቸው ሎሌአቸው ብንልም ያስኬዳል መስለው መለመንና መማለድ መረጡ እሳቸው አቤቱታቸውንና ምልጃቸውን በሚያቀርቡበት ወቅት በቤተ መንግሥታቸው የእንግሊዝ መንግሥት ምስለኔ የነበረው አቶ ፖርታል እንደሚነግረን ምስኪን ግብፅ ለስሙ ያህል እንኳን ዋጋ ያለው ጦር የላት የሚታመኑ የጦር መኰንኖች የሏት ገንዘብም ሆነ የመበደር ዐቅም የላት ሰውም የላት ስለዚህም ነው ኢጣልያኖች ምፅዋ ባለቤት የሌላት ባዶ ወደብ መሆኗን ሲያዩ ከአሰብ እየገሠገሡ መጥተው በመያዝ ግብፆችን የተኩት ያኔም ቢሆን አፄ ዮሐንስ የወሰዱት እርምጃ ቢኖር እንደልማዳቸው ስሞታቸውን ለእንግሊዞች ከማቅረብ አላለፈም ለትዝብት ያህል መታወስ ያለበት ግብፃውያን ባገራቸው ውስጥ በደረሰባቸው ውዝግብ ምክንያት የለቀቁት ምፅዋን ብቻ አልነበረም ሐረርንም ጭምር እንጂ የሐረርን መለቀቅ ጭምጭምታ እንደሰሙ የያኔው ንጉሥ ምኒልክ አካባቢውን ይቈጣጠሩ የነበሩት አውሮጳውያን እንዳይቀድሟቸው ተሽቀዳድመው ገሥግሠው ሂደው አውራጃዋን ከዐራት መቶ ዓመታት በኋላ ወደቀድሞ እናቷ መለሱ አውሮጳውያንም እንዳይዳፈሩና ጦርነት እንዳይገጥሙ ሲሉ ለምን እንደወሰዷት ገልጸው ለነዚሁ መንግሥታት በጽሑፍ አስታወቁ እንዳይቃጡም የጦር ኀይልና አዲስ አስተዳደር አቋቊመው ወደመናገሻቸው ተመለሱ እንዳልኩት አፄ ዮሐንስም እንደዚያው ግብፆቹንም ሆነ ኢጣሊያኖቹን ለመጋፈጥ ከበቂ በላይ ሠራዊትም መሣርያም እንደነበራቸው የሚያከራክር አይደለምኢጣሊያኖቹ ከምፅዋ ወጥተው ገፍተው ወደደጋው ሲንሰራፉ ከላይ እንዳልነው ጀግናው መኰንናቸው ራስ አሊ በዶጋሊ ላይ ድምጥማጣቸውን ቢያጠፋ ራሱ ያተረፋት የንጉሣቸውን ተግሣጽና ቅጣት ነበር ቈይተውም ኢጣሊያኖቹ ንጉሠ-ነገሥቱን ታዝቧቸው ሲያበቃ ንቋቸው እንደገና ገፍተው ሰዓቲትን ቢይዙባቸው ንጉሠ ነገሥቱ ወደሁለት መቶ ሺ ያህል ሠራዊት ይዘው ዘመቱ ይሁንና ለማስፈራርያ ያህል እንኳን አንድ ጥይት ሳይተኲሱ ትተው ተመለሱ4 ከዚያ ወዲያ ነው እንግዴህ በራስ አሊ ጀብዱ ተቈርጦ የነበረው የኢጣልያኖች ወሽመጥ ታድሶ ነፍስ ዘርቶ የተነሣው ኋላም ንጉሠ-ነገሥቱ ኢጣልያኖቹን በይዞታቸው ትተው የሂወትን ስምምነት ለማክበር ለእንግሊዝ ሲሉ ያፈሰሱትን ደም ሊበቀሉ አገራቸውን የወረሩትን ደርቡሾች ሊወጉ ሄዱ አገሩን የተዉት ሌጣውን በኢጣሊያን ጦር እጅ ነበር ማለት ይቻላል ኢጣሊያኖችም በተቻላቸው መጠን ከመፈንጨት አልተቈጠቡም ቢባል አባባሉ ትክክል ይመስለኛል ንጉሠ-ነገሥቱ በደርቡሾቹ በጥኑ እንደቈስሉ በቈየው ስምምነት መሠረት አልጋቸውን ለንጉሥ ምኒልክ ሳይሆን ልጄ ብለው በሞት ጣር ላይ በድንገት ለተናዘዙት ለወንድማቸው ልጅ ለራስ መንገሻ ሲተው ሰዎቻችው ዱብዕዳ ሁነባቸውና ከፍተኛ አለመግባባት አምባጓሮና ትርምስምስ በመካከላቸው ተፈጠረ በመጨረሻም እያሳደዱን ናቸው ብለው ከሚያስቧቸው ደርቡሾች እጅ አምልጠው እየታመሱና እየተተራመሱ ወደመናገሻቸው ሲደርሱ ጦራቸውም ሆነ መንግሥታቸው ምስቅልቅሉ ስለወጣ ኢጣሊያንን ለመውጋት ቀርቶ ራሳቸውን ለመከላከል እንኳን ዐቅሙም መሣርያውም አልነበራቸውም ማለት ይቻላል ሁናቴው የጠቀመው ኢጣሊያኖችን ብቻ ነበር በለስ ቀንቷቸው ንጉሠ-ነገሥቱ ገና ሰዓቲትን ትተው ዞር ሲሉ ሊንሰራፉ የጀመሩት እነሱ በጥንት ስሙ ምድሪ ባሕሪ ኋላም ኤርትራ ብለው የጠሩትን አገር ገፍተው ይዘውት ቈዩ ከራስ መንገሻ ጋር የቀረው በሥልጣን ሽኩቻ ፍጥጫው ሲፋፋም ገሚሱ ሲሸፍት ሌላው ከኢጣልያኖች ሲተባበርና እየመራቸውም የቀረውን የሰሜኑን አገር ሲያስይዝ ጥቂቱ ወደደቡብ ማለትም ወደንጉሥ ምኒልክ አመራ ይኸ ሁሉ የሆነው ከውጫሌ ውል በፊት እንጂ በኋላ አልነበረምእንግዴህ ይኸ ሁሉ የሚያሳየን የትግራይ ትግርኛ ተናጋሪን ኅብረተ-ሰብ በመከፋፈል ረገድ ያፄ ምኒልክ እጅ አለበት ማለት ሐቁን ከማዛባት ሌላ ዓላማ ያለው አይመስለኝም በጊዜው በኢትዮጵያ ውስጥ የየአካባቢው ገዢዎች የነበሩት ባላባቶች አውሮጳውያን በሚለግሡላቸው ልዩ ልዩ ስጦታና በሚሰጡት ተስፋ እየተታለሉ ከአስተዳደራቸው ሥር የነበሩትን ግዛቶች እየቈራረሱ ይሰጡ እንደነበረ ሁሉ የቀድሞዋ የባሕር ነጋሽ ምድሪ ባሕሪ ማለትም የዛሬይቱ የኤርትራ ገዢዎችም ገና የውጫሌ ውል ከመፈራረሙ በፊት አገራቸውን ለኢጣልያን አስረክበው ነበር ቢባል ሐሰት አይደለም የውጫሌ ውልም ያጸደቀውና ያንጸባረቀው ይኸንን ተጨባጭ በምድር ላይ የነበረውን ሁናቴና ሰፊዋን ኢትዮጵያን ሊውጧት ተዘጋጅተው እላይዋ ላይ ያንዣብቡ ከነበሩት የአውሮጳውያን ቄሳሮች መንጋጋ ለማዳን መፋለምም ካስፈለገ ደግሞ ጊዜ ለማግኘትና ለመዘጋጀት ታስቦበት ነው ማለት ይቻላል ማን ታዲያ ይወቀስ ከተባለ ደግሞ ሁኔታዎቹ በአፄ ዮሐንስና በልጃቸው በራስ መንገሻ ጫንቃ ላይ እንጂ በአፄ ምኒልክ ላይ እንደማይጣል ያስረዳሉ አፄ ዮሐንስ ገና ኢጣልያ እግሯን በቀይ ባሕር ሲታስገባ በደምብ ሳትደራጅ ፊት ለፊት ተጋፍጠው በእንጭጯ ለማስቀረት ሲችሉ እንድትንሰራራ ዕድል ሰጡ ጦራቸውን አስታጥቀው ግብፅንም ኢጣሊያንንም መምታት ሲገባቸው ለሥልጣን ያበቋቸውን እንግሊዝ ላንድ ነፃ አገር ገዢ በጣም በሚያሳፍር መልኩ መለመንን መረጡየምፅዋን በር እኔን ደስ ይበለው ብለው እንደከፈቱልኝ ኢየሱስ ክርስቶስ የማያልፈውንየመንግሥተ ሰማይን በር ከፍቶ ደስ ያሰኝልኝ...እኔንም ከርስዎ ጋር በምክር አንድ ሁኜከፈቃድዎ ለመዋል ያብቃኝ ጥንቱንም በእግዚአብሔር ፈቃድ ለመንግሥት የበቃሁእርስዎ በሰጡኝ መድፍ ነፍጥ ባሩድ ነው አሁን ደግሞ ይልቁን ፈጽመው ደስ ያሰኙኝከዚህ በፊትም እናት ለልጅዋ እንድትጨነቅ ለኔ መንግሥት ሲጨነቁ ይኖራሉ የምፅዋንበር እንድይዝ ያድርጉኝ ብዬ እለምናለሁብለው ለእንግልጣሪቱ ንግሥት ቪክቶርያ የጻፉት ደብዳቤ አሁን ለሚያነብ ለማንም ኩሩ ኢትዮጵያዊ የሚያሳፍር ነው ብል የተሳሳተ ስሜት ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ብዬ አልገምትም አፄ ምኒልክም በበኩላቸው1 . በዚህ መጽሐፍ ላይ አቶ መኰንን ዘለለው ዮሴፍ ጥላቻና የመከፋፈል አባዜ ይቁም በሚል አርእስት በተጻፈ ጽሑፍ ሰፊ ኂስ ጽፎበታልና ስሕተቶቹን ለመገንዘቡ ማንበቡ ጠቃሚ መስሎ ይታየኛል2 . ሌላው በነዚህ ሁለቱ ጐን መከተት ይገባል ብዬ ያሰብሁት አቶ ሙሐመድ ጃዋር የሚባለውን ነበር ግን ጽሑፎቹንና ንግግሮቹን ካዳመጥሁ በኋላ ሰውዬው የአንጐል ቀውስ የሚያጠቃው ስለመሰለኝ የሚያስፈልገው ከሒስ ይልቅ የአእምሮ በሽታ ሐኪሞች ርዳታ ስለመሰለኝ ዕዳ ላልሆንበት ብዬ ትቼዋለሁ3 . በዘመነ መሳፍንት የተከሠተው ሥርዐት አልባ ያስተዳደር ሁናቴ በኢትዮጵያ ታሪክ የንጉሠ-ነገሥቱ ሥልጣን የላላበት የውድቀት ጊዜ እንጂ በመደበኛነት አይታይም የቈየውም ብዙ አይደለም4 . የሚያሳዝነው ይኸ ለኢጣልያን የተባለው ጦር ቁጭቱን በመጀመርያ ላይ የተወጣው በንጹሕ የጐጃም ሕዝብ ላይ ነበርእንደዚህ ዐይነቱን መልእክት ባይጽፉም በመጠኑም ቢሆን የቊልምጫ ደብዳቤ ለአውሮጳውያን አላኩም አይባልም በግልጥ ልኳል ከኢጣልያን ንጉሥ ጋር ሲጻጻፉ እርስዎን የመሰለ አባት የለኝም እስከማለት ደርሰዋል ያገር ክብርና ልዕልና ተነካ ብለው ካመኑ ግን ንጉሠ-ነገሥቱ ቊርጠኝነትን እንጂ ልመናን አያውቁም ነበር አባቴ እያሉ ሲያቈላምጡት ቢቈዩም የኢጣሊያን ንጉሥ የውጫሌን ውል እሳቸው በፈለጉት መልክ ሊያሻሽሉ ፈቃደኛ አለመሆኑን እንደተረዱ እንደዚያ ዐይነቱን ውል አለመፈረማቸውን አስታወቁ ዛሬም ቢሆን ይህንን የምቀበል ሰው አይደለሁም ካሉ በኋላ ኢጣሊያኖችን በሙሉ ካገራቸው አስወጥተው ማንም የኢጣሊያን ሰው ደግሞ ወዳገራቸው እንዳይገባ አሳውቀው ለጦርነት ወደአድዋ አመሩሌላው በአፄ ምኒልክ ከሚሰነዘሩት ክሶች አንዱ ንጉሠ-ነገሥቱ ድል አግኝተው እያሉ ድሉን እስከመጨረሻው ገፍተው ኤርትራን ጭምር ነፃ እንደማዉጣት ዕድሉን ሳይጠቀሙ ወደኋላ ተመለሱ የሚል ነው ወቀሳው የጊዜውን የፖሊቲካና ንጉሥ-ነገሥቱ የተጋፈጡትን ተጨባጭ የሆኑ ውዝግቦችና ችግሮች በደምቡ የሚያገናዝብ ሁኖ አይታይም ባገራችን ማን ይንገር የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ የሚል አባባል አለ አባባሉም ትክክል እንደሆነ አያጠራጥርም ምክንያቱም ከዐይን ምስክር የበለጠ ማስረጃ የለም እንግዴህ በጦርነቱ ወቅት የነበሩት በተመልካችነትም ሆነ በተዋጊነት የተሳተፉትና ጥቂት ቈይተው የጻፉት ንጉሠ-ነገሥቱ ኢጣሊያንን ከያዙት ከሰሜን አገር ግዛታቸው ጠራርጎ የማስወጣት አሳብ እንደነበራቸው ያስረዱናል ሁኖም በሰፊው ያሰማሯቸው ታማኝ የሆኑ የአገሩ ነዋሪዎች የነበሩ ሰላዮቻቸው የነገሯቸውን አስተማማኝ ነው ብለው ያመኑትን ወሬ አዳምጠው ከሠራዊታቸውና ባካባቢው ክነበረው ተጨባጭ የፓለቲካ ሁናቴ ከኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ጥቅምም ሆነ ባካባቢው በወቅቱ ከነበረው የአውሮጳውያን የፓሊትካ አሰላለፍና ውጊያው ከጫረው ዋና ምክንያት ጋር አጣምረው ቢያሰላስሉት ፍላጎታቸው እንደማይከናወን ተረድተው እንደተው እንገነዘባለንየኤርትራ ተወላጆች የነበሩት ሰላዮቻቸው ቊጥሩ ሰፊ የሆነ ያረፈ ጦር ከኢጣሊያን አገር ገና እንደደረሰ በአስመራ በምፅዋና በከረን ደግሞ እጅግ ብዙ የጠላት ሠራዊት በጽኑና በማይደፈሩ ምሽጎች በተጠንቀቅ ይጠባበቅ እንዳለ ነገሯቸው ይኸ ሁናቴ እውነት እንጂ ሐሰት አለመሆኑን ራሱ የኢጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአድዋ ድል ማግሥት ለአገሩ ሸንጎ ባቀረበው ገለጻ በማያወላግድ መንገድ ጥርት ብሎ ቁጭ ብሏል በተጨማሪ ኢትዮጵያ አምባገነኑን የነጭ ዘር አሸንፋ ለመጀመርያ ጊዜ በድፍኑ ዓለም እንዲደፈር አድርጋለች ይኸም ለነጮች እንደማይዋጥላቸውና ኢትዮጵያም ኤርትራን ቢትነካ ከብቧት ያሉት ኀያላን መንግሥታት በብራስልስ ከተማ በተደራደሩት ውል መሠረት ዝም ብለው እንደማያዩ ታዲያ ከኢጣልያን ጐን እንደሚሰለፉና በተለይ ደግሞ እንግሊዝ ኢጣሊያን ሁለተኛ ግንባር በሐረርጌ በኩል እንዲትከፍት ፈረንሳይም በጂቡቲ በኩል ወደኢትዮጵያ የሚገባውን መሣርያ ላታስተላልፍና እሷም ራሷ ላትሸጥ ሁለቱም አገሮች እንደተስማሙና እንዳረጋገጡላት ሚኒስትሩ በዚሁ ለኢጣልያን ሸንጐ ባቀረበው ዘገባ ያመለክታል ርግጠኛ ነኝ ይኸም ወሬ ቢሆን በሰላዮቻቸውና በግቢያቸው በነበሩ የአውሮጳ ተወላጆች አማካሪዎቻቸው አማካይነት ለአፄ ምኒልክ ደርሷቸዋል አውሮጳውያን አይተባበሩም ብሎ ማሰቡ ቅሌት ነው ሊሆን አይችልም አይባልም ለምሳሌ ያህል እንግሊዝና ፈረንሳይ ለአዝማናት ደመኞች ጠላቶች ቢሆኑም ፈረንሳዮች ኻያ ዓመት ሙሉ በጀግንነት በተዋጋቸው በቱኮሎሩ መንግሥት መሪ በሳሞሪ ቱሬ ላይ የኋላ ኋላ ለድል የበቁት በእንግሊዞች ትብብር ነው ምዕራባውያን ጥቅማቸውና የነጭ ዘር ክብር የተደፈረ መስሎ ከታያቸው ኢትዮጵያን ለማጥቃት ከኢጣልያንም ጋር የማይተባበሩበት ምክንያት የለም የሳሞሪ ቱሬ ዕጣ ላፄ ምኒልክም አይደርስም ማለት አይቻልም1 ዐርቆ-አሳቢ እንደመሆናቸው አፄ ምኒልክ በብዙ ኢትዮጵያውያን ደምና ትግል የተገኘውን ድል ኤርትራን ነፃ ላውጣ ብለው መቆመር አልፈለጉም በተፈጥሯቸው ውጤቱ በማይታወቅና በማያስተማምን ጉዳይ ላይ እጃቸውን ሊያስገቡ የማይፈልጉ ንጉሥ ናቸውናየአፄ ምኒልክ ችግራቸው ግን ከዚያም የከፋ ነበር ማለት ይቻላል ሠራዊታቸው ጦሩን አንግቦ ስንቁን ተሸክሞ ከቤቱ ከወጣ ከሰባት ወር በላይ አስቈጥሯል ከዚህም ሦስቱን ወር ያሳለፈው በትግራይ ሲዋጋ ነው ስንቁን ሙጥጥ አድርጎ ጨርሶ እከፍተኛ ራብ ላይ ስለነበር እንኳን ለውጊያ ቀርቶ በሕይወትና በሞት መኻል እየጣረ ነው የነበረው እንደድሮው ጦር የትግራይን ምድር ባላገሩን ዘርፎ ለምን አይበላም እንዳይባል አፄ ምኒልክ የትግራይን ሕዝብ ቀርቶበጠላት አገርም እንኳን ይኸን ዐይነቱን ተግባር የሚፈቅዱ ሰው አልነበሩም ወታደሩ ደፍሮ ቢገኝትርፉ የንጉሠ-ነገሥቱን ጥላቻና ቊጣ ማትረፍና ለከፍተኛ ቅጣት ራስን መዳረግ ነው ንጉሠ-ነገሥቱ ውጥረታቸውን አይተው ከአማካሪዎቻቸው ቢወያዩ ሁሉም አንድ ልብ አንድ ድምፅ ሁነው ሠራዊቱ ሦስት ወር ተጐድቶ ስለተቸገረ የከሳውን አውፍረን የሞተውን ተክተን ከርመን እንመለስ2 አሉና ወደሸዋ ጉዟቸውን ጀመሩ ሲሉ በጊዜ የነበሩ ጸሓፊዎች በሙሉ ይመሰክራሉአፄ ምኒልክ ወደጒራዕ ሊጓዙ ፈልገው በማይ-ፈረስ እንደሰፈሩ እናውቃለን ይኸንንም ያደረጉት ጠላትን ከኤርትራ ሊያባርሩ ሲሆን ለምን በዚህ አሳብ እንዳልገፉ ላንድ ለሠራዬ ቄስ ሲገልጡ ወደ አገርህ መቅረባችን እዚያ መምጣት አስበን ነበር ልመጣ ያልቻልሁትም በመጀመርያ ደረጃ ቀለብ አጣን ሁለተኛም አዲስ ጠላት ደርሷአል አሉን አንተ እንደምታውቀው እኔ ደም ማፍሰስ አልወድም ያሉት ጸሓፊዎቹ የሰጡትን ምስክርነት ያጠናክራል ውጊያው እንዳለቀ የአድዋን የጦር ሜዳ ዙሮ ያየው እንግሊዛዊው ዋይልድ ተዋጊዎቹን የኢትዮጵያን ባለሥልጣኖችንና ምርኮኛውን የኢጣልያንን የጦር መኰንን ጀነራል አልበርቶኔን ካነጋገረ በኋላ በጻፈው ጽሑፍ አፄው ኤርትራን ለመውረር ያላስቻላቸው ዋናው ምክንያት የስንቅ ችግር እንደነበር ይገልጣል3 እንዲሁም ወደአዲስ አበባ የተወሰዱት የኢጣሊያን ምርኮኞች በመንገዳቸው ላይ የገጠማቸውን እየገለጡ ለቤተሰቦቻቸው በጻፏቸው ደብዳቤዎች ኢትዮጵያውያን ባሳዩት ሰብእናና በሰጧቸው መስተንግዶ እያደነቁ ሲናገሩ ቈይተው ችግራችን በቂ ምግብ ማግኘት ነበር እሱንም ተከልክለን ሳይሆን ኢትዮጵያዉያን ራሳቸው የሚበሉት ስላልነበራቸው ከኛ ይበልጥ ተቸግረው ነበሩ እያሉ ይገልጣሉአፄ ምኒልክ በዚህ አስቸጋሪ ሁናቴ ተወጥረው ሳሉ ነው እንግዴህ ኢጣልያኖች የምራቸውን ሊደራደሩ መፈለጋቸውን ሲያውቁ እኔም የምፈልገው ዕርቅ ነውና እኔ በወደድሁት ከታረቃችሁ የሚስማማኝም ቃል ከሆነ እውነተኛ ሰው አዲስ አበባ ድረስ ይምጣና ይጨርስ ብለው ወደከተማቸው የተመለሱትየአፄ ምኒልክ አሽሟጣጮች መረዳት ያቃታቸው ዋና ነገር ቢኖር የአድዋ ጦርነት መነሾው ኢጣልያኖች በሺ ስምንት መቶ ዘጠና ዓ. እ. ላይ ግዛታችን ናት ብለው ኤርትራ የሚል አዲስ ስም ሰጥተው ላለም ሁሉ ካስታወቁት ምድር አልፈው የኢትዮጵያን መሬት በመውረራቸው መሆኑን ነው ኢጣሊያኖች የቅኝ ግዛቱን ካፄ ዮሐንስ ሞት በኋላ በሰሜን የተፈጠረውን ትርምስምስና ምስቅልቅል ተገን አድርገው ነው የያዙት ግን ራስ መንገሻ ከአፄ ምኒልክ አኩርፈው በነበሩበት ወቅት የመረብ ውል ብለው በራሳቸው ተነሣሥተው ከኢጣልያን ጋር በገቡት በሺ ስምንት መቶ ዘጠና አንድ ዓ. እ. ስምምነት የኢጣሊያን ይዞታና ግዛት መሆኑን በጣታቸው ፊርማ አረጋግጠውላቸዋል የአድዋ ጦርነት የአፄ ዮሐንስ ተተኪዎችና አፄ ምኒልክም ራሳቸው እሺ ብለው የፈረሙትንና ኢጣልያንም እንደግዛቱ ከያዘው ሰባት ዓመት ያስቈጠረውን መሬቱን መልሶ ለመውሰድ እንዳይደለ መታወቅ አለበት እውነት ነው ኢጣሊያን ኢትዮጵያን ሲትወጋ የውጫሌም የመረብም ዉሎች ስለፈረሱ በውሉ ለታወቀላትም የመሬታ ይዞታ መብት የላትም ይኸ በግብር ሊውል የሚችለው ግን ኢትዮጵያ ልዕልናዋንና ነፃነቷን በማያሰጋ መንገድ ከተቻለ በሰላም ካልተቻለ በግድ ከኢጣሊያን እጅ ለማስለቀቅ ከቻለች ብቻ መሆኑ አያጠራጥርም በዚህ ጽኑ እምነት ተመሥርተው ንጉሠ-ነገሥቱ ወታደራቸው የስንቅ ችግር እያለው ኤርትራን ተሻግሮ ኢጣሊያንን መውጋት የተቀናጁትን ድል አደጋ ላይ ሊጥልና ኢትዮጵያም በጠላት እጅ ሊትወድቅ ትችላለች በሚል ስጋት ተዉት በነጭ አምባገነንነት ዘመን ብዙዎች እንደህንድና ቻይና የመሰሉ አገሮች ሳይቀሩ ሰፊውን አገራቸውን ከነጣቂዎቹ ምዕራባውያን እጅ ለማዳን ሲሉ በርካታ መሬት ከግዛታቸው እየቀነጨቡና እየሸራረፉ ሰጥተዋል አሁን ግን ጉልበት አግኝተው ነጮቹ ሲለቁ ካልሆነም በኀይል በማስለቀቅ መልሰው ሊወስዷቸው በቅተዋል ታዲያ ይኸንን የጊዜውን ፈሊጥ ተጠቅመው አፄ ምኒልክ ኢትዮጵያን ከነጭ እጅ ቢታደጓት ክፋቱ ምንድር ነውአፄ ምኒልክ በአዲስ አበባ በተዋዋሉት ስምምነት ወደአድዋ ጦርነት የመራው የውጫሌ ውል ፈርሶ ሌላ አዲስ ውል ሲፈርሙ መረብ መላሽን ማለትም የኢጣልያንን ኤርትራን በሰላምም በጦርም ከኢጣሊያን ሊያስለቅቁ ባይችሉም አገሩ በሙሉ የኢትዮጵያ መሬት መሆኑን ኢጣሊያም በምንም ምክንያት ቢትለቀው በከፊልም ሆነ በሙሉ ለሌላ ሦስተኛ መንግሥት እንዳታስተላልፍ ታዲያ ለባለቤቷ ለኢትዮጵያ መልሳ እንዲታስረክብ ያስገድዳል ይኸንን እስምምነቱ ውስጥ የተከተተውን... የኢጣሊያ መንግሥት ከዚህ አገር ለማንም ማን መንግሥት መስጠትና መልቀቅ አይቻለውም ዛሬም የኢጣሊያ መንግሥት በእጁ ከያዘው አገር መልቀቅ ያማረው እንደሆነ ለኢትዮጵያ መንግሥት ይመልሳልየሚለውን አንቀጽ ዐምስትን ኢጣሊኖች ተቀብለውት በፊርማቸው ሲያጸድቁላቸው አፄ ምኒልክ በወቅቱ በጦር ኀይል ለመያዝ ዐቅማቸው ባይፈቅድላቸውም ሕዝቡና መሬቱ ግን የኋላ ኋላ የኢትዮጵያ ሀብት መሆናቸውን አረጋግጠዋል ስለዚህም ኢትዮጵያ የመረብ መላሽ ባለቤትነቷ በገሃድ ከታወቀ ጊዜውን ጠብቃ አንድ ቀን በግድም ሆነ በሰላም አለበለዚያም በውል ከኢጣሊያን እጅ መልሳ እንደሚትረከብ ንጉሠ-ነገሥቱ ርግጠኛ ነበሩ ማለት ባይቻልም ለመጪው ትውልድ ጠንካራ መሠረት ጥለውለታል ቢባል ሐሰት አይደለም እርሳቸው የጀመረቱን ወደአስደሳች ፍጻሜ ማድረስ የተከታዩ ትውልድ ዕጣ ፋንታው ነውኢጣልያን የአድዋን ጦርነት የመረጠችው በዘመኑ አከራካሪ ባልነበረው ነጭ ዘር ከሰው ሁሉ ዘሮች ምርጥ ፍጥረት ስለሆነ የትም ቢሄድ የበላይነት አለው የሚል መርህ ዋነኛ እምነቷ ስለነበር ነው ስለዚህም እንደሌላው ነጭ በየትም ሕዝቧን ሊታሰፍር የማንኛውንም የሌላውን ዘር ሀብት አለጭቅጭቅ ሊትወርስ ሕይወትና ነጻነት ሊትቈጣጠርና ሊትነፍግ ለሞትም ሊትበይን ማለትም ሊትገድልና በራሷ ዘር ሊትተካ ግዴታና አላፊነት አለኝ ባይ ነበረች ስለዚህ ኢትዮጵያ በማንም ነጭ ሳትያዝ የቀረች ብቸኛ የጥቊር አገር ስለሆነች ለኔ ትገባኛለች ባይ ነበረች የኢትዮጵያ እምቢተኝነት ወደአድዋ ጦርነት አመራ የአድዋ ድል እንግዴህ ስለሰው ዘር እኩልነት ስለሕግ የበላይነት ሰው በሰብኣዊነቱ ለሕይወት ለሀብት ለነጻነት ስላለው መብቶች አለመደፈርም ነው ድሉ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውንን ላለም አስታወቀ አፄ ምኒልክም ዕድሉን ላገር ግንባታ ተጠቀሙት ጤናማ በነበሩት በዐሥራ ሦስት ዓመት ውስጥ ኢትዮጵያን ወደከፍተኛ ሥልጣኔ ለማራመድ በነበራቸው ምኞት በጊዜው የነበሩትን የተለያየ የሥልጣኔ ዘርፍ ከመላ ጐደል አንድ ባንድ ወዳገር ውስጥ አስገቡ ከባቡር ሐዲድ እስከሴቶች መብት መጠበቅ ድረስ ያልነኩት ነገር የለም ባርያ እንዳይፈነቀል የእጅ ሥራ እንዲከበር ጐጥና ጐሣ እንዲጠፋ ወታደርና ነፍጠኛ ድኻውን እንዳይበዘብዝ ማንም እንደፈለገ እንዲያመልክ እንጂ በሃይማኖቱ ምክንያት እንዳይሰደድ ገበሬው ከመሬቱ እንዳይነቀል በየጊዜው አዋጅ አስተላልፈዋል ለሹሞቻቸው ሥልጣን ለሰው አገልግሎት እንጂ ለራስ ጥቅም መዋል እንደሌለበት አስተምረዋል በሥልጣን በመባለግ ሕዝብን ለበደለና ለጨቈነ አገር የሚገዛው በብልሃትና በጥበብ እንጂ በጭካኔ አይደለም በማለት ገሥጸዋል ካልሰማም ከሹመቱ ሊያወርዱ ተገደዋል ሁሉንም በፍቅርና በብልሃት ከመምራታቸው የተነሣ ሕዝባቸው እንደንጉሠ-ነገሥት ሳይሆን እንደእናት በማየት እምዬ ምኒልክ የሚል ቅጽል እስከመስጠት ደርሷልየአፄ ምኒልክ ኂሰኞች ሊረዱት ያልቻሉት እሳቸው በጣሉት መሠረት ላይ አገሪቷን የመገንባት ትውልዳዊ አላፊነትና ግዴታ እንዳላቸው ነው እንደረሱትም መረዳት ከፈለግን ወደሩቅ ሳንሄድ እስኪ በአድዋ የተፈጸመውን ድል በቅርብ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ በነሱ ሥርና መሪነት ከተጐናፀፈው ሌላ ድል ጋር እናነጻጽር በሁለቱ ጦርነት መካከል ያለው ልዩነት በጣም ብዙ ቢሆንም አንዳንድ ጠቃሚ አሳብ ሊሰጠን የገዢዎቹንም ባሕርይ ለመገንዘብ ጭላንጭል ሊሆንልን ይችላልየወያኔ መንግሥት እንደድሮው ነገሥታት በጠመንጃ ኀይል የአፄ ምኒልክን ግቢ ከተቈጣጠረ በኋላ እንደዋና መርሀ-ግብሩ አድርጎ የፈጸመው ምድሪ ባሕሪን ማለትም የኢጣሊያንን ኤርትራ ራሷን የቻለች ነፃና ልዕልት አገር እንዲትሆን ነው ከመካከላቸው ጭንጩ ምሁር የተባለው መሪያቸው መለስ ዜናዊ ድርጅቱ ገና በጫካ ሳለ ትግሊ ኤርትራ ናበይ ካበይ በሚል አርእስት በትግርኛ ቋንቋ በጻፈው መጣጥፍ ቢጤ አገሪቷን እንደኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት አድርጎ ፈርጇታል ከሰውና ከሥልጣኔ ተለይቶ እዱር ውስጥ ከታጋዮቹ ጋር ሁኖ በደምብ ሳይገነዘብ የሸረበው የካርል ማርክስና የኅብረ-ስብኣዊነት ርእዮተ ዓለም አእምሮውን አደነባብሮት ካልሆነ በስተቀር በመጽሐፉ የተወሸከተው ትችት እላይ ካየነው የታሪክ ዘገባ በጣም ይጋጫል እንግዴህ አስተሳሰቡ በዚህ መልክ የተኰለኰለ ቡድን ነው ወደአፄ ምኒልክ ቤተመንግሥት እየገሠገሠ ገብቶ በዙፋናቸው ቊጭ እንዳለ ኤርትራ ከቀኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ተገላግላለች ሲል ባዋጅ ሁለቱን አገሮች መልሶ የከፋፈለ የኤርትራም መሪዎችም ቢሆኑ የቀኝ ገዢዎቻቸውን የኢጣሊያንን ቅርስና ውርስ የሚያደንቁና የሚያመልኩ ነበሩ የኢጣሊያኖች የአስተዳደር ዘመን አገሪቷ መሰል በማይገኝለት የኢሰብኣዊ ሥቃይና የአረመኔኣዊ ግፍ ማጥ ውስጥ ተዘፍቃ በኀይል ታጣጥር የነበረችበት የቀውጢ ወቅት እንደነበር ረስተውታል ኢትዮጵያም ያኔ ለሕዝቡም ለነሱም እናት አገራቸውና የነፃነት አምባቸው ተስፋቸውና ሙጥኛቸው እንደነበረች ዘንግተውታል ይኸ እንዳልሆነ ሁሉ ነፃነታቸው እንደታወጀ መሪዎቹ ለኢትዮጵያ የነበራቸው መርህ ያው ልጅ አባቱን አይብ አጓቱን እንደሚባል ከኢጣሊያን ቅኝ ገዢአቸው በወረሱት ፈሊጥና እምነት መሠረት ወይ መበታተን ካልሆነም በሞግዚትነት ማስተዳደር በሚል አቋም የተወቀረ ነበር እንግዴህ ኤርትራ በምንም መልክ ኢጣልያን ባትመስልም መሪዎቻችዋ ግን ሕልማቸው ትልቅ ነበር ማለት ይቻላልና በድንበር አመኻኝተው ባድሜ የተባለውን አካባቢ ሊወስዱ በ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. የሰሜን ኢትዮጵያን ወረሩየወያኔም መንግሥት የኤርትራ ጦር ባድሜ የተባለችውን ግዛታችንን በጒልበት ሊወስድብን ነውና የጐበዝ ያለህ ተደፍሮ የማይታወቅ ታሪክህ ስለተደፈረ መጥተህ ምታዉና ትምህርት አስተምረው ሲል የክተት ዐዋጅ ዐወጀ የኢትዮጵያም ሕዝብ እንደልማዱ እናት አገሩን ከጥቃት ሊከላከል የጥንት ጀግንነቱን ሊያስመሰክር በገፍ ወጣ በተለይም ወደዚያ ጦር ሜዳ የሄደውን ያንዳንድ የሱማሌ ኅብረተ-ሰብ አባላት ወኔና ጀብዱ ለዜና አቅርበው ሲታዩና የሚናገሩት ሲሰማ አድዋን ትዝ ያሰኛል የማንም ዐይን እንባ ይተናነቀዋል መንፈሱ ይነካል ወኔው ይንቀሰቀሳል በዚህ ውጊያ የጠፋው የአካባቢው ንብረትና የሰው ሕይወት ብዛት ሳይቈጠር ወታደሩ ብቻ ከሰባ ሺ በላይ ሕይወቱን ሠውቷል ይባላል ይኸም ማለት የአድዋ ከዐሥር ጊዜ በላይ ዕጥፍ መሆኑ ነው ያ ሁሉ መሥዋዕት ተከፍሎ የሚገርመው ግን ከድሉ በኋላ የታየው ውጤት ነውበሥልጣን ላለው መንግሥት ኤርትራ የገዛ እጁ ፍጡር ነበረች እንደፈጠራት የሠራችውን ጥፋት ተመርኲዞ ከድሉ በኋላ ወደኢምንት በቀየራት ነበር ካልሆነም የኢትዮጵያን የዘለቄታ ጥቅም የሚጠብቅ ወይንም ዳግመኛ በኢትዮጵያ ጉዳይ ውስጥ ፈጽሞ እንዳትገባ የሚያደርግ ውል በተፈራረመ ነበር ግን አንዱም አልሆነም የሆነው ማንም ጭንቅላት ያለው ማመን የሚያዳግተው በታሪክም ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ የጉድ ጉድ ነው ቢባል ሐሰት አይደለም ከአድዋ ድል በኋላ በኢትዮጵያና በኢጣሊያ መካከል የተደረገውን ትርጒም የሌለውን የቅኝ ግዛት ውል ለዘመናት ሙቶ ከተቀበረበት በግር ተፈረስ አስፈልጎ አንሥቶት ሕያው አደረገውና ድርድራችን በዚህ ይሁን አለ የኤርትራም መሪዎች ደስታውን ስላልቻሉ ቦረቁ ፈነጩ ማለት ይቻላል ነገሩ ያ ሁሉ የኢትዮጵያ ሠራዊት የተሠዋለትን ድል መልሶ ለኤርትራ ሸጠው ሆነ በዚህ ብቻ አላቆመም ድርድሩ በተካሄደበት ወቅት በሄግ የተቋቋመው የገላጋዮቹ ቡድን የኢትዮጵያ መሬት ናቸው ብሎ አንዳንድ አካባቢ ወሰኖ ሰጠ የወያኔም መንግሥት መሬቶቹ የኢትዮጵያ አይደሉም አንቀበልም ሲል ደረቱን ነፍቶ አንገቱን ገትሮ ለኤርትራ እንዲሆኑ ተሟገተ በርግጥ የቡድኑ አባላት ማመኑ አቅቷቸው በመደነቅ ወይ የጉድ ጉድ ሳይሉ አልቀሩም ቡድኑ ምርጫ ሲያጣ መሬቶቹን አለፍላጎቱ ለኤርትራ አሳልፎ ሊሰጥ ተገደደ ይሁንና በዚህ ብቻ አላበቃምየድርድሩ ውሳኔ ይፋ በሆነ ጊዜ ያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበረው አቶ ሥዩም መስፍን በጦር ሜዳ ያገኘነውን ድል በሕግ አስመሰከርነው ባድሜ ለኛ ተፈረደች ብሎ ደነፋ የፖሊትካ ጨዋታ እንጂ ሐቅ አልነበረም እውነቱ ያ ከሰባ ሺ በላይ ሠራዊት ሕይወቱን ሠዋለት የተባለው ባድሜ መንግሥት ራሱ መዳኛ ብሎ ባቀረበው የቅኝ ግዛት ውል መሠረት የኤርትራ ናት ተብሎ ተበየነ ሠራዊቱ አጥንቱን የከሰከሰለት ደሙን ያፈሰሰለት ባድሜ የከንቱ ከንቱ ሁኖ ተገኘ ብልህና አስተዋይ የሆነው የተዋጋነው ለካስ የኢትዮጵያን ሳይሆን የወያኔንና የቡችሎቹን ሥልጣንና ክብር ለመጠበቅ ኑሯል ሳይል አልቀረም በሠለጠነ ዓለም ቢሆን እንደዚህ በሕዝብ ሕይወት ላይ የሚቀልድ መንግሥት ላንዳፍታ እንኳን ሳይቈይ በፈቃዱ ሥልጣኑን ለቆ በሄደ ካልሆነም ቢያንስ ቢያንስ ለአገሩ ሕዝብ ከፍተኛ ይቅርታ በጠየቀ እንደዚህ ዐይነቱን ስሕተት ላይደግም ቃል በገባ የኢሕአደግ መንግሥት ግን አንዱንም አላደረገም ይልቅስ ምንም እንዳልሆነ አስመስሎ ሥራውን እንደወትሮው ቀጠለ በዚህም ሥራው ለሕዝብና ለአገር ጥቅም ያልቆመ መንግሥት መሆኑን በግልጥ አስረዳ ማለት ነገሩን ማቃለል ይሆናል ጥቂት ክብደት የሚኖረው ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ከልክ በላይ ናቀ ቢባል ትርጒም ይኖረዋልስለናቀም ነው እንግዴህ የአገሯን ድንበር እየሸረሸረ መሬቷን እየሸነሸነ ለባዕድና ለጐረቤት አገር የሚሰጥ ከሌላው እየነጠቀ ለወገኑና ለደጋፊው ብቻ የሚያድል አገር ገንቢዎችንና ያንድነት አራማጆችን የሚያስር የቀለም ምሁራንንና የነፃ ጋዜጦች ጸሓፊዎችን በእስር ቤት የሚያጉር የሃይማኖት መልእከተኞችንና ሰባኪዎችን የሚያሳድድ ላገር ጥቅም እንደመቆም ለባዕድ ቱኪ ሁኖ የሚያገለግል ይኸንን ሁሉ አፄ ምኒልክና የአድዋ ትውልድ ቢሰማ ምን ይል ይሆንይኸ መንግሥት ነው እንግዴህ በቅርቡ የአፄ ምኒልክን ስም ለማጉደፍ ሲል ከፍ ያለ ዘመቻ የሚያካሄድ ያለው ዘመቻውም ግቡን እንዲመታ ሲል ያልሞከረው ስልት ያላደረገው ሥራ ያላጠፋው ገንዘብ የለም ያም ሁሉ ሁኖ ግን አፄ ምኒልክን በቅኝ ገዢነት ከሚፈርጁ ከጥቂቶች የብሔረ-ሰቦቻችን ነፃ አውጪ ነን ብለው ራሳቸውን በራሳቸው ከሾሙት የዘመኑ ባላባቶችና ድርጅቶቻቸው ዘንድ ካልሆነ በስተቀር በጠቅላላ ዘመቻው የሠመረለት አይመስልም በአዞዎቹ ቄሳራውያንና በነጣቂ ባላባት የተጥለቀለቀውን የዘመኑን ዉሃ በብልሃትና በጥበብ እየዋኙት እርሳቸውም ሳይነኩ አገራቸውም ሳትጐዳ ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያንና ልጆቿን ለዝናና ለታሪክ ያበቁት አባት በቀላሉ ይሸነፋሉ ብሎ ማመኑ አስቸጋሪ ነው ሁኖም የአድዋ ጀግኖች ተተኪው ትውልድ እነዚህን ከንጉሠ-ነገሥቱ ቤተ-መንግሥት ውስጥ ተወሽቀው ስማቸውንና የገነቡትን አገር ለማጥፋት ያወጁትን የአስሶ ደምስስ ክተት አዋጃቸውን የመቅጨትና የመቀልበስ ግዴታ እንዳለባቸው መርሳት አይገባቸውም የአፄ ምኒልክ የአድዋ ክተት አዋጅ ድምፅ ማለትም አገር የሚያጠፋ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት መጥቷል... እንግዴህ ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ስለኔ ሞት አላዝንም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ርዳኝ ጉልበት የሌለህ ደግሞ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በምትችለው መንገድ ርዳኝ የነሱም የአገር አድን ጥሪ ድምፅ መሆን ይገበዋል በየአደባባዩ በየአድባራቱ በየመስጊዱ በየቀዬው በየመገናኛ መሣርያ እንዲሁም አገር-ወዳድ ኢትዮጵያዉያን በየተሰቡበትና በሚገኙበት ሁሉ በጨራራ ድምጽ ከመቼም ጊዜ ይልቅ ማስተጋባት ያስፈልጋል እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በቋንቋና ሃይማኖት በፆታና ዕድሜ በሙያና ማዕርግ በቀዬና ወገን ሳይለይ ለአገሩ ለልጁ ለሚስቱ ሲል በኢትዮጵያዊነቱ ካልተሰበሰበ ፋይዳው ሸንፈትና ጥፋት መሆኑ አምኖ መቀበል ይኖርበታል የነአሻንቴ የነዙሉ የነቱኮሎር ጦር የኋላ ኋላ ድል እንዲሆን ካበቁት ምክያቶች ዋናው ልክ ኢጣልያን የአካባቢውን የሰሜኑን ጦር በተከታታይ ድል እንደነሣች ሁሉ እነሱም ጠላታቸውን በተናጠል በመፋለማቸው ነበር የአድዋ ጦር መለዮው ኢትዮጵያዊነት ኢትዮጵያዊነት ደግሞ ብዙ ብሔረ-ሰብን ያካተተ አንድነት ነበር አንድነት ኀይል ነው እንደተባለ አንድነታቸውን መከታ አድርገው በቊጥሩ ብዛት ከዚያ በፊት በአፍሪቃ ምድር ያልታየውን የነጮችን ጦር ብትንትኑን አወጡ የአድዋ ድል የኢትዮጵያውያን መታወቂያ የነጻነታቸው ዋስትና ብቻ ሁኖ አልቀረም ለድፍኑ ዓለም ጭቁን ሁሉ የሐርነት ጨረርና መመኪያቸው ሆነ እንግዴህ በዓሉ በኢትዮጵያ ሳይወሰን ቢቻል በመላው ዓለም ካልሆነም በአፍሪቃ ክፍለ-አገር ደረጃ እንዲከበር ቢጣር ተገቢ ነው ይኸንን ግብ ለመምታት ኢትዮጵያውያን መጀመርያ ቤታቸውን ማጥራት የአድዋ ድል ያመጣላቸውን ክብርና የአንድነታቸውን መታወቂያ ማሳደስ ይኖርባቸዋል ቸር ወሬ ይግጠመን1 . እንግሊዞች ከድሉ በኋላ ለጽርኡ ንጉሥ እስክንድርና እሱን ለመሰሉት በዓለም ታሪክ ከፍተኛ ሚና ለተጫወቱት መሪዎች የሚሰጡትን ታላቅ የሚትለውን ቅጽል በመጀመርያ ላይ ለአፄ ምኒልክም ሰጥተው ታላቁ አፄ ምኒልክ በማለት ታላቅነታቸውን አውቀው ነበር ኋላ ቅጽሉን ያነሡት ኢጣልያኖች እንዲህ ማለቱ ኢጣሊያንን ብቻ ሳይሆን የነጭን ዘር በሙሉ ያዋርዳል ብለው ስለወቀሷቸው ነው ተብሎ ይታመናል2 . ያነ የኢጣሊያን ጦር እስከምፅዋ ሊያባርሩ ምክረው ነበር ግን ሠራዊቱ ሦስት ወር በረኀብ ተጐድቶ ነበርና ተቸገሩ የከሳውን አውፍረን ከርሞ እንመለስ አሉና ተመለሱ አለቃ ተክለ ኢየሱስ የኢትይጵያ ታሪክ ጸሓፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ በታሪከ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ መምህር አፈወርቅ ዮሐንስ በዳግማዊ አጤ ምኒልክ የሚነግሩን ይኸንኑ ችግር ነው3 . የአፄ ምኒልክ ድል ሙሉ ለሙሉ እንዳይሆን ያቆመው ጦሩን ያጋጠመው የስንቅ እጥረት ብቻ ነበር
አድዋ ሲከፋህ የምታጥላለው ሲደላህ የምታከብረው በዓል አይደለም! አድዋ አድዋ ነው! የመላ ጥቁር የነፃነት ቀን ነው! ጥቁርነት ሲከፋህ የምትደብቀው ስልጣን ላይ ስትሆን የሚታወስህ ከሆነ አድዋን አታውቀውም!አድዋ ወገንህ ቤተ መንግስት ሲገባ የምታከብረው ተጨቆንኩ ብለህ የምትረግመው በዓል አይደለም እንደ ሰው ቀና ብለህ እንድትሄድ ያደረገህ የተጋድሎ ዕለት ነውና! አድዋ ስትጨቆን ተስፋ ይሰጥህ ዘንድ ሲደላህ ወዳለፈ ባርነትህ እንዳትመለስ የምታስታውሰው በወረት የማይረሳ ገድል ነው!አድዋ በወረት የሚከበር በዓል አይደለም እኔና አንተ በወረት ብናከብረው በወረት ብንተወው ዓለም የመሰከረለት ነው! እኔና አንተ በወረት ብንተወው አይቀዘቅዝም እኔና አንተ በወረት ብናከብረው የበለጠ አይደምቅም! አድዋ ራሱን በደማቅ ታሪክ ያስቀመጠ ወረት ያልበገራቸው ገንዘብ ያልገዛቸው ነጭ ያላንበረከካቸው አባቶቻችን ገድል ነው!
የዓድዋ ድል በዓለም አቀፍ ታዋቂ ሰዎች እና ምሁራን ዕይታ::ባሕር ዳር የካቲት 212011 ዓ.ምአብመድ የዓድዋ ድል 120ኛ ዓመት ዝክረ በዓል ሲከበር የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝደንት ታቦ ምቤኪ የዓድዋ ድል በዓልን ማንኛውም አፍሪካዊ የኔ ነው በሚል ስሜት ማክበር እንዳለበት ተናግረዋል አፍሪካውያንን አሁንም ወደፊትም አንድ የሚያደርግ እሴት መሆኑንም ጠቁመዋል የቀድሞው ፕሬዝደንት ገጠመኛቸውን ሲያወሩም በአንድ አጋጣሚ ሦስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደ እኔ መጡ ክቡር ፕሬዝደንት በትምህርት ቤት የምንማረው ጥቁሮች የባሪያ ንግድ ቅኝ ግዛት አፓርታይድ እና ሌሎች ጥቃቶች ሰለባዎች እንደነበሩና አሁንም በእጅ አዙር ያው ነው እየተባልን ነው አፍሪካውያን የሠሩት በጎ ነገር ወይም ከተጠቂነት የተላቀቁበት ታሪክ የለም ወይ? ይህ መጥፎ ስሜት ይፈጥርብናል ከዚህ መጥፎ ስሜት መውጣት አልቻልንም አሉኝ በወቅቱ ድንጋጤ ነው የፈጠረብኝ በትምህርት ሥርዓቱ የዓድዋ ድልን የመሳሰሉ የአፍሪካውያንን በጎ ታሪኮች በአግባቡ ማካተት ትውልዱን ከመሰል ችግር ያድናል ነበር ያሉትበዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ራይሞንድ ጆናስ የዓድዋ ድል በተሰኘው መጽሐፋቸው የዓድዋ ጦርነት ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ድልን ያቀዳጀ ለጣሊያን ደግሞ የሽንፈት ጽዋን ያስጎነጨ ነበር ሲሉ ገልጸውታል ጣሊያን ዘመናዊ እና እስከ አፍንጫው የታጠቀ ጦር ይዞ ቢመጣም ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ወኔና መሰዋዕትነት ጦርነቱን ማሸነፋቸውን መስክረዋል ፕሮፌሰሩ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውንና የአፍሪካን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ቀጣይ የፖለቲካ አቅጣጫ የቀየረ ነበር ብለዋል በሙያዊ ምሥክርነታቸውበታሪክ ጥቁር ሕዝቦች ነጭ ወራሪን እስከመጨረሻው ድል ያደረጉበት የመጀመሪያው ክስተት ነበር አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆኑ አሜሪካውያንን ጨምሮ ሌሎች የቅኝ ግዛት ሰለባ ሀገራት ጸረ ቅኝ ግዛት ትግል በዓድዋ ድል ምክንያት በተፈጠረ መነሳሳት ጀምረዋል ቅኝ ገዥዎችም ከዓድዋ ድል በኋላ የግዛት ማስፋፋታቸውን ገትተዋል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ጆናስእንግሊዛዊው ጸሐፊ ፖል ሄንዝ በበኩሉ የጊዜ ንብርብር የሚል አንድምታ ባለው መጽሐፉ የዓድዋ ድል ለጥቁር ሕዝቦች የኩራት እና የትግል ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ደማቅ አሻራ የጣለ ነው ብሏልከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አንስቶ በሁለት የተለያዩ የምርጫ ዘመናት እንግሊዝን የመሩት ሰር ዊንስተን ቸርችልም ስለዓድዋ ድል ጽፈዋል የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም የዓድዋ ጦርነት ተካሂዶ ጣሊያን በኢትዮጵያ ታላቅ ሽንፈት ደረሰባት ይህም ሌሎች ሀገራት ላይ በሁለት መንገድ ተጽዕኖ አሳድሯል በአንድ በኩል አውሮፓውያን በሰሜን አፍሪካ የነበራቸው ክብር ኮስምኗል በሌላ በኩል ደግሞ ጣሊያን በአውሮፓ ኅብረት ያላት ተሰሚነት በእጅጉ ወርዷል ነበር ያሉት ቸርችልአንዳንዶች ሰር ዊንስተን ቸርችል ስለ ኢትዮጵያ ድል ማድረግ ሳይሆን ስለ ጣሊያን ድል መሆን አጽንኦት ሰጥተው ጽፈዋል ቢሉም ዓድዋ ግን ብዕራቸውን ለመምዘዛቸው ምክንያት መሆኑ ሀቅ ነበርኢትዮጵያዊው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው የዓድዋ ድል ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ተሰሚነቷ እንዲጎላ እና ትኩረትን እንደትስብ ማድረጉን አስፍረዋልሌሎች ጸሐፊያን ምሁራን እና ታዋቂ ሰዎች ስለ ዓድዋ ድል ምን አሉ? የወደዳችሁትን አካፍሉንመረጃው የተገኘው ከተለያዩ ምንጮች ነው
120ኛ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በዳላስ በደመቀ ሁኔታ ተከበረየአድዋ ድል ጀግኖች አያቶቻችን ሃገራችንና ህዝባችን በነጭ ቁጥጥር ስር በባርነት እንዳይወድቅ አጥንታቸው ከስክሰው ደማቸውን አፍስሰው እልህ አስጨራሽ ውግያናተጋድሎ በማድረግ ድንበር ተሻግሮ የመጣው የፋሽስት ጣልያን ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ጥቁር ነጭን እንደሚያሸንፍ በተግባር ያሳዩበት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆንለመላው ጥቁር ነፃነት መሰረት ነው ስለ አድዋ እንዲህ በቀላሉ ተነግሮ እሚያልቅ አይደለም ለኢትዮጵያውያን የዛሬ ማንነታችን ውጤት የአድዋ ድል ነውይችን ታሪካዊ ዕለት 120ኛውን ዓመት ለመዘከር እሁድ March 6, 2016 ፕሮግራሙ ያዘጋቸው የኢትዮጵያውያን ጉዳዮች ፎረም በዳላስ ሲሆን በእለቱ ብዙኢትዮጵያውያን ተሳትፈው ለበዓሉ ድምቀት ሰጥተውታል ፕሮግራሙ አድዋን የተመለከተ ዶክመንታሪ ለታዳሚው በማቅረብ ተጀመረ ዶር መስፍን ገናናውና አቶይርጋለም ጎበዜአገሬ ኢትዮጵያ የእለቱ የክብር እንግዳ የነበሩ ሲሆን አቶ ይርጋለም ጎበዜ አድዋን የተመለከተ ሰፊ ትምህርት የሰጡ ሲሆን ዶር መስፍን ገናናው የአርበኛአያቶቻችን የአድዋ ተጋድሎ ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር በማያያዝ ንግግር አድርገዋል የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር ዋና ጸሃፊ አቶ ሙሉጌታ ኮሚኒቲውን በመወከል ንግግር አደርገዋል አጼ ሚኒልክና እቴጌ ጣይቱ የነበራቸው በሳል አመራር በሰፊው ተወስቷልአዳራሹ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በጋሻና ጦር እንዲሁም የአጼ ሚሊክና እቴጌ ጣይቱ ባህላዊ አለባበስ ጨምሮ የሌሎች አርበኞች ባህላዊ የአለባበስ ስርዓት በለበሱ ተሳፊዎችደምቆ ነበር ከዚህ በተጨማሪ የአጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ ጨምሮ አድዋ ሲነሳ ሁሌም ስማቸው የሚነሱ አርበኞቻችን ፎቶግራፍ ሁሉንም ማግኘት ባይቻልም የተወሰኑትንተሰቅለው ነበርበፕሮግራሙ መሃል አድዋን የተመለከቱ ባህላዊ ጣዕመ ዜማ ያላቸው ሙዚቃዎች በዲጄ ዮናስዩቶፒያ የቀረቡ ሲሆን ከእንግዶችና ከታዳሚዎች ግጥም ቀርበዋል የአጼሚኒልክና የእቴጌ ጣይቱ ፎግራፍ ያለበት በኮሚቴው የተዘጋጀ ኬክ ተቆርሷል በመጨረሻም የበዓሉ ተሳፊዎች ውይይት አድርገውና የፕሮግራሙ አዘጋጆችን አመስግነውየፕሮግራሙ ፍፃሜ ሆነኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!የኢትዮጵያውያን ጉዳዮች ፎረም በዳላስ
አያቶቻችን ዛሬ ቢኖሩ አድዋ ከጣሊያን ጋር በተዋጉበት ጉልበት ከልጅ ልጆቻቸውም ጋር ይፋለሙ ነበርPublished 5 hours ago on February 27, 2019 By Teshome Tadesse አያቶቻችን ዛሬ ቢኖሩ አድዋ ከጣሊያን ጋር በተዋጉበት ጉልበት ከልጅ ልጆቻቸውም ጋር ይፋለሙ ነበር እኛ ልናፈርሳት የምንታገላትን ኢትዮጵያ በእኛ ዓይን ጣሊያንማ ምን አደረጋት? ሄኖክ ስዩም ተጓዡ ጋዜጠኛአንደማመጥም ግን ሳይነጋገሩ የተደማመጡ አያቶች ነበሩን ቋንቋችን ባቢሎን ሆኗል ምኞታችን ወንዝ ሳይሻገር ይበናልስማችን የሀገራችንን ስም አይመጥንም ተግባራችን ዕለት ጥሩ ከርሞ የከረፋ ይኾናል የሰለጠኑ አባቶች እንዳሉን ስንከራከር እንኳን ባልሰለጠነ መልኩ ነውየሰለጠነ ጦር አሸንፈናል ብለን ለመወያየት ያልሰለጠነ ስሜት ስላለን ድላችንን የዳግም ጦርነት ምክንያት እናደርገዋለን አድዋ የእኛ ድል በመኾኑ ተበድሏል ጃፓን እንዲህ ያለውን ድል ተጎናጽፋው ቢኾን ዛሬ የበለጠ የምትመነደግበት ምክንያት ይኾን ነበርእንዲህ ያለው ድል ልብ ያለው ትውልድ ወርሶት ቢሆን ሐይቁን አድርቆ ወንድሙን ጨፍጭፎ ወገኑን በድሎ ዘመኑን አጨልሞ አይኖርም ነበር አድዋ አባቶቻችን ድል ያደረጉበት ብቻ ሳይሆን ድሉን ቁም ነገር ለሌለው ትውልድ አውርሰው ያለፉበት ኩነት ነውዛሬ እነኛ ትንታግ ጀግኖች ቢኖሩ ከማን ጋር የሚፋለሙ ይመስላችኋል? ይሄን ትውልድ አይምሩትም ይሄ ትውልድ ከኢጣሊያ ወራሪ በላይ ሀገር አፍራሽ ነው በሰሩለት ሀገር መኖር ጣር የሆነበት ሀገር አፍራሽ ይሄ ትውልድ ከአንቶኖሊ በላይ ውል አፍራሽ ነው ደንብ አገላብጦ ቋንቋ ቀላቅሎ የሚያጭበረብር ይሄ ትውልድ እውነተኛ መስሎ የእውነት ካባ ለብሶ ሸፍጥ የሚወድ ነውእናም ያ ትልውድ እድሜ ሰጥቶት ከልጅ ልጆቹ ጋር አብሮ ቢቆም ከአድዋ የከፋ ጦርነት ከዚህ ትውልድ ጋ አድርጎ ከአድዋ የላቀ ድል ያስመዘግባል እርግጥ ነው እኛ ብቻ አይደለንም ወራሪን ያሸነፍን የእኛ ድል ድንቅ የሆነው ተንቀን ስለነበረ ነው በጨለማ ስለኖርን ነውከዓመታት በፊት እስረኛ አምባችን ድረስ መጥተው መውሰድ እንደቻሉ አስበው ዝቅ አድርገውን ስለገመቱን ነው እናም ድል አደረግን አይግባቡም ብለውን ነበር ተግባብተን ድል አደረግን አይችሉም ብለውን ነበር ችለን ሀገር ነጻ አወጣን ምን ዋጋ አለው? ራሱን ያላሸነፈ ትውልድ ምን ዋጋ አለው? ስሜቱን ያላሸነፈ ትውልድ የአድዋ ታሪክ ከምን ያስጥለዋል?ትንንሽ ምኞቱን የሠፈር መንግስትነት ቅዠቱን ድል ያላደረገ ትውልድ አፍሪካን ስላኮራ ታሪክ መስማት አለመስማቱ ምን ይረባዋል? የቀረችን የንስሃ እድሜ ናት ከቻልን ወደ መልካም የምንመጣባት በጨለማ ለመኖር መብራቱን ማጥፋቱ በቂ ነው ጨለማን ለመግፈፍና ብርሃን ለመፈንጠቅ ግን አበሳው ብዙ ነውአድዋ ጣሊያንን ድል ያደረግንበት ነው ጣሊያን የሚወዷትን ሀገራቸውን የተመኘ በመኾኑ ለመፋለም አላፈገፈጉም እኛስ ከጣሊያን ያነሳ ምን አደረግናት? በጣሊያን ዓይን እኛ የትኛው መንግስት የላከን ጠላት ሆነን ነው ለዘመናት የመዘበርናት መቶ ዓመት በዳዴ ያስኬድናት የሚያለቅሱ እናቶች አንገት የደፉ አባቶች ምድር ያደረግናት ማን የሚባለው የሩቅ ሀገር መንግስት በመንግስታችን ላይ ልኮን ነው? ልባችን ተሰብሮ አድዋን እናከብራለን ልብ የሚጠግነውን ድል ከልባችን ለማውጣት እንደክማለንየአባቶች መልካም ስራ ሰማይና ምድር ጽፈውታል ተከብረው አስከብረው ሀገር ኖሯቸው አልፈዋል በምድራቸው ተቀብረዋል የእኛን ጉድ ሳያዩ ያለፉ እድለኞች ናቸው ሀሳብ ያላቸው ብሩካን ናቸው እኛ ግን ከዚህ በታችን ነን ከከፍታችን ወርደን እንጦሮጦሱ ርቆናል የቪዲዮ ዘገባዎችና መዝናኛዎችን ለማግኘት ይጉብኙ ኢትዮ ጵያን የተመለከቱ የተለያዩ አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ዜናዎችን ለእንግሊዘኛ ለማንበብ
የዓድዋ ድል ያስከተለው ማህበረሰባዊ እና ስነ ልቦናዊ ዳና ማህበረሰባዊ ዳናከዓድዋ ጦርነት በፊት በተለያዩ የኢትዮጵያ ግዛቶች የሚኖሩት ህዝቦቿ እርስ በርስ የመገናኘት አጋጣሚውን ያገኙበት ጊዜ እምብዛም ነበር በተለምዶ ከሚደረጉ የንግድ ልውውጦች ባሻገር ከጫፍ እስከ ጫፍ ህዝብ በአንድነት ተምሞ በጋራ የቆመው ዓድዋ ላይ ነው እንደ ሬይሞንድ ጆናስ ገለፃ የዓድዋ ዋና መልዕክት ግልፅ ነበር ከሰሜን የሀገሪቱን ድምበር አቋርጦ እያደር ግዛቱን እያስፋፋ የመጣውን የጠላት ጦር ለመመከት ሀረሮች ወላይታዎች ኦሮሞዎች ሸዌዎችና ትግሬዎችን ይዞ የተመመው የኢትዮጵያ ጦር - በአንድ በኩል የጋራ ጠላትን በማወቅ ለጋራ አገር እንዲቆሙና ልዩነቶቻቸውን ወደጎን እንዲያደርጉ ሲያደርጋቸው - በሌላ በኩል በሚያርፉባቸው ቦታዎች ሁሉ በቀላል ሊቋረጥ የማይችል ማህበራዊ ትስስር መስርተው እንዲያልፉ አድርጓቸዋል - ወልደዋል-ተዋልደዋልለዚህም ይመስላል ገጣሚው ሰለሞን ደሬሳ ኢትዮጵያዊ እርስ በርሱ የተቀላቀለ መሆኑን ሲያነሳ በሴት አያቶቻችን ደጃፍ ማን እንዳለፈ ስለማናቅ እኔ ዘሬ የጠራ...ለማለት እንደሚያስቸግር ያተተው እውነትም ለዓድዋ ጦርነት የዘመተው የኢትዮጵያ ጦር ለ5 ወራት ከቤት ርቆ መቆየት ግድ ሲለው በመላመድ ትውልድ ፈጥረዋል ቤተሰብ መስርተዋል ይህ ከኢትዮጵያውያን አልፎ የኢጣሊያ ምርኮኞች በእስር ላይ በነበሩበት ግዜ እንኳ ከኢትዮጵያውያን ጋር ተላምደው ቤተሰብ መስርተው ኢትዮጵያዊ ሆነው እዚሁ ቀርተዋል ያ ድር ሲቀጣጠል ከርሞ ዛሬ ላይ ከልዩነታችን ይልቅ በአንድ የተጋመድንበትን ማሰሪያ ውል ጠንካራነት ያስረግጣል እርስ በእርስ በደም የተጋመድን ነንና ልበ ሙሉነትና አልበገር ባይነትዓድዋ የኢትዮጵያን አንድነት ከማስጠበቅም በላይ የነጮችን የቅኝ ግዛት ህልም ወደ ቅዠት የቀየረ ነበረ ከዓድዋ ድል ኋላ አንድም ሀገር ላይ የቅኝ ግዛት ወረራ አልተካሄደም ኢትዮጵያዊ የሆነ ስለኢትዮጵያዊነት ቢጠየቅ ወደ ሀሳቡ የሚመጣለት ገለፃ ጀግንነት ነው የጀግንነት መሰረቱ እምቢተኝነት ነው አልበገርም ባይነት ነው ይህ ስነ ልቦና በደማቁ የተፃፈው ዓድዋ ድል ላይ ነው የኢትዮጵያ መኳንንቶችና ህዝቡ ማንም ወራሪ ቢመጣ ማሸነፍ እንደሚችሉ እምነታቸው ፀንቷል ይህም የአሸናፊነትና ከሰው እኩል ነኝ የሚል የስነ ልቦና ልእልናን ለህዝቡ አጎናፅፏል ነፃነትና የጥቁር ወንድማማችነትየዓድዋ ድል የሰው ልጅ ነፃነት ክብር ከኢትዮጵያም አልፎ የመላው ጥቁር ህዝብ ወንድማማችነት እንዲያብብና የፓን አፍሪካ አፍሪካን የማዋሃድ እንቅስቃሴ በስደት ባሉ አፍሪካውያን እንዲጀመር አስተዋጽኦ አድርጓል ግፋም ሲል የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት በመላው ዓለም እየተቋቋሙ በጭቆና ይኖሩ ለነበሩ ህዝቦች ለነፃነትና ለእኩልነት እንዲታገሉ አነሳስቷል ይህንንም ተፅዕኖ ራይመንድ ጆናስ እንዲህ ይገልፁታል... የዓድዋን ድል ተከትሎ አፄ ምኒልክ የአፍሪካ የምንግዜም ታላቅ መሪነታቸው በደማቅ ቀለም አስፅፈዋል ድሉ የኢትዮጲያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን መፃኢ እድል የወሰነ ነበር በዚህም የአድዋ ጦርነት የኢትዮጲያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካም ጭምር ነው ምክንያቱም በቀጣይ መቶ አመታት የአውሮፓ የበላይነት እና አገዛዝ በአፍሪካ አክትሟል የዘመናዊት አፍሪካ የሉአላዊነት መሰረት ድንጋይ የጣለው ዓድዋ ላይ ነበር...
የአድዋ ድል የሁላችንም ነውአስገራሚዎቹ የሀዲያና የከምባታ ዘማቾች በአድዋበአፄ ዳግማዊ ምኒልክ የጦር አበጋዞች የከምባታና የሀዲያን ክልል ህዝቦችን ለማስገበርና በማእከላዊ መንግሥት ስር ለማጠቃለል በ1882 አም የተጀመረው የጦርነት ዘመቻ የተጠናቀቀው በ1885 አም ላይ ሲሆን ከሶስት አመታት በሁዋላ በተቀሰቀሰው የአድዋ ጦርነት ላይ ገና ከቁስላቸው ያላገገሙት የክልሉ ህዝቦች ለአገራቸው ነፃነትና ሉአላዊነት ስሉ በግንባር ቀደምትነት ተሰልፈው ተዋግተዋል ከፍተኛ መስዋዕትነትም ከፍለዋል የአድዋ ጦርነት የክተት አዋጅ በአፄ ዳግማዊ ምኒልክ የታወጀው በመስከረም ወር 1888 አም ነበር የክተት አዋጁ እንደታወጀ የጎጃም የቤጌምድር የወሎና የላስታ ህዝብ ከ300 እስከ 500 ኪሎሜትር ያህል የሸዋ የሐረር የባሌ የአርሲ የከምባታና ሀዲያ የሲዳሞ የጅማ የከፋ የወላይታ የወለጋና የኢሉባቡር ጦር ደግሞ ከ600 እስከ 1,000 ወይም 1,500 ኪሎሜትር ድረስ ርቀት ያለውን አገር በእግሩ እያቋረጠ ቀንና ሌሊት ሃሩርና ቁር ሳይገታው አቀበቱንና ቁልቁለቱን እየወጣና እየወረደ ያለማወላወል ለወሳኙ ጦርነት ወደሰሜን የጦርነት ግንባር እንደተጓዙ የአካባቢው ተወላጅ የሆነው የዲልባቶ ደጎዬ ፅሁፍ ያስረዳልየከምባታና የሐዲያ ክልል የገባር ገበሬ ሠራዊትን በዋና የጦር አበጋዝነት የመሩት በ1888 አም የክልሉ ገዥ የነበሩት የአፄ ምኒልክ ያክስት ልጅ የነበሩት ደጃዝማች በሻህ አቦዬ ነበሩ የከምባታን ዘማቾች የመሩት በወቅቱ የከምባታ ባላባት የነበሩት ቀኛዝማች ሞሊሶ ሄላሞ ድልበቶ ሲሆኑ ከእርሳቸው ጋር የዘመቱትን የከምባታ ገበሬ ጦረኞች የተሟላ ዝርዝር ለማግኘት ባንችልም 1 ላላምዳ መሎሮ ከሄጎ ጌዮጣ 2 አበጋዝ ትሮሬ ዋዶሌ ከቃጫ3 ጌንቤራ ግዴቦ ከደጋ ቀዲዳ 4 ወልደማርያም ባጂ ከገረምባ 5 መልከቶ ለታ ለቾሬ ከሰረራ መዝመታቸውን የከምባታ አዛውንት አረጋግጠዋል የሐዲያ ዘማቾች የተመሩት በፊታውራሪ ጌጃ ገርቦና በሌሎችም የሐዲያ መሪዎች እንደነበር ይነገራል በጽሑፍ የተቀመጠ መረጃ ስለሌለን የዘማቾቹን ብዛትና የስም ዝርዝር ለማቅረብ አልተቻለም በነበረው የዘመቻ ልማድ መሰረት ደጃዝማች በሻህ አቦዬ ወንድ ሴት ሳይባል በብዙ ሺህ የሚቆጠር የከምባታና የሀዲያን ገበሬ ሠራዊት ይዘው አድዋ ከደረሱ በሁዋላ ዳግማዊ ምኒልክ በሰጡዋቸው መመሪያ መሰረት ቀድመው የጠላትን ምሽግ የከበቡና ያስጨነቁ ጀግና ሰው እንደነበሩ ይተረካልደጃዝማች በሻህ አቦዬ የከምባታና የሐዲያ ጀግኖችን አስከትለው በአድዋ የጦር ሜዳ በአምባ ኪዳነምህረት ግንባር ከኢጣሊያ የጦር አዛዥ ከጄኔራል አልቤርቶኒ ጦር ጋር በተደረገው ብርቱ ትንቅንቅ በከፍተኛ ወኔና ጀግንነት ሲዋጉና ሲያዋጉ ሳለ በጠላት ጥይት ተመትተው የወደቁ ስመጥር የጦር ሰው ነበሩ በመሪ አዝማቻቸው ሞት የተቆጩት ጭፍሮቻቸው ከጦርነቱ ፍፃሜ በሁዋላ ብዙ የኢጣልያ ምርኮኞችን ለአፄ ምኒልክ በማስረከብ ፈንታ በበቀል መፍጀታቸው በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛልየአድዋ ጦርነትና የተገኘው አንፀባራቂ የኢትዮጵያውያን ድል መላውን አለም ያስደነቀ የታሪክ ክስተት ነበር ለዝንተአለም የሚቆይ ታሪካዊ ድል የአንዲቷ አፍሪቃዊት ነፃ አገር ኢትዮጵያ በኃይል ነፃነቷን ለመግፈፍ ግዛቷን ለመድፈርና በሕዝቦቿ ላይ የተገዥነት ቀንበር ለመጫን ባህር ተሻግሮ የመጣን ጠላት የካቲት 231888 አም አድዋ ላይ ድባቅ መታች ድል አደረገች ከሁለት ሺህ አመታት በፊት ሀኒባል በሮማውያን ላይ ካገኘው ድል በማያንስ ሁኔታ በአለም ያስተጋባውና ኢጣልያኖችን ያሸማቀቀው የአድዋ ድል አፍሪቃ በአውሮጳ ላይ እንዳገኘው ድል የሚቆጠር ታላቅ የተጋድሎ ውጤት ነበር ነውም የአድዋ ድል የከምባታና የሐዲያ እንዲሁም የሌሎች ክልሎች ህዝቦች ሁሉ የአንድነት የህብረትና የመስዋዕትነት ውጤት ከመሆኑም በላይ ማናቸውንም ተመሳሳይ ብሔራዊ ወይም አገርአቀፍ ችግርና ፈተና ለመቋቋምና በድል ለመወጣት የምንችለው እንደአድዋው ወቅት በህብረትና በአንድነት ስንቆም ብቻ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ታሪካዊ ድል ነው በሌላ አንፃር ብዙ ሺህ ኢትዮጵያውን ውድ ሕይወታቸውን የሰውበት ጦርነት ስለነበር ለበርካታ ሺህ ቤተሰቦች በመላ አገሪቱ የመሪር ሐዘን ወቀት እንደነበር መዘንጋት የለበትም ሆኖም ለነፃነት የተከፈለ ውድ ዋጋ ነበር ነፃነትም ምንኛ ውድ እሴት እንደሆነ ምንጊዜም መዘንጋት አይኖርብንም አዎን ነፃነት ነፃ አይደለምFreedom is not free.
ዋ! አድዋ! ሠዓሊ አምሳሉ ገኪዳን አርጋውዋ! አድዋ ያ ሑዳዴመድፍን ፈንጅን ደማሚት በጎራዴባሕር ተሻግሮ የሐበሻን ምድርቅኝ ሊገዛ ይሄ ደፋር!አንች አድዋ የበኩር ልጅላንቺ ውልደት ስንቱ ሲፈጅተፀንሰሽ ከውጫሌለደም መሬት ለአሞሌእርግዝናሽ ዘጠኝ ወሩዓመታትን ማስቆጠሩክፉውን ቀን ይዞ አሳሩከብቱ እረግፎ ባገር ምድሩሰው ሁሉ አልቆ በችጋሩበፋሽስት ሸር በእኩይ ግብሩከብት የሚፈጅ ደዌ ረጭቶበምን ታርሶ በምን ለምቶየገበሬው ሀብት ጠፍቶአከርካሪው ተመትቶየሚቀመስ እህል ታጥቶረሀቡ ሕዝቡን በልቶየግፍ ግፉ ተዘርዝሮዝም ይሻላል ምን ተቆጥሮበክፉው ቀን ራብ ደክሞያለቀ ሕዝብ በአዋጅ ተሞበዚያ ድቀት ተጎድቶአፈር ልሶ ግድ ተነሥቶአይቀር ነገር የሀገር ጥሪነፍሱ የሷ እሱ አኗሪጉልበት ሆኖት የሀገር ፍቅሩአስቆጥቶት መደፈሩገሰገሰ ወደ አድዋጠላት ሊግት የሞት ጽዋበአምባ አላጌ አርጎ ድምስስበመቀሌም እንዳ ኢየሱስአድዋ ላይ ከግንባሩሊሞሻለቅ ሲተም ጦሩእንደ ሙላት ደራሹ ጎርፍሲያስገመግም ጠላት ሊቀስፍከተፍ ሲል ፊት ለፊቱጥሊያን ራደ ልብ አጥቶባለ የሌለ መሣሪያ አጉልእያስጓራ ሲከላከልበመድፍ አረር በመትረየስብዙ ሲወድቅ ሲሠዋ ነፍስጠጋ ሲባል ወደ ምሽግሌላ አሳር ምን ይደረግ?በስል ችንካር በውጋቱበጠርሙስ ጦር በስለቱምሽግ ማዶ በተከለውአርበኛውን እንዲያስቀረውጠርሙስ አልፎ የፈንጅ ንጣፍ ደማሚትፋኖ የሚፈጅ እንደፍያ ባዶ እግር ቢቀረደድቢሸረከት ቢጎራረድማን ተሰምቶት ለማን ታውቆ?በፈንጅውም ረግፎ አልቆሊነሣ ይሻል ሞቶም ወድቆበወደቀው ተረማምዶምሽግ ሰብሮ ጥሶ ንዶበጠላት ላይ ማት አውርዶቆርጦ ሲጥል አንገት ጎርዶበፉከራ ቀልቶ አጭዶሲፈጅ ሲማርክ ቆልቶ አሳዶብቻ በሀገር በሕዝብ ፍቅርበሚፋጀው እንደ ገሞርአንች የረፋድ የድል ፀሐይየወጣሽው አድዋ ላይከአባትሽ ከምኒልክድባቅ መትቶ ካገባው ልክከጣይቱ ከእናት ኩሩፋኖዎቹ እያጋፈሩአድዋ ላይ ከአፈሩበቅዱሱ ጊዮርጊስ ለትተራድቶሽ ተርፈሽ ከሞትሰዓቱ ሲደርስ መወለጃሽበጭንቅ ምጥ የተወለድሽበሰው አጥንት በሰው ልጅ ደምየታረስሽው የዓለም ሰላምየሐበሻ ዘውድ የድል ማማበአጥንት ዕዳ በደም ጉማምታስከፍይ ቃል ሲሰማያችን ገልቱ ከንቱ ሮማአድዋ ቅኔ አድዋ ዜማየምትማርክ ምትስማማለሰው ልጅ ልብ ያላት ግርማየአውሬን ልብ ምታደማበአፍታ ፍልሚያ ፈጣን ሽኝትወዲያው ብልት እዚያው ጥጥትበአርበኛ ወግ በፋኖ ደንብሳይገመት ሳይታሰብነጭ በጥቁር በግፍ ገኖበጨካኝ ክንድ ይዞ አፍኖጥቁሩ ሲኖር ተኮንኖመገልገያ ዕቃ ሆኖአሜን ወዴት አለሁ ብሎአንገት ሰብሮ ተገልሎበምድሪቱ በመላ ዓለምበግፍ ሲኖር አጥቶ ሰላምለነጭ ተድላ ጥሮ ማስኖእሱ እንደሚያንስ ከልቡ አምኖቅስም ሐሞቱ ነኩቶ ፈሶመራር ሐዘን ልቡ ውስጥ ነግሦሲኖር ዘወትር ቀንበር አዝሎአድዋ ላይ የድሉ አውሎአሽቀንጥሮ ሸክሙን ጥሎነጩን እባብ ላይድን ገሎአነሣለት ከስር ነቅሎአስበርግጎ አስደንብሮፈነቃቅሎ ጥልቅ ሰርስሮእናም ዓለም ተገደደውዳቂ ሐሳብ በግድ ካደአዲስ ታሪክ ተሰነደየተጠላው ተወደደሰው መሆኑን የአዳም ዘርከነጭ ቢጫ ከቀይ ፍጡርእንደማያንስ ምን ቢጠቁርአረጋግጦ ቆመ በክብርእድሜ ለዚያች የድል ፀሐይለበራችው አድዋ ላይየባርነት ሰንሰለቱንበጣጠሰ እግር ብረቱንተቀዳጀ ነጻነቱንቀበረለት ባርነቱንየሀገሩ የመብቱራሱ ሆነ ባለቤቱዕድሜ ለዚያች የድል ፀሐይለበራችው አድዋ ላይየምዕት ዓመታት ጣር ጨለማተወገደ ድል ተሰማያች ፀሐይ የድል ጮራደማቅ ጸዳል የገድል አውራየከበረች ስጦታ ናትምንም ነገር የማይተካትከሐበሻ ሕዝብ ለጥቁር ዘርለተገፋው ለበላ አሳርየካቲት 19 2007ዓ.ም.ሠዓሊ አምሳሉ ገኪዳን አርጋው
የዓድዋ ድል በዓለም አቀፍ ታዋቂ ሰዎች እና ምሁራን ዕይታ::ባሕር ዳር የካቲት 212011 ዓ.ምአብመድ የዓድዋ ድል 120ኛ ዓመት ዝክረ በዓል ሲከበር የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝደንት ታቦ ምቤኪ የዓድዋ ድል በዓልን ማንኛውም አፍሪካዊ የኔ ነው በሚል ስሜት ማክበር እንዳለበት ተናግረዋል አፍሪካውያንን አሁንም ወደፊትም አንድ የሚያደርግ እሴት መሆኑንም ጠቁመዋል የቀድሞው ፕሬዝደንት ገጠመኛቸውን ሲያወሩም በአንድ አጋጣሚ ሦስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደ እኔ መጡ ክቡር ፕሬዝደንት በትምህርት ቤት የምንማረው ጥቁሮች የባሪያ ንግድ ቅኝ ግዛት አፓርታይድ እና ሌሎች ጥቃቶች ሰለባዎች እንደነበሩና አሁንም በእጅ አዙር ያው ነው እየተባልን ነው አፍሪካውያን የሠሩት በጎ ነገር ወይም ከተጠቂነት የተላቀቁበት ታሪክ የለም ወይ? ይህ መጥፎ ስሜት ይፈጥርብናል ከዚህ መጥፎ ስሜት መውጣት አልቻልንም አሉኝ በወቅቱ ድንጋጤ ነው የፈጠረብኝ በትምህርት ሥርዓቱ የዓድዋ ድልን የመሳሰሉ የአፍሪካውያንን በጎ ታሪኮች በአግባቡ ማካተት ትውልዱን ከመሰል ችግር ያድናል ነበር ያሉትበዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ራይሞንድ ጆናስ የዓድዋ ድል በተሰኘው መጽሐፋቸው የዓድዋ ጦርነት ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ድልን ያቀዳጀ ለጣሊያን ደግሞ የሽንፈት ጽዋን ያስጎነጨ ነበር ሲሉ ገልጸውታል ጣሊያን ዘመናዊ እና እስከ አፍንጫው የታጠቀ ጦር ይዞ ቢመጣም ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ወኔና መሰዋዕትነት ጦርነቱን ማሸነፋቸውን መስክረዋል ፕሮፌሰሩ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውንና የአፍሪካን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ቀጣይ የፖለቲካ አቅጣጫ የቀየረ ነበር ብለዋል በሙያዊ ምሥክርነታቸውበታሪክ ጥቁር ሕዝቦች ነጭ ወራሪን እስከመጨረሻው ድል ያደረጉበት የመጀመሪያው ክስተት ነበር አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆኑ አሜሪካውያንን ጨምሮ ሌሎች የቅኝ ግዛት ሰለባ ሀገራት ጸረ ቅኝ ግዛት ትግል በዓድዋ ድል ምክንያት በተፈጠረ መነሳሳት ጀምረዋል ቅኝ ገዥዎችም ከዓድዋ ድል በኋላ የግዛት ማስፋፋታቸውን ገትተዋል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ጆናስእንግሊዛዊው ጸሐፊ ፖል ሄንዝ በበኩሉ ጊዜ ሲከዳ የሚል አንድምታ ባለው መጽሐፉ የዓድዋ ድል ለጥቁር ሕዝቦች የኩራት እና የትግል ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ደማቅ አሻራ የጣለ ነው ብሏልከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ አንስቶ በሁለት የተለያዩ የምርጫ ዘመናት እንግሊዝን የመሩት ሰር ዊንስተን ቸርችልም ስለዓድዋ ድል ጽፈዋል የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም የዓድዋ ጦርነት ተካሂዶ ጣሊያን በኢትዮጵያ ታላቅ ሽንፈት ደረሰባት ይህም ሌሎች ሀገራት ላይ በሁለት መንገድ ተጽዕኖ አሳድሯል በአንድ በኩል አውሮፓውያን በሰሜን አፍሪካ የነበራቸው ክብር ኮስምኗል በሌላ በኩል ደግሞ ጣሊያን በአውሮፓ ኅብረት ያላት ተሰሚነት በእጅጉ ወርዷል ነበር ያሉት ቸርችልአንዳንዶች ሰር ዊንስተን ቸርችል ስለ ኢትዮጵያ ድል ማድረግ ሳይሆን ስለ ጣሊያን ድል መሆን አጽንኦት ሰጥተው ጽፈዋል ቢሉም ዓድዋ ግን ብዕራቸውን ለመምዘዛቸው ምክንያት መሆኑ ሀቅ ነበርኢትዮጵያዊው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው የዓድዋ ድል ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ተሰሚነቷ እንዲጎላ እና ትኩረትን እንደትስብ ማድረጉን አስፍረዋልሌሎች ጸሐፊያን ምሁራን እና ታዋቂ ሰዎች ስለ ዓድዋ ድል ምን አሉ? የወደዳችሁትን አካፍሉን
የአድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ፈተናዎችን በጋራ ትግል በማለፍ እዚህ ለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ኢር ታከለ ኡማየአድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ፈተናዎችን በጋራ ትግል በማለፍ እዚህ ለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ኢር ታከለ ኡማ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ የአድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ፈተናዎችን በጋራ ትግል በማለፍ እዚህ ለመድረሳችን አንዱ ማሳያ መሆኑን ገለጹኢንጅነር ታከለ ኡማ 123ኛው አድዋ ድል አስመልክቶ በአዲስ አበባ በሚከናወነው ፌስቲቫል ዙሪያ ባስተላላፉት መልዕክት በዓሉ ኢትዮጵያውያን ፈተናዎችን በጋራ ትግል በማለፍ እዚህ ለመድረሳቸው አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋልአባቶቻችን ከወራሪ ቅኝ ገዢዎች ጋር ተፋልመው ደምና አጥንት ገብረው በነፃነቷ የምትኮራ አገር ባለቤት አድርገውናል ብለዋልኢትዮጵያ ይህን ድል የተቀዳጀቸው በመሳሪያ ብልጫ ሳይሆን÷ በሞራልና በሃሳብ ልዕልና በፍቅርና በህብረት መሆኑን አስገንዝበዋልበዚህም የአድዋ ታሪክ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን÷ የመላው አፍሪካ ወንድሞቻችን ጭምር እንደሆነ ለዓለም መድረክ በተገኙ አጋጣሚዎች ሁሉ አዲስ አበባ የማስተዋወቅ ኃላፊነቷን እንደምትወጣም አረጋግጠዋልየድል በዓሉን ወንድምና እህት ኢትዮጵያውያን በአዲስ አበባ በሚከናወነው ፌስቲቫል በጋራ ስናከብር የአባቶቻችን ክብር የሚገለጥበት የአድዋን ቱሩፋቶች የምንቋድስበት ተመራጭ ዓለማቀፋዊ መድረክ በመሆን በቀጣይነት በጋራ ለመስራት መደላድል ይፈጥራል ብለዋልበአንድነትና በፍቅር አንድላይ ሆነን የምንዘምርበት የምንጫወትበትና እየተዝናናን ሃሳብ የምንለዋዋጥበት ፌስቲቫል መሆኑንም ነው የተናገሩትበሀሳብ የረቀቀ በእውቀት የበሰለና በክውን ጥበባት ትውልድን ከትናንት ጋር በማነጋገር የማንነት ስብዕናውን እንዲፈትሽ ለነገ የምትተርፍን ሃገር ለመስራት ከራስ ጋር ለመመካከር እድል የሚፈጥር ፕሮግራም መሆኑንም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል
የቡሄ እለት ያበደ ሁሌ ሆ እንዳለ ይኖራል እንዲሉ የአድዋ ድልና የአድዋ ጀግኖች ስም በተጠራ ቁጥርየቡሄ እለት ያበደ ሁሌ ሆ እንዳለ ይኖራል እንዲሉ የአድዋ ድልና የአድዋ ጀግኖች ስም በተጠራ ቁጥር የሚያቃዣቸው በርካቶች ናቸው ስለምንሊክ ለምትጠይቁኝ እኔም እንደገጣሚው እንዲህ እላችኋለውምኒልክ ማለፉን የምትጠይቁኝፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝእነሆ አሁንም የአድዋ ድል የሚከበርበት ቀን ቀርቧል ይህንንም አስመልክቶ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ አጭር የሕይወቱና የጽሑፉ ታሪክ ገጽ 76100-103 ከተሠኘ መፅሐፍ ላይ ያገኘሁትን መውድሠ ጀግኖች ግጥም የአድዋ ክብረ በዓል መቀበያ አድርጌ እዚህ አኑሬዋለውአጥንቱን ልልቀመውአጥንቱን ልልቀመው መቃብር ቆፍሬጎበናን ተሸዋ አሉላን ተትግሬስመኝ አድሬያለሁ ትንትና ዛሬጎበናን ለጥይት አሉላን ለጭሬተሰበሰቡና ተማማሉ ማላአሉላ ተትግሬ ጎበና ተሸዋጎበና ሴት ልጁን ሊያስተምር ፈረስአሉላ ሴት ልጁን ጥይት ሊያስተኩስአገሬ ተባብራ ታልረገጠች እርካብነገራችን ሁሉ የእንቧይ ካብ የእንቧይ ካብአራቱ ጉባኤ ይነሡልንናመኮንን ደረሶ አሉላ ጎበናአገራችን ትማር አሁን እንደገናጎበናከፈረስህ ጋራ ተነስ እንደገናዮፍታሔ ንጉሤ 1927 የኢትዮጵያ ድምፅ ?ደግሞ አንድ ጊዜ ስሙኝ ልንገራችሁታላቆቹ ልጆች እንዳይሥቁባችሁአብረውን ነው ያሉ ሞቱ እንዳይመስላችሁገና ሳስባቸው ልቤን ጨነቀውእስኪ ስማቸውን በተራ ላንሣውይህ የልብ እመሜ ጥቂት ቢሻለኝቶሎ ና ቴዎድሮስ አንተ ደግፈኝበግራ በቀኝህ ጠላት መቶብሃልበፊትም በኋላ ደመኛ ከቦሃልበል ተነሣ ታጠቅ ሞት ባንት ያምርብሃልአሁንም ሙትልኝ ታጠቅ እንደገናመቼም መች አይገድህ ሞት በጅህ ነውናቴዎድሮስን ልጄን ማንም አይደፍርህአንት ካልሞትህ በስተቀር ራስ በራስህዮሐንስን ጥሩ እሱ ይያዘኝእስኪ ካሣን ጥሩ በል አንተ ያዘኝቴዎድሮስን ወስዶ ከሣ አንተን ሰጠኝእጅግ ደስ ይለኛል ያንተ ስም ሲነሣየቁና ዐፈር ንፉግ አንተ ነህ ወይ ከሣዮሐንስ ካሣህን ማን ሊችለው ነውከዘውድ ይልቅ ሞትክን አንት የመረጥኸውእንዳንት ለድርጎ አፈር ንፉግ ሰው የለምበደምበር ላይ ብትሞት አይደነቅምበል ዕረፍ ዮሐንስ ጥራው አሉላንያንተ ግርፍ ነውና ያውቃል ዐመሌንይኸው ነጋ አሉላ ምጥዋ ገሥግሥአልወድም ባዕድ ሰው ከባሕር መለስክፉ አረም በቀለ በምጥዋ ቆላአሁን ሳይበረክት አርመው አሉላተኩላው ብዙ ነበር ምጥዋ ያለውበነጋ በነጋ አሉላ አረደውእነዚህ ጣሊያኖች ሙግት አይገባቸውአሉላ አነጣረህ ቶሎ አወራርዳቸውአሉላ ፈረስህ እንዴት ሆዳም ነውእንኳን ወንዛ ወንዙ ባሕርም አይገታውእንዴት ነህ አሉላ የተዳሊ በርአምስት ሺህ ገዳይ በአንድ ቀን ጀምበርክፉ ህልም አይቼ ሌት አልተኛሁኝአሁን ግን ተነጋ ጥቂት አረፍኩኝአሉላ አባ ነጋ መንገሻን ጥራውያባቱ ነውና ጋሻዬን ስጠውአይከፈት በሩ መግቢያ መውጫችንበል ተንሥ መንገሻ ግጠም በርበሩንይህንን ጎሽ ጠላ ማንም አይቀመሰውመንገሻ ዮሐንስ አንተ ገፍተውዳኛው ወዴት ሄዷል እስኪ መጥተህ እይአኩስም መንገሻዬ እስኪያዝ ነወይምኒልክ ዝም አልክ ወይ ተኩሎች ከበውኝረብልኝ ወዲያ እንዳይጮሁብኝይህ ጫሂ አይጩህብኝ ሰው አይታወክያላንት ዳኛ የለም ዳኛው ምኒልክዐድዋ ላይ ጣሊያኖች የዘፈኑ ለትምኒልክ ጎራደህ ወረደ ባንገትምኒልክ ወንድምህ እንዲህ ፈጣን ነውመሪው አንተ እያለህ መኮንን ቃኘውየጣሊያኖች ድርድር በገና ቢያምረውመኮንን ወንድምህ በሾተል ቃኘውእጅግ አንዣበበ ልናየው ፈራንልንገርህ ምኒልክ ሰጉድ ጋሻህንወንድምህን መኮንን የሚለው ሰው ማነውእኔስ ባስተውለው ድንግል ባላገር ነውበጣም ያሣፍራል ባሌጌ እንዳየኸውይህ ራስ መኮንን ውብ ገበሬ ነውአላጌ ላይ ዘርቶ መቀሌ ዐጨደውዐድዋ ላይ ከምሮ መረብ ላይ ወቃውዐድዋ ገበያ ላይ ከጎንህ ነበርሁእኔም እኮ እናትህ መልካም ገበየሁክብር ለመኮንን ሸመታ ረከሰከዳጉሳው ይልቅ ጥሩ እህል ታፈሰእነዚህን በጎች ምን በታተናቸውተኩላው እጅግ በዝቷል አንት ኃይሌ አንድርጋቸውሁሉም መንገድህ ነው መሪም አያሻህአንተ አሠማራቸው አቦዬ በሻህምኒልክ ዐድዋ ላይ አጥብቀህ ጠራህእስከ አውሳ በር ድረስ ተሰማ ድምፅህዋናውስ በሽታ ምንም አልጎዳቸውካገገሙ ወዲያ ግርሻ ገደላቸውዳርጌና ጎበና መከዳ እያሉህከዙፏንህ ዳኛው ማናነቃንቆህበመድፉ ጢስ ብዛት ሲጨልም አገርጎራደህ አበራ ከዳር እስከ ዳርእንዳይጠፋኝ ስምህ እንዳልዘነጋህአንተ ወልደ ጊዮርጊዘስ ዘወትር ላውሳህመድፋቸው ተርቦ አፉን ከፍቶ ቢያየውአባተ አባ ይትረፍ ጥይት አጎረሰውብዙ ሰው አለቀ አድዋ ላይ በሰይፍለምሳሌ እንዲሆን አንድ ሰው ይትረፍምኒልክ ጥራልኝ ቶሎ ጣይቱንእኔን ለመደገፍ ትችል እንደሆንምነዋ ተኮሰኝ ጣይቱ ገላሽእንዴት ነደሽ ይሆን አድዋ ላየሽእኔም በጣም ሞቀኝ አጥብቀሽ ተኩሽገና ጣይ ስትወጣ እንዲህ ያላበውቀትርማ ቢሆን የት ሊገባ ነውወሌ የጣይቱን አይቶ ብርታቷንውሃም አልመረጠ ጠጣው ድፍርሱንፈክራ ፈክራ ምንም አልቀረችአልፋ ከሴቶቹ ወንድ አሰለፈችመድፉ መትረየሱ ምንም አልጎዳቸውእንደ ጎመን ዝልቦ ጣይ አዛለቻቸውሠዓሊ አገኘሁ እንግዳ 1928
የካቲት ማለት ግንቦት አይደለምየካቲት 23 ግንቦት 20×××አንዳንድ ወዳጆች አሉኝ አድዋ የካቲት 23 የድል ቀንን እንድምንም ለመቁጠር የሚዳዱ በነጻነትና በባርነት መካከል ልዩነቱን ያለማወቅ ወይም ላለማወቅ የመፈለግ አባዜ የተጥናዎታቸው አድዋ ወይም የካቲት ሀያ ሶስት ወይም የድል ቀን ሲባል ስራ አጥተን እናውራው ወሬ ጠፍቶን እናነሰው ጉዳይ አጥተን ዝም ብለን የምንባክን ይመስላቸዋልግንቦት 20 ወይስ የካቲት 23የኢህአዴግ ድል የአፍሪካ ድልስለግንቦት 20 ድል ሳስብ የሚታየኝ ወንድሙን ለመግደልየታጠቀ ወታደር በር እያንኳኳ ወንድሙን ሲገል ነው ከማንይሆን ነፃ ያወጡን? ምን ይሆን ግንቦት 20? ለምን ይሆንየመድፉ ጩኸት? ምንድነው ደርግ በመውደቁ የኢትዮጵያስጦታ?ግንቦት 20 እንዲደምቅ የካቲት 23 እንዲረሳ ለምንተፈለገ? የምኒልክ ሐውልትን ጥሎ የአኖሌን ሐውልትመገንባት ለምን ተናፈቀ...?አድዋኢትዮጵያውያን ለአፍሪካዊያን የሞቱለት የብርሀን ቀን!!ጥቁር የድል በትር እንዳለው የታየበት የትንግርት ቀን! አድዋአድዋ አድዋ ...ኢትዮጵያውያን እንዲረሱት የሚፈለግ አፍሪካውያንየሚናፍቁት የድል ቀን!!ምኒልክ;ጣይቱ;ባልቻ አባ ሳፎ ;ሐብተጊዮርጊስ ዲነግዴ...ታሪክ መቼም የማይረሳቸው ጀግኖች!!!አድዋ የአፍሪካውያን የድል ቀባርነትን አለማወቅ አንድ ነገር ሁኖ በባርነትና በነጻነት መካከል ልዩነቱን ማስታወስ ግን ግድ የሚል ይመስለኛል ባርነት ስንል እኮ ፈጣሪ የሰጠን ሰውነት ብቻ ሳይሆን የጸጋ አምላክ የመሆን ነጻ መብታችን ተክዶ ወደ እንስሳ መጠጋት ወይም እንስሳ መሆን ነው ባርነት ስንል እኮ እጇ ለስለስ ያለችውን ፍቅረኛህን መንገድ ላይ ቀዛቃዛውን ንፋስ ልትቀበል ስትወጣ ፍቅረኛህን አንዱ ጎረምሳ ጣልያኒያዊ ለልጆቹ እቃ ገዝቶ እንደመጣ አባት ተቀብሎ አንተን ሲሸኝህ ባርነት ማለት ፈታ ብለህ እየተጫወትክ ባለህበት አንድ ነጭ ዘው ብሎ ሲገባ ስቅቅ ብለህ ከተቀመጥክበት ስትነሳ ሀበሻ አግብተህ ድንቡሽቡሽ ያለች የጠይም ቆንጆ ስትጠብቅ ክልስ ሆና ስታርፈው ምን ታመጣለህ ስትባል ነውባርነት ከዚህም በላይ ነው እህቴ የፈለግሽውን ለብሰሽ በመንገድ መሄድ የማትችይበት ማንም አንቺን ከመሬት ተነስቶና አሰኘሽኝ ብሎ የመድፍር ነጻነት ነጭ በመሆኑ የሚያገኝበት መርጠሸ ሚስት ሳይሆን ተገደሽ የጭን ገረድ የምትሆኚበት ፈልገሽ የምትለብሽው ሳይሆን ማንም ነጭ ሲያይሽ እንዴት ልታምሪው እንደምትችዪውን አለባበስ በግድ የምትለብሺበትነውባርነት ማለት ማንም ነጭ ደስ ስላለው በመኪና ስለሚገጭህ ማንም ሰውነቱ የነጣ ሰው ስላስጠላኽው ብቻ በምድር ላይ የመኖር ቀንህን የሚወስንበት እንዲሁ አይነ ውሃህ ስላስጠላው ምራቁን የሚተፋብህ እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ እዘለኝ የሚልህ እንደ ቀላል ነገር ሚስትህን ዛሬ ከኔ ጋር ነች ብሎ እንደ ቴክ አዌይ የሚወስድብህ ማለት ነውስለዚህ የካቲት 23 ከየካቲት 25 ጋር አታምታቺው አድዋን ከግንቦት ሃያ አታምታቱት የፍቅረኛ ቀን ከድል ቀን አታጋጨው ያ ሌላ ነው ይሄ ግን አድዋ ነው አድዋን ክምንም ጋር አታምታታው አድዋን ከምንም ጋር አታጋጭው የካቲት ማለት ግንቦት አይደለምየካቲት ሃያ ሶስት ላይ አያት ቅድመ አያቶችህ ደምና አጥነት የከፈሉት አንተ ዛሬ ደረትህን ነፍተህ እንድትንቀሳቀስ እንጂ ነጭ ገዝቶኝ ቢሆን ኖሮ ወይኔ? ብዙ አስፋልት ይኖረን ነበር ወይኔ ስንት ፋብሪካ ይገነባ ነበር እያልክ እንድትላዝን አይደለምበቃ አያት ቅድም አያቶችህ አስፋልት የምታነጥፍበት መሬት ሸልመውሃል ፋብሪካ የምታቆምበት አሸን ቦታ ሰጠውሃል ዲሞክራሲ የምታሰፍንበት ባርነት ያልለመደ አእምሮ አስተርፈውልሀል ልዩነትን ሳይሆን አንድነት አሳይተው ባንድነት ሀገር አስረክበውሀል ስለዚህ አታምታታው አድዋ ከምንም ጋር አይምታታም
124ኛው የዓድዋ ድል በዓል በዓድዋ ተከበረMon, Mar 02, 2020በአረጋዊ ሰለሞን 124ኛው የዓድዋ የድል በዓል የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በዓድዋ ተከበረበበዓሉ ላይ የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ደብረ ጽዮን ገሚካኤልን ዶር የፌደሬሽን ምክርቤት አፈጉባኤ ኬርያ ኢብራሂም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ሂሩት ካሳው ዶር ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲሁም ከተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች እና ከዓድዋ ከተማ የመጡ በርካታ ሰዎች ተገኝተዋልእንዲሁም የሃይማኖት አባቶች የሃገር ሽማግሌዎችና መዘምራንም በመርሃ ግብሩ ላይ ሽለላና ቀረርቶ አቅርበዋልዓድዋየአንድነታች ድርና ማግ በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ባለው በዓል ላይ የክተት አዋጅን የሚያወሳ ሙዚቃዊ ትያትር ቀርቧልጉዞ ዓድዋ 7 ተጓዦችም በስፍራው ደርሰው ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋልከጉዞ ዓድዋ ተጓዦች በተጨማሪም ሌሎች ተጓዦችም በስፍራው ደርሰው አቀባበል ተደርጎላቸዋል
123ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም መጠናቀቁን ፓሊስ አስታወቀOn Mar 2, 2019 705አዲስ አበባ የካቲት 23 2011 ኤፍ.ቢ.ሲ በአዲስ አበባ ከተማ የተከበረው 123ኛው የአድዋ ድል በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የከተማ ፓሊስ ኮሚሽን እስታወቀየኮሚሽኑ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ በሚኒልክ አደባባይ እና በመስቀል አደባባይ በደማቅ ስነ ስርዓት የተከበረው የድል በዓል ሰላማዊ ሆነ መጠናቀቁን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋልበዛሬው ዕለት በከፍተኛ ሁኔታ የተከበረው 123ኛው የአድዋ ድል በዓል ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ ሰላማዊ እንደነበረ አንስተዋልይህ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እና ለሁሉም የፀጥታ አካላት በኮሚሽኑ ስም ምስጋና አቅርበዋልበተመሳሳይ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ በዓሉ በደማቅ ሁኔታ እንዲከበርና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላስቻሉ ሁሉም አካላት ምስጋና አቅርበዋል
ያድዋ ስንኞች በዕውቀቱ ስዩምየቅዱስ ቫላንታይንን በአል ምክንያት በማድረግ ስለ አድዋ ጦርነት እንጽፋለንየቀድሞ ሰዎች የቃልና የዜማን ኃይል አሳምረው ያውቃሉ ስለዚህ ሁሌም ወደ ጦርሜዳ ከመሄዳቸው በፊት አዝማሪ እና አረሆ ይመለምላሉ ባድዋ ጦርነት ብዙ አዝማሪዎች ማሲንቆ ታጥቀው ዘምተዋል አንዳንዶች ለውለታቸው ከድል በኋላ ማእረግና መታሰቢያ ተበርክቶላቸዋል ከኒህ አዝማሪዎች መካከል ጣዲቄ የተባለችው ስመጥር ሴት አዲሳባ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሠፈር በስሟ ተሰይሞላት ነበር በኀይለሥላሴ ዘበን የቸርቺል ጎዳና ሲነጠፍ በቦታው የነበረው የጣድቄ መታሰቢያ ሳይደመሰስ አልቀረም አሁን ያዝማሪ አጣዲቄ ሉባንጃ ግባ የቸርቺል ትምባሆ ውጣ እላለሁ በቅርቡ ለሁለተኛ ጊዜ ታትሞ በሚወጣው ከአሜን ባሻገር በተባለው መጽሐፌ ጣዲቄን ከትቢያዋ ላስነሣት ሞክርያለሁይቺ አረፍተነገር እንደ ማስታወቂያም እንደ ጉራም ትመዝገብልኝበጊዜውከጠላት ጎን ተሰልፈው ተናዳፊ ግጥም ወደ ወገን ጦር የሚወረውሩ አዝማሪዎችም ኣልጠፉም ለምሳሌ አንዱ የጀኔራል ባራቴሪ ኣዝማሪ የጣልያንን ሠራዊት ታላቅነት በማካበድ የሚከተለውን ተጎርሯልዥኔራል ባራተሪዥኔራል ባራተሪማን ይችልሃል ያለ ፈጣሪበዕውቀቱ ስዩምባንዳው አዝማሪ እንደገመተው ሳይሆን ቀርቶ የጥልያን ጦር እንደማሽላ እንጀራ ተፍረከረከ ኩሩው ጄኔራል ባራቴሪም ተማረከ በምርኮው ማግስት ዳግማዊ ምኒልክ ድንኳን ተይዞ ቀርቦ ምን አባቱ አቅብጦት እንደተዋጋ ሲጠየቅ በቁጣ የተሞላ ምላሽ ሰጠ ንጉሡም ቁጣ ትናንት የጦርነቱ ቀን ነበር እንጂ ዛሬ ምን ይረባል ብለው ስቀው አሰናበቱት በድሉ ማግስት የዘመኑ ጥቁር ሆሜሮች የጦርነቱን ውሎ በቅኔ ዘግበውታል አንዱ የሚከተለውን ብሏልሰላም ለአፉከ ለፈጣሪ ዘየአኩቶዘኢይትናገር ስላቀ ወኢይነበብ ከንቶንጉሠ ነገሥት ምኒልክ ለኢትዮጵያ ማህቶቶኀልቀ ማንጀር ወስእነ ፍኖቶዤኔራል ባራቴሪይ ሶበ ገባ ደንገጸ ኡምበርቶትርጉሙ እንደሚከተለው ግድም ነውሰላም ላንደበትህ ለሚያቀርብ ለእግዜር ምስጋናዘበት ስላቅ ከንቱ ወሬ መናገርን መች ያውቅናንጉሠ ነገሥት ምኒልክ የኢትዮጵያ መብራት ፋናተጨነቀ ማጆር እግሩ ዛለ በጎዳናደነገጠ ኡምበርቶ በባራቴሪ ምርኮ ዜና ቅኔይቱ ከወገቧ በላይ ውዳሴ ከወገቧ በታች ዜና እወጃ ናት በቅኔይቱ ማጆር ተብሎ የተጠቀሰው አምባላጌ ላይ ወድቆ የተሰለበው ማጆር ቶሌዚ ሲሆን ደነገጠ የተባለው ኡመበርቶ የጣልያኑ ንጉሥ ነው ባለቅኔው ስለ ጣልያን ሁኔታ ነቄ ነበር ማለት ይቻላልያድዋ ድል የብሄርብሄረሰቦች ድል ነው ይላል የሰባተኛ ክፍል ይሁን የስምንተኛ ክፍል የሲቪክስ ማስተማርያ መጽሐፍ እውነት ነው !ያም ሆኖብሄርብሄረሰቦችን ባንድ ወታደራዊ ሥርዓት ጠምዶ ወደ ድል የመራቸው ዋናው የጦር አዝማች ምኒልክ ነበርበጊዜው ለዋናው የጦር አዝማች የውዳሴ ግጥሞች ጎርፈዋል አንድ የሸዋ ኦሮሞ አዝማሪም እንዲህ ብሎ እንደ ዘፈነ ተመዝግቧልMootin baar gamaa ceeeDaanyoo faranji reebe.አዛማጅ ትርጉም በስለሺንጉሥ ወንዙን ተሻገረውዳኘው ፈረጅኑን ወገረውባድዋ ጦርነት ብዙ የወገን ወታደር አልቆ ሜዳ ላይ ቀርቷል ይህን በትካዜ ያስተዋለ አዝማሪየዳኘው ኣሽከሮች እነሞት አይፈሬርግፍ ርግፍ አሉ እንደ ሾላ ፍሬብሎ አንጎራጉሯልእንደ ሾላ ፍሬ ቀይ ለብሰው ከረገፉት አንዱ ኣሠላፊ ገበየሁ የተባለ ወታደር ነበር ቸሩሊና ዴልቦካ የተባሉ የታሪክ ጸሀፊዎች አሠላፊ ገበየሁን ከስመጥሩ ፊታውራሪ ገበየሁ ጋር እያምታቱ ጽፈዋል ቼሩሊ አሠላፊ የተባለውን ማእረግ አሳላፊ ብሎ በመረዳት ፊታውራሪ ገበየሁ የንጉሡ አሳላፊ cup-bearer ነበር በማለት ስቷል በአድዋ ጦርነት ሁለት የተለያዩ ገበየሁዎች እንደነበሩ የምንገነዘበው በጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ የተመዘገበውን የጦር አለቆች ኣሰላለፍ ስናይ ነው ለማንኛውም አሠላፊ ገበየሁ በጦር ሜዳ ከወደቀ በኋላ ያልታወቀ አዝማሪ ያንጎራጎረለት አንጀት የሚበላ ግጥም Folk-literature of the Oromo .. በተባለው መዝገብ ተካቷል ታድያ እኔ እንጉርጉሮውን መነሻ አድርጌ የራሴን ግጥም ብጽፍ ማን ይከለክለኛል?አሠላፊ ገበዮ!እንደ እግዜር ስጋጃ ምድሩ ላይ ተሰፍተህእንደ ብረት ቁና አፈር ላይ ተደፍተህጓዶች ወዴት አሉ? ብለህ ስትጣራጓዶች ተመለሱ ከንጉሡ ጋራሚስቴ ወዴት አለች ?ብለህ ስትጣራሚስትህ ወዲያ ቀረችበሞትህ በማግስቱ ለሌላ ተዳረችይልቅ እናቴ ሆይ ! በማለት ተጣራየናት ኀዘን ዶፍ ነው ቶሎም አያባራ
የአድዋ ዘማቾችclick here for pdfየጉዞው መሥራቾችትናንትእሑድ መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓም በጨጨሆ የባሕል ምግብ አዳራሽ በተደረገ አንድ መርሐ ግብር ተጋብዤ ተገኝቼ ነበር ጉዞ አድዋ ይባላል መርሐ ግብሩ ከዛሬ 119 ዓመት በፊት ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን በዓለም ታሪክ ያልተለመደ አዲስ ታሪክ ለመሥራትና ኢትዮጵያ የምትባለውን ሀገር የማይደረስበት ከፍታ ላይ ለማስቀመጥ ሲሉ ከመላዋ ሀገሪቱ አንድ ሆነው ወጥተው አንድ ሆነው ወደ አድዋ ዘምተው ነበር ያኔ ብዙዎቹ የተጓዙት በእግራቸው ጋራ ሸንተረሩን አረሁን ገደሉን እየተሻገሩ በፍጹም ኢትዮጵያዊ ወኔና ሀገራዊ ፍቅር ነበር ያ አንድነትና የሀገር ፍቅር ስሜት ነበር ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችንን ሊደግሙት እንጂ ሊረሱት የማይገባ ታሪክ እንዲሠሩ ያደረጋቸውይህንን የአድዋ መንፈስና ዝና ክብርና ላቅ ያለ ኢትዮጵያዊነት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ አድዋ እንደ አንድ ተራ ሥነ ሥርዓት በምኒልክ አደባባይ የአበባ ጉንጉን ከማስቀመጥና አስቦ ከመዋል የዘለለ ትውልዳዊ ፋይዳ እንዲኖረው ለማድረግ አድዋ እንደ ባለሞያ ጠጅ በየጊዜው ከጥንስሱ እየተቆነጠረ በየትውልዱ እንዲጠጣ ለማስቻል እንደ ሰራፕታ ዱቄት በየዘመናቱ ቡኾ ውስጥ እንደ እርሾ እየተጨመረ እንዲበላ ለማብቃት አድዋ ላይ የታየው የላቀ ኢትዮጵያዊነት አንደ ሜሮን ቅብዐት ከትውልድ ትውልድ ሳይቋረጥ እየፈላ የሁሉ ማጥመቂያ እንዲሆን የተነሡ ወጣቶች ያዘጋጁት መርሐ ግብር ነበር እንደ አድዋ ዘማቾች ወኔ እንጂ ሌላ ሀብት የሌላቸው ወጣቶች እነዚህ ወጣቶች አንድ አስደማሚ ተግባር ጀምረዋል በየዓመቱ የአድዋ በዓል ከመከበሩ ቀደም ብለው ከአዲስ አበባ በመነሣት በእግራቸው ወደ አድዋ መዝመት አባቶቻቸውና እናቶቻቸው በእግራቸው የተጓዙትን መንገድ እነርሱም በእግራቸው መከተል የቀድሞ የአድዋ ዘማቾችን ስሜት እየተጋሩ ታሪካቸውን እያጠኑ በየደረሱበት ለሚያገኙት ሁሉ የአድዋን የላቀ ኢትዮጵያዊነት እየሰበኩ የትውልድን ቃል ኪዳን ማደስተጓዦቹ ከመልስ በኋላበድንኳን እያደሩ ያገኙትን እየቀመሱ ከአራዊት ጋር እየታገሉ ከተራራና ገደል ጋር እየተገዳደሩ እየወደቁ እየተነሡ እየታመሙ እየተፈወሱ እየደከሙ እየጀገኑ እያዘገሙ እየፈጠኑ ከአንድ ሺ ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነውን መንገድ በእግር ማቆራረጥ አድዋ ላይ ተጉዘው የታሪክ ማርሽ በዘወሩ ጀግኖች ስም ራሳቸው እየሰየሙ የመንፈስ ወራሽታቸን ማረጋገጥ የዘንድሮ ተጓዦች ስድስት ናቸው ከስድስቱ አንዷ ሴት ናት ጽዮን ትባላለች በጉዞው ስሟ ደግሞ እቴጌ ጣይቱ ከአንድ ሺ ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነውን መንገድ በእግሯ አቆራርጣ እንደ እቴጌ ጣይቱ አድዋ ላይ ሰንደቋን ተክላለች መድረኩ ላይ ወጥታ የእቴጌን ታሪክና የጉዞውን ትዝታ ስትተርክ የሆነ የሚንፎለፎል ትኩስ ወኔ ከውስጧ እየወጣ ይገርፈን ነበር እናለቅሳለንም እንገረማለንም እናጨበጭባለንም የማትነጥፍ ሀገርከጉዞ አስተባባሪዎች አንዱ የሆነው መሐመድ ስለ ጉዞው ዓላማና ሂደት ሲገልጥ እርሱ ራሱ ከዐፄ ምኒሊክ ሠራዊት ጋር የዘመተ ነበር የሚመስለው መቼም መሐመድ ስለ ኢትዮጵያ ሲያወራ መስማት በባለሞያ ካህን የተከሸነ ቅዳሴ እንደመስማት ያለ ነው ያወጣዋል ይተርከዋል ያውም ከዕንባና ከስሜት ጋራእነዚህ ወጣቶች የዛሬ ዓመት በ2008 ዓም አንድ ታላቅ ታሪክ ሊሠሩ አስበዋል የአድዋ አንድ መቶ ሃያኛ ዓመት ሲከበር አንድ መቶ ሃያ ተጓዦችን ይዞ ወደ አድዋ በእግር ለመዝመት ወጣቶች ናቸው ግን ልባቸው ሸምግሏል ብዙ ሊስቧቸው የሚችሉ ብልጭልጭ ነገሮች ነበሩ ነገር ግን ሀገራዊውን ታሪክ መርጠዋል ከሺ ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆነውን መንገድ በእግር አቆራርጠው የሀገራችንን ባንዴራ ከፍ አድርገው በየደረሱበት አድዋ ላይ የተገለጠውን ያንን ሁላችንንም የሚያኮራ ኢትዮጵያዊነት እየተረኩ በእግራቸው ሊጓዙ ተነሥተዋልጽዮን - እንደ እቴጌ ጣይቱእንደ እኔ እንደ እኔ አንድ ትውልድ ታሪኩን ሲያነሣ በማንነቱ ሲኮራ ታሪክም ለመሥራት ሲቆርጥ መደገፍ ይገባል እላለሁ ወጣቶች ከሥነ ምግባር ሲወጡ ማንነታቸውንና ታሪካቸው ሲረሱ ለሀገራዊ ነገሮችም የእኔነት ስሜት ሲያጡ እንደምንወቅሰውና እንደምናዝነው ሁሉ በሀገር ፍቅር ስሜት ሲነሡና ታሪካችንን ከፍ አድርገው በአዲሱ ትውልድ አዲስ መንፈስ ውስጥ ሊጽፉት ሲተጉም አብረናቸው መሥራት ይገባናል ታሪካችንና ማንነታችን እንደማይዘነጋ ማረጋገጥ የምንችለው ተተኪው ትውልድ የእኔ ነው ብሎ በራሱ መንገድ ሊገልጠው ሲሞክር ካየን ብቻ ነውየጉዞው አስተባባሪ ያሬድ ሹመቴእናግዛቸው አብረናቸውም እንቁም የቻልን የጉዟቸውን ወጭ እንጋራ ያልቻልን በሚደርሱበት ቦታ ሽሮ ሠርተን ውኃ ቀድተን በማስተናገድ የጥንት አያቶቻችን የአድዋ ዘማቾችን የሸኙበትን ታሪክ እንድገመው በሚደርሱባቸው ቦታዎች ያሉ ትምህርት ቤቶች ደግሞ ወጣቶቹ ከተጓዦቹ ጋር ስለ ታሪካቸው እንዲወያዩ መርሐ ግብር ያዘጋጁ የእምነት ተቋማት ደግሞ በሚደርሱባቸው ቦታዎች በመቀበል ለታሪካችንና ማንነታችን ያለንን የከበሬታ ሥፍራ እናሳይ በየቦታው የምንገኝ ኢትዮጵያውያንም በየደረሱበት ቦታ እየተቀበልን ባንዴራውን ከፍ አድርገን በማሻገር የታሪክ ተረካቢነታችን እናረጋግጥ አንድ መቶ ሃያኛውን የአድዋ በዓል በ2008 ዓም ከአበባ ማኖር በዘለለ በማይረሳ የወጣቶች ታሪካዊ ጉዞ እናክብረው ጠቢብ አስቦ ይሠራልጎበዝ ደግሞ ከሚሠሩት ጋር ያብራል
ጉዞ አድዋ እና በህብረተሰቡ የተፈጠረው ብዥታባሕር ዳርጥር 182011 ዓ.ምአብመድ ከአምስት ዓመት በፊት በአምስት ተጓዦች ነበር የተጀመረው ጉዞ አድዋ ባለፉት አምስት ዓመታት በነበሩት ዝክረ ጉዞ አድዋም 56 ተጓዦች ተሳታፊዎች ሆነዋል ዘንድሮ የሚከበረው 123ኛ የአድዋ ድል በዓል እንዳለፉት ጊዜያት በእግር ጉዞ ተጀምሯልከአለፉት ዓመታት በተለየ መንገድ የዘንድሮው ጉዞ አድዋ የተጓዦችና የጉዞ ቡድኖች በቁጥር ጨምሯል 29 የተጓዥ አባላትን የያዘ አንድ የጉዞ አድዋ በጎ አድራጎት ማህበር እና 48 ተጓዦችን የያዘ ሌላ ቡድን በኬር ኢቨንት ኤንድ ኮምዩኒኬሽን ተዘጋጅቷልበኢትዮጵ የዓይን ባንክ ድርጅት የአምባሳደርነት ተልዕኮ የተሰጠው የጉዞ አድዋ በጎ አድራጎት ማህበር መነሻውን በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል አድርጎ እና ሰላም ፍቅር እና አንድነት ለኢትዮጵያ! በሚል መሪ ሃሳብ የዘንድሮውን ጉዞ አድዋ ከጀመሩ ቀናት ተቆጥረዋልበሌላ በኩል በኬር ኢቨንት ኤንድ ኮሚዩኒኬሽን አዘጋጅነት የአድዋ ድልን ለመዘከር ከሃረር የተነሳ ሌላ የጉዞ ሁነት አዘጋጅ ቡድን አለ ትናንት በአድዋ የተከፈለልንን በማሰብ በመስዋትነት የተሰራችውን ሀገራችን በፍቅር ለመጠበቅ የሚያስችል መልዕክት ለትውልዱ ማድረስ! የሚል ዓላማ አንግበዋል የዘንድሮው የአድዋ ድል የጉዞ በዓል ካለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታት በተለየ መልኩ በሁለት የጉዞ ቡድኖች መካሄዱ በህዝብ ዘንድ ግርታ ፈጥሯል የአድዋን ድል በዓል የመዘከር ዓላማ ያለው ጉዞ እና ተቀራራቢ ስያሜ መያዛቸው ግርታውን ይበልጥ አጉልቶታልጉዞ አድዋ ከጉዞ ያለፈ ዓላማ እንዲኖረው እየሰራን ነው የሚለው የጉዞ አድዋ በጎ አድራጎት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ እሸቱ ማህበሩ ሌሎችን ታሪኮችን ጨምሮ ዓመቱን በሙሉ የሚሰራ በጎ አድራጎት እንዲኖር ጥረት እያደረግን ነው ይላልየማህበሩ አስተባባሪ ጋዜጠኛ ሚኒሊክ ፋንታሁን እስካሁን በተካሄዱ ተከታታይ የአድዋ ጉዞዎች ሁሉንም የአድዋ ታሪኮች በአግባቡ እየዘከሩ አልነበረም በዘንድሮው የጉዞ አድዋ በዓል አፄ ሚኒሊክ ወደ አድዋ ሲዘምቱ ባደሩባቸው ቦታዎች ሁሉ በማደር ታሪኩን ለማስታወስ እና የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ስራ እየሰሩ መሆኑን ገልፆልናልየኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ላደረገላቸው የበጀት ድጋፍ ምስጋና ያቀረበው ማህበሩ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስተር የድጋፍ ደብዳቤ ለመስጠት መዘግየቱን እና በአንዳንድ አካላት በማህበራዊ ሚዲያ የተፈጠረው የማጥላላት ስራ ተገቢ አይደለም ሲሉ ቅሬታቸውን በተለይም ለአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ተናግረዋልጉዞ አድዋን ለማካሄድ መንግስት ይፈቅድ ይሆን አይሆን ከሚል ጭንቀት ወጥተን በመንግስት የምንሸኝበት ጊዜ ላይ ደርሰናል የሚለው የጉዞ አድዋ ሁነት ዝግጅት አስተባባሪ አቶ ያሬድ ሹመቴ ምንም እንኳን ጉዞው አድካሚ እና ፈተና የበዛበት ቢሆንም የተከፈለልንን በማሰብ እንበረታለን ነው ያለው የዘንድሮው የጉዞ አድዋ ዝግጅት በሁለት ቡድኖች በመደረጉ በህዝቡ ዘንድ ከፈጠረው ግርታ በተጨማሪም የህጋዊነት ጥያቄንም አስነስቷልበጉዞ አድዋ በጎ አድራጎት ማህበር ስም ህጋዊ የሰውነት ምዝገባ ያለን የእኛ ማህበር ብቻ ነው የሚሉት የጉዞ አድዋ በጎ አድራጎት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ እሸቱ በዚህ ስም የሚንቀሳቀስ ማንኛውም አካል ህጋዊነት አይኖረውም ይላሉ በኬር ኢቨንት ኤንድ ኮምዩኒኬሽን ድርጅት የተዘጋጀው የጉዞ አድዋ አስተባባሪ አቶ ያሬድ ሹመቴ በበኩላቸው ትናንት አድዋ ላይ ድል ያደረጉት አባቶቻችን በአንድ አቅጣጫ አልሄዱም መንገዳችን ቢለያይም መዳረሻችን አድዋ ነው ከህጋዊነት ጋር ተያይዞ ለሚነሳው ጥያቄ ግን እኛ ህጋዊ የሆነ እና በሚመለከተው አካል የተሰጠ ፈቃድ አለን ብለዋልስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጡን በስልክ የጠየቅናቸው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶር. ሂሩት ካሳው የህጋዊነት ጉዳይ ተቋማቸውን እንደማይመለከት ገልፀው በየደረሱበት አካባቢ ህዝቡ ድጋፍ እና አቀባበል እንዲያደርግላቸው ግን ለሁለቱም የተጓዥ ቡድኖች የድጋፍ ደብዳቤ ሰጥተናል ብለዋልአድዋ በሁለት ቡድኖች እና በውስን ተጓዦች ብቻ መወሰን የለበትም የሚሉት ሚኒስትሯ ተቋማቸው የተጓዦች ቁጥር በየጊዜው እያደገ እንዲሄድ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል በጉዞ አድዋ የበጎ እድራጎት ማህበር የድጋፍ ደብዳቤ መዘግየትም በሰራተኞች የግልፀኝነት ችግር የተፈጠረ መዘግየት እንደነበር ጠቁመዋል
ዓድዋ የእኛ ... የትውልድ ኩራት ነቢዩ ሲራክ የጦርነቱ መነሻ ምክንያት ... የዓድዋ ጦርነት መነሻ ምክንያት የሆነው የውጫሌ ውል አንቀጽ 17 ሲሆን ይህ አንቀጽ የኢትዮጵያን ህልውና የሚፈታተን ሆኖ በመገኘቱ እንዲሰረዝ የተደረገው ሙከራም በጣሊያን እምቢተኝነት በመክሸፉ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ የጣሊያን ወረራ መሰማትና እቴጌ ጣይቱ ... የጣልያንን እምቢተኝነት ተከትሎ ሚኒስትሮች የጦር አለቆችና መኳንንቱ ባካሄዱት የምክክር ጉባኤ ላይ እቴጌ ጣይቱ ብጡል እኔ ሴት ነኝጦርነት አልወድምሆኖም ግን ኢትዮጵያን የጣሊያን ጥገኛ የሚያደርግ ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ ሲሉ የሰጡት አስተያየት ነበር የኢትዮጵያው ንጉሰ ነገስት የዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ ... ጣሊያን ውል አፍርሶ ኢትዮጵያን ሲወርር በጉልበቱ የጀግኖችን ሃገር ሊፈታው እንደማይችል ያውቅ ነበር ጣልያን በልዩነታችን ገብቶ ሊለያየን እቅድ አቅዶም ነበር ይህንንም ለማሳካት በተለያየ አስተዳደር ግዛት ለይተው በሚቆራቆሱ የጦር አበጋዞችና በንጉሱ መካከል የነበረውን የከፋ ልዩነት መጠቀም ለድል እንደሚያበቃው አልሞ መነሳቱ እውነት ነበር ያም ሆኖ የንጉሰ ነገስቱ መኳንንቱን ሹመኞችን እና የጦር አለቆችን ሰብስበው በመምከር ብሔራዊ ክብርን ማስጠበቁ ይቅደም አንድምታ ያለው ሃሳባቸው ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ በሰለጠነ መንገድ ከመግባባት ላይ ደረሱ ይህም ምክክርና ስምምነት ሁሉም በአንድነት ለነጻነትና ክብሩ ይተጋ ዘንድ ታላቅ አስተዋጽኦ ያደርግ ዘንድ ሁሉም በየስራ ድርሻው ተመድበው መስራት ጀመሩ መስከረም 1888 ዓ.ም ወር ላይ ንጉስ ምኒሊክ ጣሊያንን ለወረራ መዘጋጀቱን በስለላ ባለሟሎቻቸው በቅርብ አረጋገጡ በወረራ ዝግጅቱ የተቆጡት ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ እንዲህ በማለት አስነገሩ ... እግዚአብሄር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ እኔም እስካሁን በእግዚአ ብሔር ቸርነት ገዛሁ ከእንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ስለእኔ ሞት አላዝንም ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም አሁንም አገር የሚያጠፋ ሃይማኖትን የሚለውጥ በፊት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባህር አልፎ መጥቷል እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም የአገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሃዘንህ እርዳኝ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልምርህም ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም... ዓድዋና የጦሩ ዝግጅት ... የዓድዋው ጦርነት በጣልያኖች በኩል የቆየ የቀኝ ግዛት ጥማቸውን ለማሳካት ቀድሞ የተጠነሰሰ ነበር በኢትዮጵያውያን ዘንድ ግን የጦርነት ዝግጅቱ እስከ ሰባት ወር የፈጀ እንደነበር ይነገራል ዝግጅቱ ተጠናቆ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ጎህ ቀዶ እስኪጠልቅ በቀድሞዋ ትግራይ ጠቅላይ ግዛት በዛሬዋ ክልል አንድ ትግራይ ውስጥ በምትገኘው በዓድዋ ከተማ ይገጥም ዘንድ ቀኑ ደረሰ ! በዓድዋው ዘመቻ በመቶ ሺሕዎች ሆኖ የዘመተው የኢትዮጵያ ጦር ከጥቂቱ በስተቀር አብዛኛው ጦር ሰይፍ ጋሻና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ይዞ እንደ ነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ ጣሊያን በአስር ሽዎች የሰው ሃይል በዘመናዊ የጦር መሳሪያና በወታደራዊ ሳይንስ የሰለጠነ አውሮፓዊ ጦር ነበርና ከፍ ባለ ስንቅና ትጥቅ ተደግፎ ወረራ መጀመሩ ይጠቀሳል አንጸባራቂው የዓድዋ ድል ... የጥቁሮች ድል ! የጣሊያን ጦር በጄኔራል ባራቴሪ እየተመራ ባህር ተሻግረሮ ሲመጣ የተወረረችው የኢትዮጵያውያን ጦር የሚመራው በንጉሰ ነገስት ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ ነበር ጀግና ብልህና አርቆ አስተዋይዋ ባለቤታቸው እትየ ጣይቱ ብጡል በዚያ ባልሰለጠነ ዘመን ስልጡን ነበሩና በባለቤታች ከሚመራው የአርበኞች ግንባር እኩል ተሰልፈው ሃገሬውን ስንቅ ትጥቅ በማስታጠቅና በማበረታታት የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አልነበረም ኢትዮጵያውያን በንጉሱ ብልህ አመራርና ክተት ብለው በህብረት ተነሱ ከሽኩቻና ዝብሪት ተዘፍቀው የባጁት የየግዛቱ ሹሞች እና የጦር አበጋዞችም በንጉሰ ነገስት አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ ልዩነታቸውን አስወግደው በህብረት ተመሙ ! የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ከ118 ዓመታት በፊት በዕለተ ሰንበት ክብሩ የተነካው አርበኛ ህዝብ ዓድዋ ላይ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ተንቀሳቅሶ ባካሔደው ውጊያ እብሪተኛውን ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ የጣሊያን ጦር ጋር ገጠመ ! ከማለዳ አንስቶ ጀንበር እስክታዘቀዝቅ ባለው ጊዜ የተካሄደው ጦርነት እልፍ አእላፍ መስዋዕት ሆነው በኢትዮጵያ ድል አድራጊነት በዓድዋ ተደመደመ !ጣሊያን ከአንባላጌ እስከ አድዋ ተጠራርጎ እንዲወጣ ያደረገው የጥቁሮች ድል! በሚል አለም ባወደሰው የዓድዋ ድል የጣሊያን መንግስት የሃፍረት ማቅን በግዱ ተከናነበ የዓድዋ ድል በመላ በአለም ከተበሰረ በኋላ የወረራው መነሻ የሆነውን የውጫሌ ውል ፈርሶ የጣልያን መንግስት በውጫሌ ውል የነበረውን አጉል ምኞቱን ይሰርዝ ዘንድ ግድ ሆነበት ወራሪው በሽንፈቱ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙሉ ነፃነት አውቆ እና ተቀብሎ የሰላም ስምምነት ያደርግ ዘንድ ተገደደ ! የስምምነት ውሉም ለአለም መንግስታት ተሰራጨ ውሉ የደረሳቸው መንግስታት እና ሃገራት የኢትዮጵያን የተረጋገጠ ሉአላዊ መንግስትነት በውድም ሆነ በግድ ተቀብለው አረጋገጡት ! የዓድዋ ድል በዳግማዊ አጤ ምኒሊክ ድብዳቤዎች ... ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የዓድዋን ድል አስመልክተው ለፈረንሣዊው ሙሴ ሞንዶን የዛሬ 118 ዓመት የጻፉለት የምሥራች ደብዳቤ እንዲህ ብለው ነበር የምሥራች በእግዚአብሔር ቸርነት የየካቲት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ኢጣልያንን ድል አድርጌ መታሁት በጨረቃ ሲገሰግስ አድሮ እሰፈሬ ድረስ መጥቶ ገጠመኝ አምላከ ኃያላን ረድቶኝ ፈጀሁት ደስ ብሎኛል ደስ ይበልህ አጤ ምኒሊክ በመጋቢት 23 ቀን 1988 ዓ.ም. ለፈረንሳዊው ሙሴ ሸፍኔ በላኩለት ደብዳቤ ያቸው እንዲህ ብለዋል ... ከአላጌ ጦርነት በኋላ ጣሊያኖችን ጦርነት ይቅር የክርስቲያንም ደም በከንቱ አይፍሰስ እርቅ ይሻላል ብላቸው እምቢ ብለው መጥተው በጥጋባቸው ዓድዋ ላይ ተዋግ ተው ድል ሆኑ እኔ ግን በድቁርናቸው ብዛት የነዚያን ሁሉ ክርስቲያን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኳቸው ብዬ ደስ አይለኝም ነገር ግን በግፍ የመጡ ሰዎች ናቸውና እግዚአብሔር ግፉን አነጣጠረን... በማለት ያስታወቁ ሲሆን ምኒልክ ለሞስኮብ ንጉሥ ኒቆላዎስም መጋቢት 23 ቀን 1988 ዓ.ም በጻፉት ደብዳቤያቸውም እንደ አውሮፓ ነገሥታት ሥራት ሁሉ ጠብ መፈለጋቸውን ሳያስታውቀኝ እንደ ወምበዴ ሥራት ሌሊት ሲገሰግስ አድሮ ሲነጋ ግምባር ካደረው ዘበኛ ጋር ጦርነት ጀመረ ጥንት ከአህዛብና ከአረመኔ አገራችን ጠብቋት የሚኖር አምላክ ከእኛ ባይለይ በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረግሁት... ብለው መጻፋቸው ይጠቀሳል አልፋና ኦሜጋ የማይረሳው መስዋዕትነት ... አልፋና ኦሜጋ በክብር ይዘከራል !ልክ የዛሬ 118 ኛ አመት እሁድ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓም ታላቁ የዓድዋ ድል በዓድዋ ሰንሰለታማ ተራሮች ላይ ተበሰረ ! ይህ የጥቁር ህዝብ በቅኝ ገዥዎች ከተቀዳጃቸው የዓድዋ ድል እውን እንዲሆን አቀበት የወጡ ቁልቁለት የወረዱ እርጥብ የጨሰባቸው ደረቅ የነደደባቸው ከቤታ ቸው የተፈናቀሉ የቆሰሉ የሞቱ መዳረሻቸው የጠፋ ጀግኖቻችን አልፋና ኦሜጋ የማይረሳው መስዋዕትነት ነው ... ይህ አንጸባራቂ ድልም እነሆ አልፋና ኦሜጋ በክብር ይዘከራል ! ልክ የዛሬ 118 ዓመት ከዘመነው የፋሽሽት ጣሊያን ጦር እና ጦር ሰራዊት በላይ የጥቁር ህዝብ ብሔራዊ ክብርና ኩራት ልቀው የታዩበት የጦርነት አውድማ ነው ! ዓድዋ !በዓድዋ ድል እንኮራለን ! የዓድዋን ድል በክብር እናዘክራለን !ክብር ለደሙ ለቆሰሉና በክብር ለሞቱ ሰማዕታት !ክብር ለጀግኖቻች አርበኞቻችን !ከብር ለእምየ ምኒሊክ ! ክብር ለእቴጌ ጣይቱ !ክብር ለኢትዮጵያ !እንኳን ለታላቁ የዓድዋ የድል በአል አደረሳችሁ !የመረጃ ምንጮቸ : በታዋቂ የታሪክ አዋቂዎች ከተጻፉት የታሪክ መዛግብትከአድዋው ጦርነት ዙሪያ ከቀረቡት የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት በተለያዩ በጊዜ ስለ ዓድዋ ድል ገድል ዙሪያ ከተጻፉ ጋዜጦችና መጽሔቶች ሲሆን ለአንባብያን እንዲመች አድርጌ አቅርቤዋለሁ Share ButtonTwitterFacebookLinkedinEmailPrintDisclaimer: We are not responsible for any losses or damages that may have caused by using our services. EMF declines all responsibility for the contents of the materials stored by users. Each and every user is solely responsible for the posts. Posted by ethioforum on March 2, 2014. Filed under Uncategorized. You can follow any responses to this entry through the RSS 2.0. Both comments and pings are currently closed.One Response to ዓድዋ የእኛ ... የትውልድ ኩራት ነቢዩ ሲራክኦይቻ ኦኒ_ኦኔMarch 2, 2014 at 1:21 PMከቅርብ ጊዜወዲህ ስለ አድዋና ሚኒልክ ብዙ ይባላል::ታሪክ የነካካ ታሪክንም በጨርፍታ የሚያልፍየሚያዛባ:: አርሲ የተተከለው ሀዉልት ነገሩን ያባባሰውና ይበልጥ ወገናዊ አደረገው::ያደረገው ይመስለኛል::ለሁሉም ለሁለም ምኒልክ ማን ነበሩ? ከጣሊያን ጋር ከአድዋ በፊትም በሁዋላም የነበረው ግኑኝነት ምን ይመስል ነበር?ኣድዋ ያሸናፉ ሚኒሊክ ናቸው ወይስ ጣይቱ? ለማሆኑ ጣይቱ ማህኖሩስ ኖሮ?የአይን ምስክር የሆነውን የፈታውራሪ ተክለ ሀዋሪያትን የህይወ ታሪክ ደግሞ ደጋግሞ ማንበብ ጥሩ የማስለኛል::
የእንዳ ኢየሱስ ምሽግ- ከእቴጌ ጣይቱ እስከ ዶክተር ክንደያclick here for pdfየመቀሌው ምሽግ ጥንታዊ ፎቶየአድዋ ጦርነትና ድል ሲነሣ ምንጊዜም አብሮ የሚነሣ የኢትዮጵያውያን የጀግንነትና የብልሃት ዐውደ ውጊያ አለ የመቀሌው ምሽግ ውጊያጣልያኖች የመረብን ወንዝ ተሻግረው ወደ ትግራይ ሲገቡ ጠንካራ ምሽግ ከሠሩባቸው ቦታዎች አንዱ መቀሌ እንዳ ኢየሱስ ነበር ምሽጉን ማጆር ቶዞሊ አስጀምሮት እርሱ በአላጌው ውጊያ ሲሞት ማጆር ጋልያኖ አጠናቅቆታል ለመቀሌው ምሽግ መጠናከር ዋናው ምክንያት ጣልያኖች አላጀ ላይ በራስ መኮንን በሚመራው የኢትዮጵያ ጦር የገጠማቸው ሽንፈት ነው ጄኔራል አርሞንዲ ኅዳር 28 ቀን 1888 ዓም የደረሰበትን የአላጌን ግንባር ሽንፈት ተከትሎ ወደ ኋላ በሸሸው የጣልያን ወታደር አማካኝነት ከባሕር ወለል በላይ በ2240 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘውን የእንዳ ኢየሱስ ምሽግ የበለጠ እንዲጠናከር አደረገ በቦታው የሚገኘውን የኢየሱስን ታቦት አስወጥቶ ቦታውን ሙሉ በሙሉ ምሽግ አደረገውእነ ፊታውራሪ ገበየሁ ታሪክ የሠሩበትና የኢትዮጵያውያንን ጥምር ክንድ ጣልያን በሚገባ በቀመሰበት በአላጌ ግንባር ማዦር ቶዜሊ በራስ ዐሉላ ብርጌድ ደረቱን ተመትቶ የወደቀበት ነውአላጌ በሩ ላይ ሲወርድ ማዦርእንደ ግራኝ ሁሉ በሰባት አረር - ተብሎለታል በዚህ ጦርነት አምስት ካፒቴኖች ዐሥር የመቶ አለቆችና ሁለት ምክትል መቶ አለቆች በጦርነቱ ተገደሉ ሁለት ሺ የሚደርሱ የኢጣልያ ወታደሮችም አለቁ ራስ መኮንንም የጣልያኖቹን ሬሳ ከየቦታው አስለቅመው በቤተ ማርያም አስቀበሩት ይህም ጣልያኖች መቀሌ ላይ ጠንካራ ምሽግ እንዲሠሩ አደረጋቸው ጄነራል አርሞንዲ የመቀሌው ምሽ በተመለከተ የሚዋዥቅ ሐሳብ ነበረው ትቶ ለመሄድም አስቦ ነበር ነገር ግን ይህንን ማድረግ የጣልያንን ክብር መንካት ነው ብሎ ያመነው ከዚህም አልፎ የኢትዮጵያን ጦር የሚንቀው ጋልያኖ የመቀሌው ምሽግ ላለማስደፈርና ተዋግቶ ለመሞት ቆረጠ በሁለተኛው የጣልያን ወረራ ጊዜ መልሶ የተሠራው የመቀሌው ምሽግጳውሎስ ኞኞ እንደሚለው የመቀሌ ምሽግ በደቡብ በኩል 3 ሜትር ስፋት ያለው ግንብ እየሆነ ተገነባ ምሽጉ ዙሪያ ክቡን ካለው አጥር ሌላ ከግንቡ 30 ሜትር ያህል ራቅ ብሎ በጣም የሾሉ እንጨቶች በምሽጉ ዙሪያ በብዛት ተተከሉ ካንዱ ሹል እንጨት እስከ አንዱ ሹል እንጨት ያለው ርቀትም 20 ሳንቲ ሜትር ያህል ነበር እነኚህ ሹል እንጨቶች ከመሬት በላይ ያላቸው ከፍታ 30 ሳንቲ ሜትር ነው ከሹል እንጨቶቹ አልፎ ደግሞ እሾካማ ሽቦ እየተድቦለቦለ በምሽጉ ዙሪያ እየተተከለ ተከምሯል ከሽቦው ውጭ ደግሞ ጠርሙስ እየተሰበረ እንዲነሰነስ ተደረገ ይላልጣልያኖች ይህንን ያደረጉት የኢትዮጵያ ወታደሮች ባዶ እግራቸውን ናቸውና ይህን አደገኛ እሾሃማ አጥር ተሻግረው ለመግባት ይከብዳቸዋል ብለው በማሰባቸው ነበር እንዳሉትም ምሽጉን ለመስበር በተደጋጋሚ የተደረጉ ሙከራዎች ሊሳኩ አልቻሉምጣልያኖች ከምሽጉ ሥራና አጥር በተጨማሪ በምሽጉ ውስጥ ጠንካራ ጦር መሽጎ ነበር ተክለ ጻድቅ መኩሪያ እንደሚሉት በጋልያኖ የሚመራው አንድ ባታልዮን ጦር 21 የጦር መኮንኖችን 176 ነጭ ለባሾችን 1150 የሀገር ተወላጅ ወታደሮችን እና አንድ መድፈኛ ጦር የያዘ ነበር ጳውሎስ ኞኞም የመቀሌ ምሽግ 20 ከፍተኛ መኮንኖች 13 ዝቅተኛ መኮንኖች 150 ባለ ሌላ ማዕረግ ወታደሮችና አንድ ሺ ጥቁር ወታደሮች ነበሩበት ይላልበራስ መኮንን የሚመራው የኢትዮጵያ ጦር የአላጀን ድል ተከትሎ ወደ መቀሌ ገሰገሠ ኦገስት ዋይልድ የራስ መኮንን ጦር ኅዳር 30 ቀን 1888 ዓም የመቀሌውን ምሽግ ከብቦ መቀመጡን ጦርነቱንም ታኅሣሥ 18 ቀን መጀመሩን የሚገልጡ አሉ ጳውሎስ ኞኞ ግን ጦርነቱ የተጀመረው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ መቀሌ ከገቡ በኋላ ታኅሣሥ 30 ቀን መሆኑን ይናገራልዐፄ ምኒሊክ መቀሌ ሲገቡ የመቀሌው የእንዳ ኢየሱስ ምሽግ ዙሪያውን ተከበበ ጦሩ ከጣልያን መድፍ ርቀት ውጭ ሆኖ በጨለቆት በኩል የንጉሠ ነገሥቱ ጦር የራስ መኮንንና የፊታውራሪ ገበየሁ ጦር በደብሪ በኩል የሸዋ ጦር በምሥራቅ በኩል የንጉሥ ተክለ ሃይማኖትና የራስ መንገሻ ጦር በገምበላ በኩል የራስ መንገሻ አቲከም እና የራስ ወሌ ጦር እንዲሠፍር ተደረገ ሊቀ መኳስ አባተ ቧ ያለውና በጅሮንድ ባልቻ ደግሞ መድፎቻቸውን ይዘው በስተ ምሥራቅ በኩል አመቺ ሥፍራ ያዙ ብዙዎቻችን እንደሚመስለን የኢትዮጵያ ጦር ወደ አድዋ ሲዘምት ኋላ ቀር መሣሪያ ብቻ አልያዘም የኢትዮጵያን ጦር ለውጤት ያበቁት ጠንካራ የሀገር ፍቅር ተገቢ የሆነ ዝግጅትና አደረጃጀት የሁሉም ሕዝብ ሁለገብ ተሳትፎ የዐፄ ምኒልክና የጦር ጄኔራሎቻቸው የአመራር ጥበብ ከዚያ በፊት ከውጭ ወራሪዎች ጋር በተደረጉ ውጊያዎች የተቀሰሙ ልምዶች እና ትክክለኛ የጦርነት ምክንያት ናቸውዐፄ ምኒልክ ለማይቀረው ጦርነት ቅድመ ዝግጅት አድርገውበታል ሀገሪቱ ጠብቃ ባቆየቻቸው መሣሪያዎች ላይ ከፈረንሳይ ተገዝተው በጅቡቲ በኩል የገቡትና በየዐውደ ውጊያው የተማረኩት ዘመናዊ መሣሪያዎችም ለጦርነቱ ውለዋል ኦገስት ዋይልድ ይህንን ሁኔታ ሲገልጠው the Hotchkiss quick firing guns with a longer range ...were of a caliber of about two inches, firing both solid and percussion shell, and their range and accuracy were much superior to the muzzle-loading mountain guns of the Italians. ይላል ተክለ ጻድቅ መኩሪያም ከፈረንሳይ ሀገር ተገዝቶ የመጣውና በኢትዮጵያውያን እጅ ያለው የመድፍ ጥይት እስከ 4500 ሜትር ድረስ ሄዶ የሚመታ ሲሆን የኢጣልያኖች ግን 3800 ሜትር የሚሄድ ነበር ይላሉ በዚህ መሣሪያ ላይ እነ ሊቀ መኳስ አባተ ቧ ያለውና በጅሮንድ ባልቻ አባ ነፍሶ ያሳደጉት ፈረስ ያህል ተክነውበታልኢትዮጵያውያን በመድፎቻቸው እየተረዱ ምሽጉን ሰብረው ለመግባት በተደጋጋሚ ሙከራ አድርገው ነበር መሰላል አምጥተው ወደ ምሽጉ ከታች ወደ ላይ በድፍረት ለመውጣትም ሞክረዋል ነገር ግን ምሽጉ ከነበረበት ስትራቴጂያዊ አቀማመጥ አንጻር ሊሳካ አልቻለምበመጨረሻ ግን የእቴጌ ጣይቱ መላ በአጭር ጊዜ ምሽጉ እንዲለቀቅ አደረገ ማይ አንሽቲ ምንጭ እቴጌ ጣይቱ ሊቀ መኳስ አባተ ቧ ያለው ጋር መክረው ተዋግተው ለተረፉት ደስ የሚያሰኝ የክብር ሽልማት እሰጣለሁ ለሞቱትም ተዝካራቸውን አወጣላቸዋለሁ ብለው ብለው የላኳቸው በዝቅተኛ መኮንኖች የተመሩት የኢትዮጵያ ወታደሮች ከምሽቱ በ11 ሰዓት ገብረ ጊዮርጊስ ድል ነሤ እና ሸዋዬ የሚባሉ አሽከሮች ሶስት ሦስት መቶ ወታደሮች ይዘው ወደ ማይ አንሽቲ ምንጭ ወረዱ ምሽጋቸውንም ሠሩ እቴጌይቱ ሌሊቱን ሙሉ አምላኬ ሆይ አታሳፍረኝ እርዳኝ እያሉ ሲጸልዩ ማደራቸውን ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ዐፄ ምሊክና የኢትዮጵያ አንድነት በሚለው መጽሐፍ ላይ ይገልጣሉ ማይ አንሽቲ ከእንዳ ኢየሱስ ምሽግ 150 ክንድ ርቀት ላይ ይገኝ ነበር ወታደሮቹ በሌሊት ገሥግሠው ምንጩን ከበቡት ምንጩ የሚገኘው ከእንዳ ኢየሱስ ምሽግ ወረድ ብሎ ገደል ሥር ነበር የእቴጌ ጣይቱ ወታደሮች ከምንጩ በ15 ክንድ ርቀት ላይ አድፍጠው ተቀመጡ ጣልያኖች ምንጩ ለምሽጉ ቅርብ ስለነበር ይያዛል ብለው አልገመቱም ውኃው በኢትዮጵያውያን መያዙን ሲያውቁ ምንጩን ለመቆጣጠር መድፎቻቸው ጎትተው አውጥተው በተደጋጋሚ ጥረት አደረጉ ቦታው ከምሽጉ በኩል ለሚደረግ የመድፍ ምት ምቹ አልነበረም ለፊት ለፊት ውጊያም ከጣልያኖች ይልቅ ለኢትዮጵያውያን የተመቸ ነበር ምንጩን ለመቆጣጠር ጣልያኖች ያደረጉትን ጥረት የኢትዮጵያ ወታደሮች አደናቀፉት ሊቀ መኳሽ አባተና በጅሮንድ ባልቻም የጣልያን መድፎችን በመነጽር አይተው ደበደቧቸው ከዚያም አልፈው የጣልያኖችን መድፍ በመድፍ አፉን መትተው ሥራ አስፈቷቸው በዚህም ምክንያትአባተ አባ ይትረፍ ነገረኛ አዋሻኪ ሰውይህን መድፍ ከዚያ መድፍ አቆራረጠው - ተብሎ ተገጥሞላቸዋልየጦርነቱ ጊዜ እየጨመረ ሲመጣ የጣልያኖቹ ውኃ እያለቀ መጣ መጀመሪያ በራሽን ውኃ መታደል ጀመረ በመቀጠልም ችግሩ ከጣልያን ወታደሮች ዐቅም በላይ ሆነ እቴጌ ጣይቱ ግን ለምሽጉ ጠባቂዎች በየቀኑ ስንቅ ይልኩ ነበር ጣልያኖቹ ቀሪ ዕጣ ፈንታቸው ሞት መሆኑን ሲያውቁት ከ45 ቀን ከበባ በኋላ በድርድር እጃቸውን ለመስጠትና ምሽጉን ከነ መሣሪያው ለቀው ለመውጣት ወሰኑ ጥር 21 ቀን በድርድሩም መሠረት ምሽጉ ተለቀቀ ጣልያኖች መሣሪያቸውን አስረክበው ወጡ ዐፄ ምኒልክም በሰላም ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ ሸኟቸው ዳግም በውጊያ ካገኟቸው እንደማይምሯቸው አስጠነቀቋቸው ይህንን ውጤት ያመጣው እቴጌ ጣይቱ የዘየዱት መላ ነው አስቀድመው ለጣልያኑ አምባሳደር ለአንቶኒሊ እስንዳስጠነቀቁት ጦርነቱን አልፈለጉትም ነበር በሀገር ላይ ሲመጣ ግን እዚያው የጦሩ ዐውድማ ላይ እንገናኛለን ነበር አንቶኖሊን ያሉት እቴጌ ጣይቱ ያሉት አልቀረም ለአድዋው ድል በር ከፋች የሆነውንና የካቲት 23 ቀን ለሚዋጋው ሠራዊት የሞራል ከፍታ የፈጠረውን ድል አስመዘገቡት ለጎብኝ እንዲያመች ሆኖ የተጠገነው ምሽግ የግቢው መግቢያ እቴጌ ጣይቱ ታሪኩን ለመሥራት ሳይከብዳቸው ለ121ኛው የዐድዋ ድል በዓል አከባበር አድዋ ላይ የተገኙት አርቲስቶች ስማቸውን ማንሣት ከበዳቸው ኢትዮጵያውያን በፈጠሩት ዘዴ ብለው ያለፉት ይህንን የጣልያን መዛግብት ሳይቀሩ በድንቅ የሚያነሡትን የእቴጌ ጣይቱን ታላቅ ጥበብ ነው ዐድዋን እያከበሩ ምኒሊክንና ጣይቱን አለማንሣት ማለት አሜሪካን ከመከፋፈል ታድጎ ወደ አንድነት ያመጣትን የአሜሪካ የርስበርስ ጦርነት የሚባለውን ዘመቻ ታሪክ አንሥቶ አብርሃም ሊንከንን መዝለል ማለት ነው የዶጋሊን ድል አንሥቶ ዐሉላ አባ ነጋን መዘንጋት የሕወሐትን የመቀሌ እሥር ቤት ሰበራን ታሪክ አንሥቶ ኃየሎም አርአያን መተው ማለት ነው በዐድዋው በዓል ላይ የዐፄ ምሊክ ስም ያነሡት ሁለት ተናጋሪዎች ብቻ ነበሩ የደቡብ አፍሪካው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ታቦ ኢምቤኪና የጉዞ አድዋ አስተባባሪ ያሬድ ሹመቴ ለእናንተ ኮፍያችንን በክብር እናነሣለን የግቢው ንጣፍ በብርጭቆ ስብርባሪ ተነጥፏልእንደ ንጉሡ አጎንብሱ ብለው ጣልያን ዐድዋ ላይ የሠራውን ስሕተት በደገሙት አርቲስቶቻችንና አርቲስቶቹ ታሪክ ዘለው ታሪክ እንዲያጠለሹ መመሪያ በሰጡት አለቆቻቸው እያዘንን 121ኛውን የዐድዋ ድል ልናከብረው ነበር የኢትዮጵያ አምላክ ሲረዳን ግን የእንዳ ኢየሱስ ምሽግ እንደገና እንዲያዝ ያደረገውን ታሪክ የካቲት 26 ቀን 2009 ዓም መቀሌ ላይ አየን የዛሬ 2 ዓመት የአድዋ ተጓዦ ወጣቶች በእንዳ ኢየሱስ በኩል ሲያልፉ ምሽጉ ፈራርሶ ተንቆና ተረስቶ በዚያ ላይ የተሠዉት ኢትዮጵያውያን መቃብር ክብሩ ተዋርዶ ዐጽማቸው የትም ወዳድቆ ተመለከቱ አዘኑ ዐፄ ምኒልክ ያልቻልክ በኀዘንህ እርዳኝ እንዳሉት አዝነው ግን ዝም አላሉም የመቀሌ የኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ክንደያ ገብረ ሕይወት ይህንን ነገር እያዩ ለምን ዝም አሉ? ሲሉ ጠየቁ ያሬድ ሹመቴ ስሜት የሞላበት ግልጽ ደብዳቤ ጻፈ ሌሎችም ያንን ጩኸት አስተጋቡት መቼ ተነሡና የወዳደቁት የሚለው የእጅጋየሁ ሺባባው ቃል እውነት ሆኖ አየነው ብለን ኀዘናችንን ገለጥንምሽጉ እንዳይፈርስ የተገነባው የመጠበቂያ ግንብ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰማ ባለ ሥልጣን ሰምቶም የሚፈጽም ባለ ሥልጣን በሥዕለት ከሚገኙ ነገሮች መካከል ናቸው ዶክተር ክንደያና አመራራቸው ግን ሰሙ ሰምተውም ቅርስን የሚመለከተውን የዩኒቨርሲቲውን የትምህርት ክፍል ጠሩከዩኒቨርሲቲው የግንባታ ክፍል ጋር በመሆን ታሪኩንና ቅርሱን የሚጠብቅ ዲዛይን እንዲዘጋጅ አዘዙ የዲዛይኑን ዝግጅትም ራሳቸው ተከታተሉ በዩኒቨርሲቲው በጀትና የሰው ኃይል የእንዳ ኢየሱስ ምሽግ እንዲጠገን አካባቢው እንዲጸዳ ለጎብኚዎች በሚሆን መልኩ እንዲዘጋጅ ዐጽሞቹ በክብር እንዲሰበሰቡና በልዩ ሥነ ሥርዓት እንዲቀበሩ አስደረጉየምሽጉ ጥገና ሥራ ተፈጽሞ ባለፈው እሑድ የካቲት 26 ቀን ተከብሯል ጣልያን አድርጎት እንደነበረው ዙሪያውን በሽቦ ታጥሯል መንገዱ ጣልያን ኢትዮጵያውያንን ለመከላከል አድርጎት እንደነበረው የብርጭቆ ስብርባሪ ተነስንሶበታል በመቃብሩ ላይ ታሪኩን የሚዘክሩ ማስተዋሻዎችን ለማድረግ ተመቻችቷል ከመንገዱ መጨረሻ ያለውን መቃብር በንጹሕ ሣር ለማሣመር ተሰናድቷል ከመከራው መንገድ በኋላ ለስላሳ መስክ ይጠብቀናል ከዐርበኞቹ ተጋድሎ በኋላ ያገኘነውን ነጻነት ለማስታወስ ነው ምሽጉ ከውጭ ሲታይዩኒቨርሲቲው በቀጣይነት እቴጌ ጣይቱ በብልሃት ያስያዙትን ታሪካዊውን የማይ አንሽቲ ምንጭ ታሪካዊነቱን ጠብቆ አገልግሎቱን እንዲቀጥል ለማድረግ መወሰኑን በዕለቱ ገልጧልታሪካዊ ቅርሶች ጠባቂና ተከባካቢ ካላገኙ ወደ ተረትነት መቀየራቸው የማይቀር ነው ዩኒቨርሲቲዎቻችን ዩኒቨርሳል ነገሮችን ከማጉላት ይልቅ መንደራዊ ነገሮችን ወደ ማቀንቀን ከሚወርዱ እንዲህ ያሉ ሥራዎችን በመሥራት ታሪክ ዐውቆ ታሪክንም ጠብቆ ታሪክ የሚሠራ ትውልድ እንዲያፈሩ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ችቦውን ከፍ አድርጎታል
የዓድዋ ታሪክ ድል ብቻ ሳይሆን ዕዳም ነውምዕራባውያኑ አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመቀራመት በጀርመን በርሊን ከተማ ተማምለው ሲያበቁ ኢትዮጵያ በጣሊያን እጅ እንድትወድቅ ተፈረደባት ጀግኖች አባቶቻችን ግን ዓድዋ ትፍረደን አሉ የውጫሌ ስምምነት ይሏት አንቀፅ 17 እሳት አስጫረች ጦር አማዘዘች በኢትዮጵያውያንና ጣሊያን መካከል 1888 ዓ.ም በዚያን ወቅት ኢትዮጵያውያን ጦርና ጎራዴ ይዘው ለዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች እንግዳ የነበሩ አያቶቻችን ከታንከኛና ከመድፈኛ ጋር ጦርነት የገጠሙ እጆች የሰማይ በራሪ አውሮፕላኖችን እያዳሸቁ እንኩትኩት ሲያደርጓቸው ዓለምን ጉድ አስብለው አፋቸውን አስያዙ ፀሀፍትም ታሪኩ መራራ ቢሆንም ሊከትቡት ከብዕር ተናነቁ የዓድዋ ድል ጦርነት ዝምብሎ ጦርነትን አሸነፈ ተብሎ የሚፃፍ የሚዘከር አልነበረም አንዲት ጠብታ ውሃ ሰደድ እሳትን ከምድረ ገጽ እንዳጠፋች የሚነጻፀር እንጂ በዓድዋ ጦርነት ወቅት በርካታ የክፍለ አገር ገዥዎች እኔ እገዛ እኔ እገዛ በሚል ጦር ተማዝዘው ጠዋትና ማታ እርስ በእርስ ይጠዛጠዙ እንደነበር ይታወቃል ይሁንና ጠላት በመጣ ጊዜ የፖለቲካ ሽኩቻ አላገዳቸውም የሃይማኖት ልዩነት አልታያቸውምየፆታ ነገር አልገደ ባቸውም ሁሉም እምነቱ ሃይማኖቱ ሚስቱ ርስቱ ማንነቱ ሁሉ አገር ነበር ማን በአገር ይደራደራል አብዛኞቹ ጦርነቱ ሲጀመር ነገሩ የዳዊት እና ጎልድ ጨዋታ ይሆናል ብለው ገምተው ነበር እንደ ነዲድ እንጨት ለእሳት ተማግደው ማን ያሸንፈኛል ብሎ ከፊታቸው ተሰልፎ የነበረውን የጠላት ጦር አብረከረኩት ስንት ሕይወት ገብረው በስንት መከራ ተፈትነው ይኸው ነፃ ትውልድ ተፈጠረ አይ ጀግንነት አይ ወኔ! የዓድዋ ድልን ለኢትዮጵያውያን ሲያወሩት የሚያምር ለጠላት ግን እንኳንስ ሊያወሩት ቀርቶ ሲያስቡት መራር ነው የዓድዋ ድል በእርግጥ ዘላለማዊ ድል ነው የማይደበዝዝ ፍትህ ለተጠሙ የሚያበረታታ የማይጎመዝዝ የፅናት ተምሳሌት ነው ስለ ዓድዋ ዘላለም ቢጻፍ ቢተረክ የማያሰለች ከክፍለ ዘመን በፊት በጎልያድ እና ዳዊት መካከል የተካሄደ የጦርነት አምሳል ነው በጦርነት ወቅት ንጉሠ ነገሥት ኢትዮጵያ አፄ ምንሊክ ጠላት በአገራቸው በመጣ ጊዜ ክብሬ ማዕረጌ አላሉም በሃሳብ የማይስማሟቸውን ሰዎች አላራቁም በአገር ጉዳይ የጋራ ጠላት መጥቶብናል እና ኑ! አገራችንን ከወራሪ እናድናት ብለው ነበር ነጋሪት የጎሰሙትየዓድዋ ድል ማለት ልዩ ክስተት ነው በመሞት ውስጥ የኖረ ሕይወት ነው የዓድዋ ድል ማለት በማይነገር ረቂቅ ትዕይንት ውስጥ በሚጣፍጡ ቃላት አፍ በሚያስከፍት ድርሰት ተከሽኖ ጀግኖች የሚግባቡበት ቅቡል ቋንቋ ነው ዓድዋ ማለት ለጨለመባት አፍሪካ የብርሃን ወጋገን ያሳየ ማለት ነው ብቻ ዓድዋ! ማለት ከኢትዮጵያውያን በስተቀር ለቀሪው የዓለም ህዝብ ህልም የሚመስል ግን የተጨበጠ እውነት ነው በቃ ዓድዋ ብዙ ነው!በዚያን ወቅት የሮምን አደባባይ አስቧት በሀዘን ማቅ ተውጣለች በዚያን ወቅት አስቡት በዓድዋ ለአገራቸው ክብር መስዋዕት የሆኑ አባቶችና እናቶች አስከሬን ተረፍርፏል ግን የጀግና አስከሬን! እንኳንስ በሕይወት ኖረው ሞተው የሚያርበደብዱ የሀበሻ ጀግኖች!አባቶቻችን ለትናንት ማንነታቸው ሲጨነቁ የዛሬ ማንነታችንን አቆዩልን የትናንት ታሪክን ላለማጉደፍ ሲዋደቁ የእኛን ዛሬ ታሪክ አደመቁት ለዛ አበጁለት ዓድዋ ላይ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ደማቸውን አፍስሰው ነው ዛሬ የምንኖርባትን ምድር ያስረከቡን የምንግባባበትን ቋንቋ የምንጽፍበትን ፊደል የምንቀኝበትን ዜማ ያቆዩልን ከባዕዳን ባህልና ቋንቋ የታደጉን በትዕግስትና በብልሃት እንጂ በለው በለው! አሳድደው በሚል መርህ አይደለም ወጣቱ ከቀደምት አባቶች አንዳች ነገር ሊማር ግድ ይለዋል በዚህ ዘመን ጦርነት የለም ፌዴራላዊ ሥርዓት ተዘርግቶ ብዙሃንን ጨፍልቆ የሚኖርበት እድል የተመናመነ ይመስለኛል አባቶቻችን ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው አገርን ሊገነባ በሚችል አጀንዳ ላይ እንዴት እንደተጠመዱና ስምና ዝናቸውን አስከብረው እኛንም አስከብረው የኖሩ ስለመሆናቸው ማጤን ይገባልታዲያ ይህ ለዛሬው ትውልድ ዕዳ ነው ወራሪን ከአገር ለማስወጣት በአንድነት ያበረ ክንድ በአሁኑ ወቅት የተገላቢጦሽ ሆኖ አንዱን ሰው ከሌላ ክልል የመጣህ ነው ብሎ ማሳደዱ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ሆኗል ለመሆኑ ይህ ምን ይሉት ፈሊጥ ነው? አንዱ ያፈራውን ንብረት ሌላው እያወደመ አገሬ ብሎ ማቀንቀን ከወዴት የመጣ ፈሊጥ ነው? ታዲያ! ከ122 ዓመት በፊት የነበረ ንቃተ ህሊና ዛሬ ላይ ወደዬት ተሰወረ? እንኳንስ ለኢትዮጵያውያን ቀርቶ ለሚሊዮኖች የአፍሪካ ወንድምና እህቶች አርዓያ የሆ ነች አገር ስለምን ውጥንቅጦች ውስጥ እየገባች መጣች ብለን መጠየቅ ይገ ባል እንደ ቅጠል ረግፈው ያቆዩልንን አገር እንደ ቄጠማ አለምልመን ማስቀጠል እንጂ ጊዜው እንዳለፈበት የባህር ዛፍ ቅጠል ከመሬት ላይ መወ ርወር የለብንም ያሻገሩንን ባህር አል ፈን ትንሽዋ ኩሬ አስምጣን እንዳታ ስቀረን ሁላችንም በንቃት ማየት አለ ብን በእኔ እምነት ይህ ትውልድ በዓድዋ ድል ብቻ የመጣ ከፍሎ የማይጨርሰው ዕዳ አለበት በዚያን ዘመን አንድነቱን አጠናክሮ ጠላቱን ያልፈለሰፈ ህዝብ ዛሬ እንደምን ድህነትን ማሸነፍ ይሳነዋል እንዴት በባዶ እጁ በዓለም ጦረኛ የተባለን ሰራዊት ድባቅ የመታ ህዝብ የእለት ጉርስ ይቸግረዋል? እነዚያ አባቶቻችን ዛሬ ቀና ብለው ቢያዩን ምንኛ ባዘኑብን ምንኛ በተቀየሙን! አፅማቸው ይወቅሰናል በነገራችን ላይ የዓለም ታሪክ የአሸና ፊዎች ናት ዓድዋ ላይ አሸን ፈናል ግን ደግሞ አሁን ተሸንፈናል ቁጭት ርቆናል እልክ እና መነሳሳት ያንሰናል በጉንጭ አልፋ ክርክሮች ተጠ ምደናል ነገን ብሩህ ከማድረግ በዘለለ ትናንት ላይ ተጥደናል ዓድዋን መድገም እንዴት ይሳነናል? ይህን ግን መለወጥ ግድ ይለናል ሁላችንም በተመደብንበት ሞያና ኃላፊነት ላይ በአግባቡ ከሠራን ሁሌም ዓድዋ አለ ከምንምነት ወደ ስልጣኔ ማማ ከወጣን ሁሌም ድል አለ እኛ ለዚች ዓለም ህዝብ በውድ ዋጋ መሸጥ ከምንችለው ትልቁ ሃብታችን አንዱ የዓድዋ ድል ነው ማንም ሰው ቢመጣ ኮፒ ራይቱ የእኛ ብቻ የሆነ ነው የዓድዋ ድል የዓድዋ ድል ብንሸጠው የማያልቅ ሃብታችን ነው እናማ ኑ! እንሽጠው ዓድዋን እናስ ተዋውቅ ስለ ዓድዋ በተናገርን ቁጥር አልሸነፍባይነት ስነልቦናን በትውልድ ልብ ውስጥ ማኖር ነውና በወጣቱ ልብ ውስጥ አይበገሬነትን ማንገስና ታሪካችንን መና ገራችን ነውና የዓድዋን ድል ስንሸጠው ስንለውጠው ብንውል አይሰለችም ምክንያቱም ውድ ብርቅና ድንቅ ነው የጠንካራ ስነልቦና ተምሳሌትና የማይ ንበረከኩ አልሞ ተኳሽ አባቶቹን ጀብድና ገድላቸውን ማን አልሰማ ይላልና! ዓድዋን እንዘክረው እናስተዋውቀው እንማ ርበትስለዓድዋ ድል ከተናገርነውና ብዙዎች ከተናገሩት የታሪክ ድርሳናት ፍንትው አድርገው ከፃፉትና ከፃፍነው ሁሉ ገና ያልተነገረ ገና ያልተጻፈ አለ ወዲህ ደግሞ ይህን ታሪክ የሚያኮስስ ድህነት የሚባል ደንቃራ ከፊታችን ተገትሯል እናም ታሪካችን ሙሉ ይሆን ዘንድ ዛሬም ነገም መትጋት አለብን ዛሬ እየሞትን ሳይሆን እየኖርን ታሪክ መስራት የምንችልባቸው አጋጣ ሚዎች በርካቶች በመሆናቸው ሁላችንም ኃላፊነ ታችን ልንወጣ ይገባል በትናንት ታሪክ ብቻ የምንኩራራ ህዝቦች ሳንሆን ከትናንት ታሪክ የሚቀጥል ሌላ የታሪክ ምዕራፍ መክፈት ይገባናል ግዴታችንም ነው እርሱም ድህነትን ታግሎ ማሸነፍ የሆነው ሆኖ ግን በ21ኛው ክፍለዘመን ውስጥ ሆነን እንደ 19ኛው ክፍለ ዘመን ማሰብ ግድ ባይለንም ታሪክን መዘንጋት ግን አይገባም በዚያን ዘመን ግፍ እና ሰቆቃ ያደረሱብንን ሰዎች አንርሳቸው ቂም ግን አንያዝባቸውክፍለዮሐንስ አንበርብር,
የአድዋ ድል: ከጦር አውድማ የተሻገረ የአባት አያቶቻችን ገድልአድዋ ጫማችንን አውልቀን የምንቆምበት የአፍሪካ የተቀደሰ ስፍራ ነው ዩዌሪ ሙሴቪኒጥንት አባቶቻችን እንደ አንድ መክረው እንደ አንድ ወስነው በአንድ ወኔና ተነሳሽነት እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣን ወራሪ ሃይል መመከት የቻሉበት የአድዋ ድል በአል እነሆ 122ኛው ዓመት ላይ ደረሰ እዚህ ግባ በማይባል የጦር መሳሪያ ሳይኖር ነገር ግን የህብረት ክንድ ባጠነከረው ወኔ አባት አያቶቻችን ያስመዘገቡት ድል በአስገራሚነቱ እስካሁንም አነጋጋሪ እንደሆነ ነው የዛሬ 122 አመት የተፈፀመው የጦር ሜዳ ገድልን በወቅቱ የነበሩ ታዋቂ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ብዙ ብለውለታል በየዓመቱም በሚካሄደው የድል በአል አከባበር ላይ የአፍሪካም ሆነ አለም አቀፍ ሚዲያው ስለ አድዋ ፅፈውና ተናግረው ሊጨርሱ አልቻሉም በተለያዩ ጊዜያትም አድዋን እያነሱ ለህዝባቸው አልበገር ባይነትንና አሸናፊነትን እያስተማሩበት ይገኛሉ የሃገር መሪዎች ሳይቀሩ ስለ አድዋ ዘመን ተሻጋሪ አስተያየቶችን ሰጥተውበታል በተለያዩ ጊዜያት የትኞቹ መገናኛ ብዙሃን ስለ አድዋ ምን አሉ የሚለውን ቀጥለን እንመልከት የአድዋ ድል የአለማችንን ታሪክና ፖለቲካ ከላይ ወደ ታች ግልብጥብጡ እንዲወጣ ያደረገ የኢትዮጵያውያን ብሎም የአፍሪካውያን ድል ነው ሲል ስለ አድዋ ዘገባው ላይ ያነሳው ኦሪጅንስ ዶት ኮም አውሮፓውያን በአፍሪካውያን ላይ ይዘውት የቆዩትን አመለካከት የቀየረ እንደነበርም አስታውሷልየአድዋ ጦርነት ዝም ብሎ ከተራ ትርክት የሚመደብ ጦርነትም አይደለም በማለት ሃሳቡን ያጠናከረው የድረ ገፁ ፀሃፊ በአንድ ወቅት የአድዋ ጦርነትን አስመልክቶ ብዕሩን ያነሳውን ሬይሞንድ ጆናስ የተባለን ፀሃፊ ሃሳብ ይጋራል ሬይሞንድ ጆናስ የጦርነቱን የኋላ ዳራ ጦርነቱንና ከጦርነቱ በኋላ የነበሩ ክስተቶችን ግልፅ አድርጎ በብዕሩ የከተበ የታሪክ ፀሃፊ ነው ፀሃፊው የአድዋን ጦርነትና ከዚያም በኋላ የተገኘው ድል አመጣ ባላቸው ሶስት ጉዳዮች ላይ ተመርኩዞ ይገልፃቸዋልእንደ ፀሃፊው አድዋ የቅኝ ገዢነት አስተሳሰብን የገታ የጣሊያን ቅኝ ገዢን ጉልበት በአርበኝነት ተጋድሎ ያሽመደመደ ነው የወራሪው የጣሊያን ጦርን ቅስም የሰበረ በወቅቱ የነበረውን የጣሊያን ገዢ ሃይል በራሱ ተማሪዎች ቪቫ ምኒሊክ እንዲሉ ያስገደደ ድል ነው የአድዋ ድል የአድዋ ድል በወቅቱ የአፍሪካን አህጉር ይዞ ሲበዘብዝ ለነበረው የቅኝ ወራሪ ሃይል ትልቅ ትምህርትን ያስተላለፈ መሆኑን ፀሃፊው እንደ መጀመሪያ ጉዳይ ያነሳል በሁለተኛነት የአድዋ ድል የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ጥበበኛና ሊገለፁ የማይችሉ ታሪካዊ መሪ እንዲሆኑ ያስቻለ መሆኑን ሬይሞንድ ይጠቅሳል የጦር ጀግኖች ድልን ባጣጣሙበት ቅፅበት ሰዋዊ አስተሳሰባቸውን ያጡና ሌሎች ያልተገቡ ድርጊቶችን ሲፈፅሙ ማየት ሰርካዊ በሆነባት አለም አጼ ምኒልክ ምርኮኞቻቸውን የያዙበትን ሂደት ፀሃፊው ለአድናቆት እንዲንደረደር እንዳደረገው ፅፏል የባለቤታቸውን የእቴጌ ጣይቱ ብጡል ጠንካራ ድጋፍ ስራ ላይ በማዋል ውጤታማ እንዳደረጋቸውና ይህም የአጼ ምኒልክን ብልህነት የሚያሳይ ነው የአጼ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ የጀግንነት ተግባር ስፔንን አንድ ካደረጉት ባልና ሚስት ፈርዲናንድና ኢዛቤላ ጋር በማገናኘት ፀሃፊው ገልፆታል ህዝቡን ለአንድ አላማ በጠንካራ ተነሳሽነት አንዲተም በማድረግ ለአለም ህዝብ አስገራሚ የድል ብስራትን ያወጁ መሪ መሆናቸውንም ፀሃፊው የአጼ ምኒልክን ብልህነት ከገለፀባቸው ጉዳዮች መካከል ነው ሌላውና ፀሃፊው በሶስተኛነት ያነሳው ጉዳይ የአድዋ ድል ለአፍሪካውያን ብሎም ለአፍሪካ አሜሪካውያን የፓን አፍሪካ እንቅስቃሴ ምልክት መሆኑን ነው የአድዋ ድል አጼ ምኒልክ በትረ ስልጣናቸውን አጠናክረው የሃገራቸውን ነፃነት እንዲያስከብሩ ያደረጋቸው ሲሆን ለፓን አፍሪካን ራዕይ አቀንቃኞች ደግሞ በተምሳሌትነቱ የሚጠቀስ ነው ለዚህም ይመስላል እኤአ በ1904 የሃይቲው የፓን አፍሪካ ባለ ራዕይ ቤኒቶ ሲልቪያን እንደ ሌላኛዋ ሃገሩ ወደሚቆጥራት ኢትዮጵያ መምጣቱ ሃይቲ በ18ኛው ክዘመን መባቻ የመጀመሪያዋ የተሳካ የጥቁሮች አብዮት የተካሄደባት ሃገር መሆኗን ፀሃፊው ሳይዘነጋ ያነሳል የአድዋ ድል በአለም ታሪክ ውስጥ ነጮች ስለ ጥቁሮች እንዲሁም ጥቁሮች ስለ ነጮች ከድሉ በፊት የነበራቸውን አመለካከት የቀየረ ትልቁ የለውጥ መዘውር ነው በማለት ፀሃፊው ሃሳቡን ቋጭቷልአፍሪካ ከአድዋ ድል ልትወስዳቸው የሚገቡ ትምህርቶች በርካታ ናቸው ሲል ስለ አድዋ ድል ምስክርነቱን የሚሰጠው የሩዋንዳው ኒው አፍሪካን ጋዜጣ አጼ ምኒልክ በሃገር ውስጥ የነበረባቸውን ልዩነት ትተው በወቅቱ በየራሳቸው የጦር ሃይል የነበራቸውን የየአካባቢ ገዢዎች በማስተባበር አንድ መቶ ሺ ሰራዊት አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ማስድረጋቸውን እንደ አንድ ማሳያ ያነሳልሌላኛው መቅሰም የሚገባው ትምህርት ብሎ ያነሳው ደግሞ አጼ ምኒልክ የባለቤታቸውን እገዛ ቸል አለማለታቸውና በውጫሌ ስምምነት ወቅት የተፈጠረውን ጉዳይ እንዲከታተሉ ሃለፊነቱን ለእቴጌ ጣይቱ መስጠታቸውን ከብልህነት ፅፎላቸዋል የአፍሪካ ሃገራት የውል ስምምነት contract agreement ሲገቡ መውሰድ የሚገባቸውን ጥንቃቄ ለአድዋ ጦርነት በመንሰኤነት የተጠቀሰው የውጫሌ ውል ሂደት ትልቅ ትምህርት ሊሆናቸው እንደሚችል ኒው አፍሪካን ጠቅሷል ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት በኋላ አፍሪካውያን ከምዕራባውያን ጋር በሚገቡት ጥንቃቄ የጎደለው ውል ሳቢያ የአፍሪካን ሃብት መቀራመቱን የተለመደ አድርገውት እንደቆዩ ዋቢ አድርጓል የአፍሪካን ታሪክ ለመረዳት የአድዋን ጦርነት ታሪክ መገንዘብን ይጠይቃል ያለው ኳርትዝ አፍሪካ በጦርነቱ በሁሉም ሁኔታ የኢትዮጵያውያን አሸናፊነት የታየበት እንደነበር እማኝነቱን ሰጥቷል ለዚህም ዘ ኒውዮርክ ታይምስ እኤአ ማርች 2 ቀን 1896 ኢትዮጵያውያን በጣሊያናውያን ላይ የፈፀሙትን ታላቅ የጀግንነት ተግባር በሚያወሳውና Abyssinians defeat Italians: Both wings of Baratieris army enveloped in energetic attack. በሚል ርዕስ ያሰራጨውን ዘገባ በአስረጂነት ተጠቅሞበታል ሽንፈቱን የተከናነበው የጣሊያን ወራሪ ሃይል 3ሺ የጦር ሃይል አባላቱን ሲያጣ 60 መሳሪያዎችን ጨምሮ በሁሉም የጦር ክፍሉ ላይ ከባድ ኪሳራ እንደደረሰበት ኒውዮርክ ታይምስ በቀጣይ እትሙ ላይ ይዞት ወጥቷል የኢትዮጵያውያኑ የጦር ሜዳ ውሎ ስኬትና ጀግንነት በበርካታ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በስፋት ተዘግቦ እንደነበርም የታሪክ ድርሳናት ከትበውት ይገኛልየኢትዮጵያውያን ድል ቅኝ ገዢዎች በአፍሪካ ላይ የነበራቸውን እሳቤ ከመሰረቱ የቀየረ ከመሆኑም ባለፈ ታላቅ የኋላ ዘመን ታሪካዊና ፖለቲካዊ ክስተቶች እንዲፈጠሩም ያደረገ ነበር አፍሪካውያን በፀረ ቅኝ አገዛዝ ተጋድሎ ውስጥ በቅኝ ገዢዎቻቸው ላይ ስኬታማ ውጤት ሊያስመዘግቡ እንደሚችሉ የተነበየ ብሎም ያሳየ ድል ነው ሲል ኳርትዝ አፍሪካ ገልፆታልየሱዳኑ ሱዳን ትሪቡን በአንድ ወቅት የአድዋ ድልን አስመልክቶ ባስነበበው እትሙ በወቅቱ እጅግ ኋላ ቀር መሳሪያ የታጠቀው የኢትዮጵያ ጦር በአስገራሚ ወኔ በጊዜው ገንዘብ ሊገዛው የቻለውን መሳሪያ የታጠቀውን የጣሊያን ጦር ማሸነፉን ፅፏል በጣሊያን በኩል ሙትና ቁስለኛ የሆነውን ሃይል ሱዳን ትሪቡን ሟቾቹን 7ሺ እንዲሁም ቁስለኞቹን ደግሞ 1ሺ 500 መሆናቸውን ይገልፅና 3ሺዎቹ መማረካቸውን ያሳያል እኤአ በ1896 ዓ.ም የኢትዮጵያውያን ጀግንነት ያሳየው የአድዋ ድል የወራሪው የጣሊያን ጦር በሁለቱም የአለም ጦርነቶች ሽንፈትን እንዲከናነብ ጥላውን እንዳጠላበትም ጋዜጣው አክሏልየቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ በያመቱ ሜይ 25 በሚከበረው የአፍሪካ ቀን ጉባኤ ላይ ተገኝተው ስለ አድዋ በአል ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል ምቤኪ የአድዋ ጦርነት የኢትዮጵያ ነፃነት እንዲቀጥል ከማድረጉም ባሻገር ሀገሪቷ በወቅቱ በቅኝ ግዛት እንደተያዙት ሃገራት እንዳልሆነች ያሳየችበትም ጭምር እንደሆነ የገለፁበት ሁኔታ በአፅንኦት ሊጠቀስ የሚገባው ነውየበርሊኑ ጉባኤ አፍሪካ በቅኝ አገዛዝ ውስጥ መውደቅ እንዳለባት ሲወስን ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አፍሪካ በቅኝ ግዛት ቀንበር መያዝ የለባትም አሉ ተሳካላቸውም ነበር ያሉት ምቤኪ ተሰብሳቢውን ባስደመሙበት ንግግራቸውየኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ በአድዋ ድል ክብረ በአል ላይ በተገኙበት ወቅት በአድዋ ድል በአል አከባበር ስነ ስርዓት ላይ በመገኘታቸው ብቻ ክብር እንደሚሰማቸው ተናግረው ለድል በአሉ ምን አይነት ክብር መስጠት እንዳለባቸው እንዲህ ብለው ነበር ...ጫማዬን ማውለቅ ይኖርብኛል ምክንያቱም ይህ የተቀደሰ ስፍራ ነው አድዋ የአፍሪካ የተቀደሰ መሬት ነው አድዋ የአፍሪካን የውርደት ሸማ የገፈፈ ነው አፍሪካ በውጭ ወራሪ ሃይል ተይዛ በቅኝ ግዛት ተይዛ ነበር ብለው የሚያስቡ ሰዎች ሃፍረት ሊሰማቸው ይገባልየአድዋ ድል በአል ከዚህም በበለጠ የተቡ ብዕሮች ሊፅፉለት የሰሉ አዕምሮዎች ጥልቅ ጥናት ሊያደርጉበት ርቱዕ አንደበቶች ሊናገሩለት ይገባል የአሁኑ ትውልድም ጥንት አባት አያቶቹ የሰሩትን ገድል ከማወቅ በዘለለ በተግባር እንዲኖራቸው ማድረግ ከሁሉም የቀደመ ተግባራችን መሆን አለበት ደራሲዎቻችን የኪነ ጥበብ ባለሙያዎቻችን አልፎ ተርፎም የፖለቲካ ሰዎቻችን ወጣቱ ትውልድ ሰርክ አባቶቻችን ዘር ቀለም ቋንቋ ሳይገድባቸው የሰሩትን ገድል እንዲገነዘብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል
አድዋ 122ኛዉን የአድዋ ድል በአል ለማክበር ዝግጅቷን አጠናቃለች የአድዋ ከተማ ታሪካዊዉን የአድዋ ድል 122ኛ አመት በድምቀት ለማክበር በርካታ ዝግጅቶችን ማጠናቀቋን በስፍራዉ የተገኘዉ የዋልታ ባልደረባ ዘግቧልዘጋቢያችን ከስፍራዉ እንደገለፀዉ በዛሬዉ እለት የአድዋ ተራሮችና የአድዋ ድል ቱሪዝም ፕሮጀክት ተመርቋል የአድዋ ድልን ታሪካዊ ዳራና ሌሎች ከዚህ ድል ጋር ተያያዥ የሆኑ ጭብጦችን ለማስተላለፍ ያለመ የፎቶ አዉደ ርእይ መካሄዱም ታዉቋልበአድዋ ተራሮችና የድል ቦታዎች ጉብኝት መካሄዱም ተመልክቷልየፓናል ዉይይትና የጎዳና ላይ ትርኢቶችም እንዲሁ በበአሉ አከባበር መርሃ ግብር ዉስጥ መካተታቸዉን ለማወቅ ተችሏልበአሉን ለማክበር እንግዶች የአገርዉስጥና የዉጭ ጎብኝዎች የመንግስት ባለስልጣናትና የስራ ሃላፊዎችአባት አርበኞች የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ሌሎች ወደከተማዋ መግባታቸዉም ተገልጿል
የአድዋ ድል የመላው አፍሪካና የጥቁር ህዝቦች ድል ነው ...በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርየካቲት 232010 የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካና የጥቁር ህዝቦች ድል መሆኑን በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ቪልማ ቶማስ ተናገሩ አምባሳደሯ ይህን ያሉት122ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ በተከበረበት ወቅት ነውአምባሳደሯ ይህን ታላቅ በዓል ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በማክበራቸው መደሰታቸውንም ነው በተለይ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የገለጹትበበዓሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መታደማቸውን የተናገሩት አምባሳደሯ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች የአገራቸውን ባህል በሚገልጽ አለባበስና በደመቀ ሁኔታ ሲያከብሩ መመልከታቸው አስደስቷቸዋልኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ይህ ታላቅ ድል በመላው ዓለም በቀኝ ያልተገዛች ሃገር ሆና ስሟን እያስጠራት እንደሚገኝ አምባሳደሯ ተናግረዋልየአድዋ ድል በአል የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካና የጥቁር ህዝቦች ድል በመሆኑ ትልቅ ደስታና ኩራት እንደሚሰማቸው አስታውቀዋልኢትዮጵያውያን ይህንን አንድነታቸውንና አሸናፊነታቸውን ድህነትን ድል በማድረግ መድገም አንደሚገባቸውም ገልጸዋልየኩባ ዶክተሮችና መምህራን በኢትዮጵያ በጤናና ትምህርት ዘርፎች ላይ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል የሁለቱ አገሮች ወዳጅነትና ግንኙነት በቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አምባሳደሯ አመልክተዋል
የአድዋ ድል በእድል ሳይሆን በአባቶች መስዋዕትነትና በአገር በቀል ወታደራዊ ሳይንስ የተገኘ ነው አቶ ረመዳን አሸናፊየአድዋ ድል በእድል ሳይሆን በአባቶች መስዋዕትነትና በአገር በቀል ወታደራዊ ሳይንስ የተገኘ ነው ሲሉ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ረመዳን አሸናፊ ተናገሩ122ኛው የአድዋ ድል በዓል ትናንት በብሔራዊ ቴአትር በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯልአድዋ ከዘመኑ የቀደመ ለአገር ዳር ድንበር መከበር እምነት ቋንቋ ዘር አስተሳሰብና ጾታ ሳይለያቸው የአገር ፍቅር ከሩቅም ከቅርብም የጠራቸው ኢትጵያውያን ወራሪ የጣሊያን ጦርን ድባቅ የመቱበት የደምና የአጥንት ክፍያ ዋጋ ነውጥቁር የነጭ የበታችና አሽከር ተደርጎ በሚታሰብበት ዘመን ኢትዮጵያውያን አንደፈርም እምቢ ለአገሬ! በማለት ታላቅነትን የጻፉበት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ሲታወስ ልክ አድዋ ላይ ሰንደቃችን ከፍ ብሎ በክብር ይውለበለባልአድዋ የጥቁር ሕዝቦች አንድነት የአመራር ብቃት ሕብረት ፍቅርና ጀግንነት የታየበትና ሌላው ዓለም እውነትም ጥቁር ማለት! ብሎ የተገረመበት የድል ቀን ነውአድዋን ስናስብ ኢትዮጵያውያን ከጭቆና ቀንበር በአጥንታቸውና በደማቸው መስዋእትነት ነጻ መውጣታቸው ብቻ አይደለም የሚጎላው ከወራሪ ነጮች መዳፍ ውስጥ መውጫ አጥተው የነበሩ ሕዝቦች የትግል ምልክትና የነጻ መውጣት መለከት መሆኑም ጭምር እንጂየባሕልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ጋር በመሆን ዛሬ ባዘጋጁት መድረክ 122ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯልበዓሉ አድዋ የአብሮነትና የአንድነት ተምሳሌት በሚል መሪ ቃል ነው የተከበረው በበዓሉም አመራሮች የአባት አርበኞችና ሌሎች ተጋባዦች ተገኝተዋልየባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ረመዳን አሸናፊ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የአድዋ ድል ለመላው ዓለምና በተለይም አፍሪካዊያን ከባርነት እንዲላቀቁ ምሳሌ ነው ብለዋልበመሆኑም የአድዋ ድል በዓል መታወስና መዘከር ያለበት የድል ቀን ነው ብለዋልየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር አቶ መሳይ ደምሴ የአድዋ ድል በዓል ኢትዮጵያውያን አባቶች ለሀገራቸው ያላቸውን ክብር ያሳዩበትና ለቀሪው ዓለም ወደ ነጻነት መውጫ የዘረጉት ድልድይ ነው ይላሉበመሆኑውም የአድዋ ድል ከመቼውም በላይ ክብርና ልዕልና የሚገባው የማንነታችን መኩሪያና መታወቂያ ነው ብለዋልበዚህ ለ122ኛ ጊዜ ዛሬ በተከበረው የአድዋ ድል በዓል ላይ ግጥሞች ቀርበዋል መነባንቦች ተነብንበዋል ሙዚቃዎችም ተሞዝቀዋልበቀጣይ ቀናትም ሌሎች የአድዋን ድል የሚዘክሩና የሚያስታውሱ ዝግጅቶች በመላ ሀገሪቱ ይከበራሉ
ከዓድዋ ምን - እንዴት እንማር? Featuredየዓድዋ ድል የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት መሆኑን የኢትዮጵያውያንን የአድዋ ውሎ ከዘከሩ የታሪክ ጠበብት መካከል የዋሽንግተኑ የታሪክ ሊቅ ፕሮፌሰር ራየሞንድ ጆናስ ዘ ባትል ኦፍ አድዋ-አፍሪካን ቪክትሪ ኢን ዘ ኤጅ ኦፍ ኢምፓየር በሚለው ጽሁፋቸው አስፍረዋል ፕሮፌሰሩ በዚህ ጽሁፋቸው የአድዋ ድል ለአፍሪካውያን ቅኝ አገዛዝን ታግሎ መጣል እንደሚቻል ያሳየ የኢትዮጵያንም ታላቅነት ያስመሰከረ ስለመሆኑ ደጋግመው ያወሳሉዓድዋ ለእኔ ነጻነቴ ነው ክብሬም ነው የሚሉት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን በ1888 ዓ.ም የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያንን ጀግንነት ያሳየ ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ህዝቦች የአሸናፊነት መንፈስን ያጎናጸፈ መሆኑን ይገልጻሉኢትዮጵያ የራሱ የሆነ ባህል ታሪክና ማንነት ያለው በራሱ ቋንቋ የሚናገር ህዝብ ያላት አገር እንደሆነች ለዓለም ህዝብ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመሰከረችበትም እንደሆነ ያብራራሉ ህዝቡ በየአካባቢው በራሱ ባህል የሚኖር እርስ በእርሱ የሚጣላ እንኳን ቢሆን የውጭ ወራሪ ሲመጣበት ልዩነቱን ወደጎን ትቶ በአንድ የሚተባበር በአገሩ ጉዳይ ላይ የማይደራደር መሆኑን ጠላት በሚገባ የተገነዘበበት ድል መሆኑንም ያስረዳሉዓድዋ ሲከበር ውስጤ የደስታ ስሜት ብቻ ሳይሆን ኩራትም ይሰማዋል ለአያት ቅድመ አያቶቻችን ትልቅ ዋጋ መስጠት እንዳለብን ይነግረኛል የሚሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር አቶ ሲሳይ መንግስቴ ናቸው የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ስልጣኔ ጀግንነትና ብልህነት ለነጮች ብቻ የተተወ ይመስላቸው ለነበሩ አፍሪካውያን ሁሉ የነጻነት ጮራ የፈነጠቀ የይቻላል መንፈስ ያሰረጸ እንደሆነም ያምናሉየኢኮኖሚና ፖለቲካ ሙሁር የሆኑት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸ ደግሞ የዓድዋ ድል ለመላው ጥቁር ህዝብ ደስታ የፈጠረውን ያህል አውሮፓውያንን ያስደነገጠም እንደነበር ይናገራሉ እርሳቸው እንደሚሉት የአድዋው ድል ኢትዮጵያ ምንጊዜም በልጆቿ ተጋድሎ ነፃነቷ ተከብሮ ታሪኳና ባህሏ ተጠብቆ እንደኖረና እንደሚኖር ያረጋገጠ ነው ሆኖም ግን የአድዋን ድል በዓመት አንድ ቀን በሚካሄድ ስብሰባ ከመዘከር ባለፈ ትውልዱ በሚፈልገው ልክ እንዲረዳው አልተደረገምልጅ ዳንኤል ጆቴ በበኩላቸው እንደሚናገሩት የአድዋ ጦርነት ወራሪ ጦር ድል የተመታበት ሲሆን የአሁኑ ጦርነት ደግሞ ድህነትን ድንቁርናን ሙስናና ብልሹ አሰራርን ታግሎ የማሸነፍ ነው እነዚህን ችግሮች ማሸነፍና ነገን እውን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ ለዛሬነታችን መሰረት የሆነውን ትናንትን ስናውቅና ዛሬን በትክክል ስንሰራ ነውወጣቱ የኢትዮጵያ የሰላምና የነጻነት ሰንደቅ ዓላማ በእጁ ነው ይሄን መሬት ላይ ቢጥለው አብሮ ይከሰከሳል የሚሉት ልጅ ዳንኤል ወጣቱ ከአድዋ ድልና ከድሉ ባለቤት ጀግኖች ይቻላል የሚለውን የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ተላብሶ ችግሮችን ለመፍታት ከራሱ መጀመርና በሚያከናውነው ተግባር ጥቅም ለማግኘት ሳይሆን አገራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ብሎ መስራት እንዳለበት ይመክራሉ ለዚህም የአድዋ ጀግኖች ከየአቅጣጫው ወደአድዋ የተመሙት ከንጉሱ ወይም ከመንግስት ጥቅም እናገኛለን ብለው በማሰብ ሳይሆን አገርን ሊወር የመጣን ጠላት አንገት አስደፍቶ ከአገር ማባረርን ዓላማ አድርገው የአገር ክብርና የወገን ዝናን አስቀድመው እንጂ በማለት በአብነት ይጠቅሳሉአቶ ሲሳይም መንግስቴም በዚህ ሀሳብ ይስማ ማሉ እርሳቸው እንደሚሉት ዓድዋ ፖለቲካዊ ነጻነታችንን አረጋግጦልን ያለፈ ቢሆንም በዚህ ዘመን ፖለቲካዊ ነጻነት ብቻ በቂ አይደለም የዳበረ ኢኮኖሚ መፍጠር ያስፈልጋል ለዚህም ከአድዋ ጀግኖች መተባበርን ጽናትንና አሸናፊነትን ለመማርና ሀላፊነትን ለመወጣት የሁሉም ዜጋ በተለይም የወጣቱ ተሳትፎ ወሳኝ ነውየዓድዋ በዓል ለእኔ ከሁሉም በዓላት በላይ ነው ምክንያቱም የነጻነት ዋጋ ያጣጣምንበት ነጮችን ማሸነፍና ማንበርከክ እንደሚቻል ያሳየንበት ነው ይሄን ካሰብን ዓድዋ የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች በዓል ነው የሚሉት አቶ ሲሳይ የመንግስት ባለስልጣናት የፓርቲ አባላትና መሪዎች የሃይማኖት አባቶች ትምህርት ቤቶችና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአጠቃላይ ሁሉም ዜጎች ሊያከብሩት ሊጠብቁትና ሊያስቡት ለመጪውም ትውልድ ሊያስተላልፉት እንደሚገባ ይገልጻሉ ይሁን እንጂ እርሳቸው እንደሚናገሩት በዓሉ እንደ ታላቅነቱና እንዳለው ብሄራዊ ፋይዳ በደመቀና ሁሉንም በሚያንቀሳቅስ መልኩ እየተከበረ አይደለም አፄ ኃይለስላሴ ለንግሥ በዓላቸው ደርግም ለመስከረም ሁለት ይሰጡ የነበረውን ትኩረት ያህል ለአድዋ በዓል ሲሰጡ አልተስተዋሉም አሁንም ቢሆን ለሌሎች በዓላት ለድርጅቶችና ተቋማት ምስረታ በዓላት የሚሰጠውን የሚዲያ ሽፋን የዶክመንተሪና ሌሎች መርሃ ግብሮች ለአድዋ በዓል እየተሰጠ አለመሆኑን ያወሳሉይህን ሀሳብ የሚጋሩት ዶክተር ቆስጠንጢኖስም አሁን አንዱ የሚያስደነግጠው ነገር ድሮ የነበሩና ኢትዮጵያ የምትባል አገር ያስረከቡንን መሪዎቻችንን ማሞገስና መዘከር እንደተከለከለ አይነት ነው የማየው ምክንያቱም በስም እየተጠቀሱ ሲወገዙ እንጂ መልካም ስራቸው ሲነገር አይሰማም በየአደባባዩም የእነዚህን የአገር ባለውለታ መሪዎች ሳይሆን የተለያዩ ድርጅቶችን ማስታወቂያዎችና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሰዎችን ሀውልት እየሰራን ነው ያለነው ሲሉ ገልጸዋል በአንድ ወቅት ጥቁሮችና ነጮች በአንድ አውቶቡስ የማይሄዱባት አሜሪካ አሁን በጥቁር እየተመራች ወደታላቅነት ስትገሰግስ እኛ ግን በ18ኛውና 19ኛው ክፍለ ዘመን በነበረ አስተሳሰብ በታሪካችንና ማንነታችን እንጨቃጨቃለን ይህ ሲታይ ከአድዋ ታሪክ የወሰድናቸው ነገሮች አሉ ለማለት አልደፍርም ይላሉአቶ ሲሳይ በበኩላቸው በየዘመኑ ስልጣን ላይ የሚቀመጡ መንግስታትና ፖለቲከኞች አድዋን ባሰቡ ባከበሩና ባገዘፉ ቁጥር የእነርሱ ክብር የሚደፈቅባቸው ስለሚመስላቸው ብዙ ትኩረት ሲሰጡት አይታይም ሲሉ ይወቅሳሉ ሚዲያውም ባለስልጣናቱን ተከትሎ ስለሚሄድ በተመሳሳይ ትኩረት አለመስጠቱንም ይተቻሉ በመሆኑም የፌዴራል መንግስቱም በአግባቡ አስቦበት ሊያከብረውና መልዕክት ሊያስተላልፍበት የክልል መንግስታትም ይህን መሰሉን ብሔራዊ በዓል ቢያንስ ከክልል በዓላት እኩል ቢያዩት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ያብራራሉለምሳሌ አጼ ምኒልክን የአንድ ጎሳ መሪ እንደነበሩና ሌላውን በቅኝ ግዛት ሲይዙና ሲጨቁኑ እንደነበረ ብቻ ነው የሚታየው እንጂ አገር እንዳቀኑ ጣልያንን አሸንፈው ለአፍሪካም ኩራት እንደሆኑ ኢትዮጵያ የሚባል ካርታን መስርተው እንዳለፉ አይደለም እየተነገረ ያለው የሚሉት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ይሄንኑ ሀሳብ ያጠናክራሉ ሆኖም ከዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ወጥቶ ታሪክ በጥሩነቱም ሆነ በመጥፎነቱ ህዝቡ እንዲያውቀው ቢደረግ ከመጥፎው እንዲማር ጥሩውን ደግሞ እንዲያዳብረው የሚያስችል መሆኑን ይመክራሉበኢትዮጵያውነታችን ለሚያኮራንና በብዙ መስዋዕትነት ለተገኘው ድል ተገቢውን ክብር ሰጥቶ ትውልዱን በማስተማር እንዲሁም የታሪክ ሙሁራን ተገቢውን መረጃ በመሰብሰብ ታሪኩን በመሰነድ እንዲተላለፍ በማድረግ ትውልዱ ትክክለኛ ታሪክ እንዲይዝና ከታሪኩ ተምሮም የተሻለ አገራዊ ድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እንደሚገባ ነው ሙሁራኑ የሚመክሩት
122ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመላ አገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው አንድ መቶ ሃያ ሁለተኛው የአድዋ ድል በዓል በድምቀት እተከበረ ነውበተለይም ጦርነቱ በተካሄደበት ዓድዋ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አባት አርበኞች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ነውየሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት የማርሽ ቡድንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር አርቲስቶች የአደዋን ገድል የሚገልጹ ልዩ ልዩ ትርኢቶችን በማቅረብ ላይ ይገኛሉበመዲናችን አዲስ አበባም በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከጠዋቱ 12 ሰዓት መድፍ ተተኩሷልበአሁኑ ሰዓት ደግሞ በዓሉን ለማክበር በአፄ ሚኒሊክ አደባባይ የተሰባሰቡ የመዲናዋ ነዋሪዎች በዚሁ አካባቢ የተዘጋጀውን የፎቶ አውደ ርዕይ በመጎብኘት ላይ ናቸውበአውደ ርዕዩ ለነጻነት የተዋደቁ ጀግኖች ሰማዕታት ጥንታዊ የጦር መሳሪያዎችና በወቅቱ የነበሩ የጣሊያን ጦር አዛዦች ፎቶዎች ለዕይታ ቀርበዋልየኤፌዴሪ መከላከያና ፌደራል ፖሊስ ማርች ባንዶችም በአደባባዩ ዙሪያ ልዩ ልዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማሰማት ላይ ናቸውየጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር አባላት በጥንታዊ የክብር ልብሶቻቸው ተውበው የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለቡ በአደባባዩ ዙሪያ ደስታቸውን በፉከራና ሽለላም ጭምር እየገለጹ መሆናቸውን በቦታው የሚገኘው ሪፖርተራችን ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል
የአድዋ የድል በዓል በአርባ ምንጭ ከተማ በፓናል ውይይት ተከበረ የሉአላዊ አንድነታችን ተምሳሌት የሆነውን የአድዋ ድል ወጣቱ ትውልድ ድህነትን በማሸነፍ ሊደግመው እንደሚገባ የጋሞ ጎፋ ዞን አስተዳዳሪ ገለጹ122ኛው የአድዋ የድል በዓል ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯልየዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢሳያስ እንድሪያስ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የአድዋ ጦርነት በኢትዮጵያዊያን ድል ሊጠናቀቅ የቻለው ህዝቡ ሉዓላዊነቱን ለማስጠበቅ በአንድነት በመዝመቱ ነውኢትዮጵያዊያን አባቶች በአድዋ ሜዳ ጠላትን ለማሸነፍ ያስተባበሩት የጋራ ክንድ አዲሱ ትውልድም ድህነትን ለማሸነፍ ተባብሮ በመስራት መድገም አንዳለበት አስገንዝበዋልየአድዋ ድል በአገራዊ ሉአላዊነት የማንደራደር ህዝቦች መሆናችንን ያሳያል ያሉት አስተዳዳሪው ወጣቱ ትውልድ ይህንን አኩሪ ታሪክ በአግባቡ እንድያውቅ ወላጆች ልጆቻቸውን የማስገንዘብ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋልከበዓሉ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ጴጥሮስ ሰኞ እንደተናገሩት አዲሱ ትውልድ ስለ አድዋ ድል ተገቢው እውቀት እንዲኖረው በወጣት ማዘውተሪያዎች የተደራጁ መረጃዎች ሊቀመጡ ይገባልሌላኛው ተሳታፊ አቶ ተስፋዬ አልቦ በበኩላቸው ሁሉንም ኢትዮጰያዊ በአንድነት ያሳተፈውን የአድዋ ጦርነት የድል ታሪክ ወጣቱ ትውልድ ተገንዝቦ የራሱን ታሪክ እንዲሰራ በማድረግ ረገድ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋልበበዓሉ የአድዋን ድል የሚዘክር ሰነድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ከዞን ሴክተር የተውጣጡ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል
ትውልዱ አንድነቱን በማጠናከር የአድዋን ድል ሊደግመው ይገባል ትውልዱ አንድነቱን በማጠናከር አገሩን በማሳደግና በመጠበቅ የአድዋን ድል ሊደግመው እንደሚገባ ተመለከተ122ኛው የአድዋ ድል በአል አስመልክቶ የፓናል ውይይት ተካሂዷልየበአሉ ተሳታፊ የሃይማኖት አባት መምህር ሊቀ አድባር ተገኝ በሰጡት አተያየት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ አገራችን በውጭ ሃይል እንዳትወረር ውድ ህይወታቸውን ሰውተው ለዛሬዋ ታላቅ ቀን አብቅተውናልሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነት በመንቀሳቀስ ያስገኙትን ድል የአሁኑ ትውልድ በሚገባ በመረዳት የትላንት ጀግኖች ያወረሱትን ነጻና የተከበረች አገር መጠበቅ ይገባዋል ብለዋልሌላው የበአሉ ተሳታፊ የአዲስ አበባ አረጋውያን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ጌታቸው ክፍሌ አባቶቻችን እጅ ለእጅ ተያይዘው ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ኩራት የሆነ ድል አስመዝግበዋል አባቶቻችን ያስረከቡንን አገር በአንድነት በመጠበቅና የተጀመሩትን የልማት ስራዎች ከዳር በማድረስ የኢትዮጵያን ህዳሴ ማብሰር ይጠበቅብናል ብለዋልበአድዋ የተገኘው ድል በልማት እንዲደገም የአገሪቷን ሰላም በመጠበቅ ሁሉም የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ እንደሚገኝ የተናገረው ደግሞ የኤፌድሪ መከላከያ ሰራዊት አባል ኮለኔል ካህሳይ በርሄ ነውበአድዋ ድል የተገኘውን የኢትዮጵያ ጀግንነት ታሪክ በልማት ለመድገምና የአገሪቱን ሰላም ለመጠበቅ ሰራዊቱ ዝግጁ መሆኑን ተናግሯልየአድዋ ድል እጅግ የሚያኮራ መሆኑን የጠቀሰው ወጣት ይበልጣል አሰፋ ለዚህ ላበቁን አያት ቅድመ አያቶቻችን ምስጋናና ክብር እንደሚገባቸው ተናግሯልሰንደቅ አላማችን የበለጠ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ወጣቱ ከፍተኛ ሃላፊነት ያለበት በመሆኑ ጠንክሮ መስራት ይኖርበታል ነው ያለው ወጣት ይበልጣልየአድዋን ድል አስመልክቶ ጥናት ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ባህሎች አካዳሚክ ዳይሬክተር ዶክተር ሙሉጌታ ጌታቸው አድዋ የብሄር ብሄረሰቦች በጋራ የስገኙት ኢትዮጵያውያንን የሚያኮራ ድል መሆኑን ነው የተናገሩትዛሬም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ልክ እንደ አድዋው ድል በአንድነቱ በመጽናትና በመተባበር አገሩን መጠበቅ ይገባዋል ብለዋልየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አፈጉባኤ ዶክተር ታቦር ገብረመድህን በበኩላቸው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በባዶ እግሩ በርካታ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ በኋላቀር መሳሪያ ድል ያደረገበት መሆኑን ተናግረዋልየበለጸገችና ሰላሟ የተጠበቀች አገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ዜጎች የውጭም ሆነ የውስጥ ጠላቶች ሰለባ እንዳይሆኑ እጅ ለእጅ ተያይዘው መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋልየአድዋ ድል በዓል ነገ በአዲስ አበባ ሚኒሊክ አደባባይ ይከበራል
የአድዋ ድል በዓልን በየአመቱ ከማክበር ባለፈ ለገቢ ማሰገኛነት ማዋል ይጠበቅብናል- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የአድዋ ድል በዓልን በየአመቱ ከማክበር ባለፈ ድሉን የሚዘክሩ ነገሮችን በማልማት ለገቢ ማሰገኛነት ማዋል ይጠበቅብናል ሲሉ ዋልታ ቴሌቪዥን ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገልጸዋልእንደ ምሁራኑ ገለጻ የሰለጠኑ ሃገራት እንደሚያደርጉት የአድዋ ጦርነትን አስከፊ ገጽታና የተገኘውን ጣፋጭ ድል የሚያሳዩና የሚያስታውሱ ነገሮችን በማልማት ከፍተኛ ገቢ ማግኘት ይቻላልበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመካነ ቅርስ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ሙሉጌታ ፍስሃ እንደገለጹት የጦርነቱን ገጽታ የሚያሳዩ ትወናዎችን በየአመቱ ማሰራት እንዲሁም ሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦችን የሚወክሉ ትንንሽ ቤቶችን በአድዋ አካባቢ በመገንባት ለማረፊያነት ማዋል ከገቢ ምንጮች መካከል ሊጠቀሱ ይችላሉበሌላም በኩል የድሉን አጠቃላይ ገጽታ የሚያሳይ ሙዚየም መገንባትና በድሉ የተሰዉትን ሰማዕታት የሚዘክር ሃውልት ማቆም መቻልም እንዲሁ ከፍተኛ የቱሪስት መስህቦች ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል ዶክተር ሙሉጌታበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ተክለሃይማኖት ገብረ ስላሴ በበኩላቸው በኢትዮጵያና ጣሊያን መካከል የተደረገው ጦርነት በኢትዮጵያ አሸናፊነት እንዲደመደም ካስቻሉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው የአላማ ጉዳይ ነው ብለዋልበወቅቱ የጣሊያኖች አላማ የራሳቸው ያሆነውን መሬትና ሃብት በመውረር የራሳቸው ማድረግ ሲሆን የኢትዮጵያዊያን አላማ ደግሞ የሀገራቸውን ድንበር ከጠላት ወረራ መከላከል በመሆኑ ከፍተኛ የአላማ ጽናት እንዲኖራቸው አስችሏቸው ነበር ብለዋልሌላኛው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር ዶክተር አህመድ ሃሰን በበኩላቸው የአድዋ ድል ጥቁር ህዝቦች ተሸናፊ ብቻ ሳይሆኑ አሸናፊ እንደሆኑም ያሳዩበት ነው ብለዋልጥቁር ህዝቦች ሁሉ የእኛም ድል ነው ብለው የተቀበሉትን ይህን የአድዋ ድል አሁን ያለው ትውልድ ሊገነዘበውና ሊዘክረው ይገባልም ብለዋል ዶክተር አህመድበመሆኑም በአድዋ ድል ትውልድ የፈጸመው ታሪካዊ ገድል በተለይም በወጣቱ እንዲዘከርና ከድሉ ተገቢውን ገቢ ማግኘት እንዲቻል የታሪክ ምሁራንን እና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላትን ያላሰለሰ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል ምሁራኑ
አድዋ ታላቁ የጥቁር ሕዝቦች1የመቶ ሃያ አንደኛው የ፻፳፩ኛው ዓመት የድል በሃል ኢትዮጵያን ለድልያበቃው አንድነትና አመራር ለምለም ተሊላ Managing Editor of Ee-JRIF and NES-GLOBAL... እኛ ግን እንኳን ልእልፍና ለሁለት እልፍ ሰው የኢጣሊያ ሀገር ስው ሁሉ ቢመጣ የኢጣሊያን ጥገኝነት ይቀበላሉ ብለህ እትጠርጥር. አጤ ምኒልክ ነሐሴ23 ቀን 1887 ዓ.ም. አውሮጳ ለነበረው ለሙሴ እልግ ከጻፉት የግል ደብዳቤ ላይ2...እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም ግን እንዲህ መሳዩን ውል ከመቀበል ጦርነት እመርጣለሁ...እቴጌ ጣይቱን ጠቅሶ ሳሊምቢኒ በ1890 ዓ.ም.እንደጻፈው3መግቢያበአስራ ስምንተኛው ምህተ ዓመት በዘመናዊ የጦር ሃይል የታጠቀና በሰለጠነ የጦር ሰራዊት የተደራጀ የቅኝግዛትና የመስፋፋት ህልም ያለውን የወራሪው ጣሊያንን ኃይል አንዲት አፍሪካዊት ሀገር አድዋ ላይ አሸንፋ ድልለመቀዳጀት ያስቻላት የንጉሰ ነገስቱና የሕዝቡ በአንድነት መቆም ትልቅ ድርሻ ነበረው በተለይም ሕዝቡ ከሰሜን እስከደቡብ ከምህራብ እስከ ምስራቅ ከጫፍ እስከጫፍ በጋራ ጠላትን ለመመከት በአንድነት መነሳት በመቻሉ ነው ይህጽሑፍም የአድዋው ጦርነት መንስሔውና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወራሪው ጣሊያንን ለመመከት በጋራ በአንድነትየተሰባሰበበትንና የዘመተበትን መንገድ በማጤን የአድዋው ጦርነትና ታላቁን ድል በመቃኘት አድዋ ላይ ዋናው የጦሩ መሪየነበሩት ንጉሰ ነገስቱና አማካሪዎቻቸው በጦርነቱ ወቅትም ሆነ ከዚያ በፊት በሀገር ጉዳይ ላይ ያሳለፏዋቸውን ውሳኔዎችናየወሰዱዋቸውን እርምጃዎች ከንጉሰ ነገስቱ የግል ስብዕናቸው ጋር በማነጻጸር ከድሉ በኋላ ኃያላኑ የአውሮጳ ሀገራትንጨምሮ የኢትዮጵያ ወዳጆችም ሆኑ ጠላቶች ድሉን አስመልክቶ በኢትዮጵያና በንጉሰ ነገስቱ አጤ ምኒልክ ላይ በወቅቱየወሰዱዋቸውን ውሳኔዎች ይዳስሳልለአድዋው ጦርነት ዋናው የጦርነቱ ሰበብ የነበረው የውጫሌ ውል ተብሎ የሚጠራው ውል ነው4 ይህም በሺህስምንት መቶ ሰማንያ አንድ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. ከንጉሰ ነገስቱ አጤ ዮሐንስ ሞት በኋላ አጤ ምኒልክ ሀገራቸውንለማረጋጋት እየተዘዋወሩ በነበሩት ሰዓት ወሎ ድረስ በመሄድ ውጫሌ ላይ በጉዞዋቸው ላይ እንዳሉ ኮንቲ አንቶኔሊየተባለውየጣሊያን መልህክተኛ ተሯሩጦ ያስፈረማቸው ውል ሲሆን የዉሉም አስራ ሰባተኛው ፲፯ኛው አንቀጽ በአማርኛናበጣሊያንኛው ትርጉም መፋለስ ምክንያት ነው አስራ ሰባተኛው አንቀጽ በአማርኛው የሚለው የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስትከአውሮጳውያን ነገስታት ለሚፈልጉት ጉዳይ ሁሉ በጣሊያን መንግስት አጋዥነት መላላክ ይቻላቸዋል ሲል በጣሊያንኛው ግንየኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት በጣሊያን መንግስት አማካይነት ማድረግ ይገባዋል5የሚል በመሆኑ የጣሊያንኛው ትርጉም የኢትዮጵያን በጣሊያን ስር ጥገኛ መሆን የሚያመለክት ሲሆን የአማርኛው ግንኢትዮጵያ የጣሊያን እገዛ ሲያስፈልጋት ብቻ እንድምታገኝ የሚያረጋግጥ የመረዳዳትና የመልካም ግኑኝነት ብቻ ነውበእርግጥም በወቅቱ የኢትዮጵያው ንጉሰ ነገስትና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ ብጡል ውሉን ሲፈራረሙ የጣሊያንን ድብቅ1 2 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 1393 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 1484 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራል ማተሚያቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 1965 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራል ማተሚያቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 211 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክየመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 140 135ሴራ አልተረዱትም ነበር በጣሊያን በኩል ግን ውሉን ከተፈራረሙበት ዕለት እ.ኤ.አ. ከኦክቶበር አስራ አንድ ፲፩ ቀንሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ጀምሮ ኢትዮጵያ በጣሊያን ስር ነች6 በማለት ለአስራ ሁለትየአውሮጳ ሀገራትና ለአሜሪካም ጭምር የእወቁልኝ ዓይነት ደብዳቤ ጽፎ ነበር የኢትዮጵያ መንግስት ግን የጣሊያንን ድብቅየመስፋፋትና የቅኝ ግዛት ህልም ማወቅ የቻለው ኢትዮጵያ የአጤ ምኒልክን የንግስናቸውን ዜና ለማሳወቅ ለአውሮጳ ሀገራትደብዳቤ በምትላላክበት ጊዜ የጣሊያን መሪ ንጉስ ኡምቤርቶ ኢትዮጵያ ከሌሎች አውሮጳውያን ሀገራት ጋር በቀጥታ መላላክየለባትም ደብዳቤው በጣሊያን በኩል ማለፍ ነበረበት በሚል አምባጓሮ ሲያስነሳ ነው በተለይም በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያሁለት ፲፰፻፹፪7 ዓ.ም ኃያላን የአውሮጳ ሃገራት የባርያ ንግድን ለማስቀረት በነበራቸው ጉባኤ ላይ ጣሊያንኢትዮጵያን ወክዬ የምቀርበው እኔ ነኝ ማለቷ ሳያንስ እንግሊዝ ጀርመን ቤልጅየም ኦስትሪያና ሌሎቹም የአውሮጳሃገራት የጣሊያን መንግስት ለኢትዮጵያ ተወካይ ቢሆን አንቃወምም በሚል የጣሊያንን ፍላጎት በድምጽ ብልጫማጽደቃቸው ኢትዮጵያ እራስዋን የቻለች የማንንም ፈቃድ የማትጠብቅ ሉሃላዊት ሀገር መሆንዋን መናቅ ለአጤ ምኒልክእጅግ አስደንጋጭ ነበርበመሆኑም ንጉሱና ንግስቲቱ ይህንን የጣሊያንን ድብቅ ፍላጎት ካወቁበት ጊዜ ጀምሮ የውሉ አስራ ሰባተኛውአንቀጽ እንዲስተካከል በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ጣሊያን ግን በሰው በገንዘብ በአውሮጳውያንና በመልህክተኞችምበማታለልና በንቀት አንቀጹን ላለማስተካከል ያላደረገው ሙከራ የለም አጤ ምኒልክና ባለቤታቸው ግን የሀገራቸውንሉሃላዊነት ላለማስደፈር የነበራቸውን ጠንካራ አቋም በተግባርም በክርክርም ለማስረዳት የሄዱባቸው መንገዶች ፍጹምቆራጥነት የተሞላበትና የወራሪውን ህብሪት ፊት ለፊት ተጋፍጠው በድፍረት በመንገር የገለጹባቸው ታሪካዊ እውነቶችለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው የጥቁር ሕዝብ ለዘላለም አኩሪ ሆነው ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፉ ታላቅእሴቶች በመሆናቸው ኢትዮጵያን ለድል ያበቃው የንጉስ ነገስቱና የንግስቲቱ ጽኑህ ታላቅ አመራር ሕዝባቸውን ከዳርእስከዳር ማንቀሳቀስ የቻለ ነበር አጤ ምኒልክ ይህ የውል ሰነድ እንዲስተካክል በደብዳቤም በሰውም በተደጋጋሚቢጠይቁም በተቃራኒው ጣሊያን ግን የኢትዮጵያን መንግስት የመደለል ሙከራው ስላልተሳካላት በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያአንድ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. ውጫሌ ላይ ዉሉን ያስፈረመውን የጣሊያን መንግስት መልህክተኛ የሆነው ተልኮ ለመጨረሻጊዜ ለመደራደር በሚዘጋጁበት ሰዓት እቴጌ ጣይቱም ከመልህክተኛው ጋር የሚደረገው ውይይት ላይ ገብተው ሲከራከሩለአንቶኔሊ የቅኝ ግዛት ሙከራ አልበገር በማለት የአስራ ሰባተኛው እንቀጽ ጨርሶ ተሰርዟል በማለታቸው መልህክተኛውከመናደዱ የተነሳ ምኒልክን ስልጣናቸውን ሁሉ ለሴት ለቀው ያላግጡብናል8 ብሎ መናገሩ ተዘግቧል ምክንያቱም አጤምኒልክ ደም እንዳይፈስ ብዙ ሙከራ እያደረጉ ሳለ አንቶኔሊ የሚፈልገው የኢትዮጵያን በጣሊያን ጥገኝነት ስር መውደቅበመሆኑ እቴጌይቱ ነጻነትን አሳልፎ ላለመስጠት ምንም ዓይነት የጣሊያን ሙከራ እንዳይሰካ ያደረጉ ሴት በመሆናቸውበምኒልክ ስርወ መንግስት የነበራቸው ድርሻ ትልቅ አስተዋጾ እንደነበረው ነው መልእክተኛው የመሰከረው በተጨማሪምበክርክሩ ወቅት ኮንት አንቶኔሊ የቅኝ ግዛትና የመስፋፋት ስሜቱን መደበቅ ስላልቻለ በአጸፋው ንጉሱና ንግስትቲቱምአፍሪካዊ ጽናታቸውን በድፍረት በመግለጽ ለወራሪው እንደማይበገሩለት በማረጋገጣቸው በተለይም እቴጌይቱመልህክተኛው የውሉን ወረቀት መቅደዱና የጦርነት ዛቻውን በሰሙ ጊዜ የዛሬ ሳምንት አድርገው የሚደነግጥልህ የለምበሚል ምላሻቸውን ከመስጠት አልፈው እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም ግን እንዲህ መሳዩን ውል ከመቀበል ጦርነትእመርጣለሁ ማለታቸውን ሳሊምቢኒ የተባለው ሌላው የጣሊያን መልህክተኛ እ.ኤ.አ. በአስራ ስምንት መቶ ዘጠና፲፰፻፺ ዓ.ም. የጻፈውን በመጥቀስ ጳዉሎስ ኞኞ ዘግቦታል እንኳን ድሮ ጥንት በአስራ ስምንተኛው ምህተ ዓመትዛሬ በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በዓለም ላይ በሀገር ጉዳይ የመሪነት ቦታው ላይ የሴቶች ድርሻ ከወንድ እኩል ባልሆነበትዘመን የጥንቷ ኢትዮጵያ ግን በአስራ ስምንተኛው ምህተ ዓመት ሴቶችን በአመራር ላይ ያስቀመጠች ብቻ ሳትሆነ በውሳኔላይም ሴቶች ድምጽ እንደነበራቸው አድዋ ላይ ያስመሰከረች ኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ አፍሪካዊት ሀገር ነች ጣሊያን ኮንትአንቶኔሊን በዋና መልእክተኛነት የውጫሌ ውልን ለይምሰል እንዲደራደር ቢልክም እራሱ ሳሊምቢኒን ግን ውሉ ባለበትእንዲጸና እንዲያደርግ መታዘዙን ጠቅሷል በተለይም በስተመጨረሻ ላይ ከመልህክተኛው ጋር ሲደራደሩ ሙከራው በሙሉበዕለቱ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ በንቀት ያደረገው ሙከራ ውሉ ለአምስት ዓመት ብቻ ስለሆነ ሶስት ብቻ ነው የቀረንናእንጠብቅ የሚሉ የማታለያ ቃላቶች ሲወረውር ምኒልክ ትዕግስታቸው በማለቁ የሰጡት ምላሽ:እንዲህ ነገሩ ሳይጎላ እንዲህ ባጓጉል እንኳን ሶስት ዓመት ሶስት ቀንም ቢሆን አያድርምና ይልቁንስ አሁን ቶሎ ይለቅ9 በማለት ነው ቁርጡን የነገሩትበመሆኑም ምኒልክ በቆራጥነት በዘመናዊ የጦር መሳሪያና በሰለጠነ ወታደር የተደራጀውን የወራሪውን የነጭ ጦርበዚያ ዘመን እንኳን ሶስት ዓመት የሶስት ቀናትም ጊዜ እንደማይሰጡት አስረግጠው በመንገር ያላቸውን ጠንካራ አቋምና6 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 1437 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 144-1488 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራል ማተሚያቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 213-2159 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 146-150136የሀገራቸውን ሉዓላዊነት እንደማይደራደሩ ነው ያረጋገጡት አንቶኔሊ የመጨረሻው ሙከራው ለማሳመንም ሆነ ለማታለልስላልተሳካለት ተናዶ ሲወጣ የሚሄድበት በቅሎ እንዲሰጠው ያዘዙ ስልጡን መሪ ናቸው እንደጳዉሎስ ኞኞ አገላለጽየውጫሌ የውል ሰነድ የተቀደደው በመድፍ ነው ከዚህ ታሪካዊ የንጉሰ ነገስቱና የእቴጌዪቱ ምላሽ የምንገነዘበው ቁምነገር ቢኖር ልክ እንደወንዶቹ የኢትዮጵያ ሴቶች በነበራቸው አስተዋይና ብልህ አመራር በሀገር በወገንና በማንነታቸው ላይለተነሳ ለውጪም ሆነ ለውስጥ ሃይል እንደማይበገሩ በተለያዩ መንገዶች ይገልጹ እንደነበር ያረጋግጣልለአድዋው ጦርነት መነሻው የውጫሌ ውልም ሆነ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ከአጤ ምኒልክ በሳልና አስተዋይአመራር በተጨማሪ እቴጌይቱም ያሳዩት ቆራጥነት የሚያመለክተው በጊዜው ኢትዮጵያውያን ሴቶች የነበራቸውን ቦታ በግልጽከማሳየቱ በተጨማሪም የጥንት ኢትዮጵያውያን ወንድ ገዢዎችም ሴቶቹን በሴትነታቸው ሳይንቁዋቸው በምክርም ሆነ ውሳኔበመስጠት ድርሻቸው ያከብሩዋቸው እንደነበርና ባጠቃላይ የኢትዮጵያውያንን ስነ ልቦና የተለየ ከፍተኛ ግምት የሚያሰጠውታላቅ እሴት ነው ከእቴጌ ጣይቱ በፊትም ጥንት የነበሩትን የኢትዮጵያ ነገስታት ስንፈትሽ የጥንትዋ ኢትዮጵያ በኩሽ ነገድስም የኩሽ ምድር በኩሽ ልጆችም በሳባ ስም የሳባ ምድር በአቢስ ስም አቢስንያ ስትባል ቆይታ በመጨረሻ አባታቸውኩሽ ከሞተ ከሁለት ሺህ አራት መቶ ሃምሳ ዓመታት በኋላ ማለትም ከክርስቶስ ልደት በፊት በሁለት መቶ ሃምሳ አራትዓመተ ዓለም ፪፻፶፬ ዓ.ዓ በአባታቸው በኩሽ በሁለተኛው ስሙ በኢትዮጵ ስም ኢትዮጵያ10 ብለው ከመሰየማቸውበፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ ከነገሱት ነገስታት ውስጥ ሴቶችም ይገኙበት ነበር ከነኚህም መሀል ከክርስቶስ ልደት በኋላበሰላሳ አራት ፴፬ ዓ.ም. የነገሰችው ሰባ ሶስተኛዋ ገዢ ፸፫ኛዋ11 ንግስት ገርሳሞት ህንደኬ ሰባተኛ ፯ኛየተባለችው ወሰንዋን ተሻግራ ባሁኑ ፓለስታይን በጋዛ የራሷ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሾማ እንደነበር በቅዱስ መጽሐፍም12ተጠቅሷል ከእርሷም በኋላ የተለያዩ ሴት ነገስታት ነግሰዋል በአጤ ቴዎድሮስ ስርወ መንግስት ደግሞ አጤ ቴዎድሮስሸዋን ለማስገበር በሺህ ስምንት መቶ አርባ ስድስት ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. ለጦርነት ወደ ሸዋ በዘመቱበት ጊዜ የሸዋው ንጉስኃይለ መለኮት ሞተው ስለነበር ልጃቸው ምኒልክን13 በአስር ዓመቱ አስረው ወስደውት ነበር ነገር ግን ህጻኑ ምኒልክሲያድግ ከታሰረበት አምልጦ ወደ ወረይመኑዋ ገዢ ወደ ወይዘሮ ወርቂት ግዛት ስለገባ አጤ ቴዎድሮስ ከወይዘሮ ወርቂትጋር ከባድ ውጊያ አድርገዋል ልክ እንደ ህጻን ምኒልክ የወይዘሮ ወርቂት ልጅም የአጤ ቴዎድሮስ እስረኛ ስለነበር ንጉሱበምኒልክ ንዴት የወርቂትን ልጅ ቢገሉባቸውም ወይዘሮዋ ግን የንጉሱ ሃይለኛነት ሳይበግራቸው ምኒልክን አሳልፈው ያልሰጡሲሆን እንዲያውም ወደ ዘመዶቹ ወደ ሸዋ የላኩ አስራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ያፈራቸው የወረይመኑ ገዢ የነበሩትወይዘሮ ወርቂት ሌላዋ ደፋር ጠንካራና ቆራጥ ሴት የኢትዮጵያ ሴቶች ከአድዋው ጦርነት በፊትም ጉልህ ድርሻእንደነበራቸው ያረጋግጣል በአጤ ምኒልክ ስርወ መንግስትም ልክ እንደጥንቶቹ ኢትዮጵያውያን ሴቶች እቴጌይቱም ያሳዩትቆራጥነት የሚያመለክተው ልክ እንደንጉሰ ነገስቱ በዚያ ዘመን ኢትዮጵያውያን ሴቶችም በዘመናዊ የጦር መሳሪያና በሰለጠነወታደር የተደራጀውን የወራሪውን የነጭ ጦር በሀገራቸው ሉዓላዊነት እንደማይደራደሩ ነው ያረጋገጡትአንዲት እፍሪካዊት ሀገር በዘመናዊ የጦር መሳሪያ በታጠቀና በሰለጠነ የጦር ሃይል የተደራጀን ተስፋፊና ቅኝ ገዢየወራሪውን የጣሊያንን ሃይል በባህላዊ የእጅ ጥበበበኞች ስራ በምታፈራው የጦር መሳሪያ በጦርና በጎራዴ በጩቤናበአንካሴ በጦርና በጋሻ በመመከት ከመቶ ሃያ ዓመታት በፊት እንደ የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በሺህ ስምንት መቶሰማንያ ስምንት ፲፰፻፹፰ ዓመት ምህረት የወራሪው የቅኝ ገዢውን ዕቅድ በማክሸፍ ጣሊያንን ያስበረገገች ዓለምንያስደመመች ምህራባውያንን ያስደነገጠች አውሮጳውያን ጀርመን በርሊን14 ላይ አፍሪካን ለመቀራመት ያቀዱትን ዕቅድደግመው እንዲያጤኑት ያደረገች15 ብቸኛዋ በዓለም ታሪክ ጸሐፊዎችና በሊቀ ሊቃውንቶች አድዋ ላይ ድል ማድረጓየተመሰከረላት ድል የተቀናጀችበትን የድል በሃሏን ከአጋሮችዋና ከነጻነት ናፋቂው የዓለም ሕዝብ ጋር በጋራ የምታከበረውየአድዋው ድል ባለቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካውያን የነጻነት አርማ ስትሆን ኢትዮጵያዊነት ደግሞ ፕሮፌሰር ሐሰን ሁሴንሚኒሶታ ላይ ከጠቀሱት ብንዋስ16 ኢትዮጵያዊነት የዘር ሐረግ ቆጠራ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነት ታሪክ ሕግ ፍልስፍናና10 አባ ጎርጎሪዮስ 1974 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እትም አዲስ አበባ ገጽ 1211 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራልማተሚያ ቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 1112 የሐዋርያት ስራ 8:20-4013 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 8914 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 33715Pearce, J. 2014. Prevail: The Inspiring Story of Ethiopias Victory overMussolinis Invasion, 19351941: New York, NY: Skyhorse Publishing. p. 27-2816 137ማህበራዊ ስነ ልቦና መሆኑ የተረጋገጠበት የአድዋ ድል የሁሉም የነጻነት ናፋቂ ሕዝቦች ድል ነው ኢትዮጵያ የአድዋንድል ለመቀዳጀት ባህላዊ የጦር መሳሪያ ጋሻ ጦርና ጎራዴን ይዘው በባዶ እግራቸው በሶና ጥራጥሬ እየተመገቡበመድፍ ጭስ ታፍነው በሰማይና በምድር በመትረየስ በጦርና በታንክ የታጀበን በሰለጠነ የጦር ሃይል የተደራጀውንተስፋፊና ቅኝ ገዢውን የጣሊያንን ወራሪ ሃይል አንዲት አፍሪካዊት ሀገር እንዴት ልትቋቋመው ቻለች ስንል መልሱንለማግኘት የጥንቷ ኢትዮጵያ ሕዝቧ ኃይሏና ግዛቷ እንደ ሀገር ከአድዋ ድል በፊት ምን ትመስል ነበር የግዛት ስፋትዋናየሕዝብዋስ ጥንካሬ እንዴት ነበር ብሎ መቃኘት ያስፈልጋልጥንታዊቷ ኢትዮጵያ ሕዝቧ ኃይሏና ግዛቷ የጥንትዋ ኢትዮጵያ ታሪኳ የሚያሳየው ሕዝቧ ለጠላት እንደማይበገርና በየጊዜው የነገሱት ነገስታትም የሕዝቡንአንድነት ጠብቀው በየዘመናቱ የመጡባቸውን ፈተናዎች በአሸናፊነት እንደተወጡ ያሳያል እንደቀደሙት አባቶቻቸውእንደጥንት የኢትዮጵያ ጀግኖች የሕዝቡ አንገዛም ባይነትና የሀገሩን ሉሃላዊነት ላለማስደፈር ካለው ቆራጥነት በተጨማሪምአጤ ምኒልክ ሕዝባቸውን በአንድነት በወራሪው ጠላት ላይ እንዲነሳ ያስተባበሩበት ፈሪሃ እግዚሃብሔር የተሞላበት የክተትአዋጅና ታላቅ አመራር የእቴጌዪቱም ብልሃትና አስተዋይነት የሞላባቸው ውሳኔዎች ለአድዋው ድል ትልቅ ሚናተጫውተዋል በሳይንስ ምርምር ኢትዮጵያ የሰው ልጅ መገኛ መሆንዋ በድንቅነሽ በሉሲ17 ኢትዮጵያ ውስጥ ከአፋር ከደንከልየተገኘው የከርሰ ምድር ቅሪት ከሶስት ሚሊዮን ዓመታት በላይ ዕድሜ ያለው የሴት አጽም የሚያመለክተው የሰው ዘርበእንግሊዝኛው አጠራር ሆሞ ሳፒያንስ የተባለው ከኩሽ ምድር ከኢትዮጵያ ከአፋር ተነስቶ የሰው ልጅ ምድር ላይእንደተበተነ በመረጃ የተረጋገጠ ሲሆን በቅዱስ መጽሐፍም የኖኅ የልጆቹ ነገዶች እንደ ትውልዳቸው በየሕዝባቸው ...እነዚህ ናቸው አሕዛብም ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከእነዚህ ተከፋፈሉ18ይልና ከጥፋት ውኃ በኋላ የኖኅ የልጅልጅ በሆነው በኩሽ ልጆች ኢትዮጵያ ትገዛ እንደነበር19 በመሆኑም የኖኅ የልጅ ልጆች የኩሽ ነገዶች ኢትዮጵያንእንዳቀንዋትና ከክርስቶስ ልደት ከአንድ ሺህ አስራ ሶስት ዓመታት በፊት ማለትም ከ፲፻፲፫ ዓመተ ዓለም ጀምሮ እስከክርስቶስ ልደት ድረስ ብቻ ስልሳ ስምንት ፷፰20 ነገስታት ኢትዮጵያ ላይ እንደተፈራረቁባት ከክርስቶስ ልደት በኋላደግሞ እስከ ሺህ አራት መቶ ዘጠና ሁለት ዓመት ምህረት ፲፬፻፺፪ ዓ.ም. ድረስ መቶ ሰማንያ ስድስት ፻፹፮ነገስታት ኢትዮጵያን መግዛታቸውንና21 የጥንትዋ ኢትዮጵያ በጥንት ዘመን መንግስት መስርታ በራሷ ስትደዳደር የነበረችግዛትዋም እጅግ በጣም ሰፊ እንደነበር በመልክሃ ምድር አቀማመጡም ከግብጽ ጋር የተያያዘና ሕዝቦቿም በንግድ ስራቸውየታወቁና የበለጸጉ በሃይላቸውም የተፈሩና የተከበሩ22 ነበሩ የግሪክ ባለቅኔው ሆሜርም የኢትዮጵያ ሕዝቦች በጉልበትሃይለኞች እንደነበሩ ሲገልጽ የምህራባውያን የታሪክ አባት የሆነው ሔሮዶተስም ኢትዮጵያውያን በሃይል ከሰዎች ሁሉየሚበልጡ ብሎ ከመጥቀሱ ባሻገር በቅዱስ መጽሐፍ ደግሞ የኩሽ ልጅ ... በምድር ላይ ሃያል መሆንን ጀመረ እርሱም በእግዚአብሔርፊት ኃያል አዳኝ ነበር 23 ይላል በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በተተነተነበትመጽሐፍ ላይ ኩሽ ሁለት ስም ነበረው ሁለተኛው ስሙ ኢትዮጲስ ይባላል አቅኝዎቹም በአባታቸው ስም ይችን ሀገር ኢትዮጵያ ብለዋታልበዕብራይስጥ ሙሴ ኩሽ እያለ የጠራውን በብሉይ ኪዳን ኢትዮጵያ... እንደሚል24 ተጠቅሷል በቅዱስ መጽሐፍም በሳይንስም ሊቀሊቃውንቶችና ታሪከ ጸሐፊዎች የመስከሩላት የሕዝቧን አንድነት ተጎናጽፋና ተከብራ ለሃያሌ ዘመናት በራሱዋ ነገስታትስትገዛ የኖረች ኢትዮጵያ ታላቅ ጥንታዊት አፍሪካዊት ሀገር ነችበሌላ በኩል ደግሞ ጥንት እነይሁዳ በምድረ ግብጽ በባርነት ላይ በነበሩበት ወቅት የኢትዮጵያ ነገስታት የተደላደለመንግስት መስርተው በነጻነት ይኖሩ እንደነበር በተለያየ መንገድ በሚገባ ተዘግቧል የኢትዮጵያ ወሰንም በምስራቅ እስከማዳጋስካር በሰሜን እስከ ኑብያ ዳር በደቡብ ደግሞ እስከ ኒያንዛ ባህር እንደነበርና ዛሬ የመን የሚባለው ሀገርም17 18 ዘፍጥረት 10:3219 ዘፍጥረት 2:1320 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 8-1421 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 4022 ትንቢተ ሕዝቅኤል 29:10 ኢሳይያስ 43:3 ዜና መዋዕል 2 ካልዕ 16:8 አባ ጎርጎርዮስ1974 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እትም አዲስ አበባ ገጽ 12-1423 ዘፍጥረት 10:8-9 አባ ጎርጎርዮስ1974 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እትም አዲስአበባ ገጽ1224 አባ ጎርጎርዮስ1974 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እትም አዲስ አበባ ገጽ 11-12138የኢትዮጵያ ግዛት እንደነበር25 ከመጠቀሱ በተጨማሪም ከክርስቶስ ልደት በኋላ በሰላሳ አራት ፴፬ ዓ.ም. ኢትዮጵያን የገዛችው ንግስት ገርሳሞት ህንደኬሰባተኛ ፯ኛ26 ወሰንዋን ተሻግራ ባሁኑ ፓለስታይን በጋዛ የራሷ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሾማ እንደነበርተጠቅሷል ሌላው ደግሞ በአረብ ሀገር የሚኖሩ ክርስቲያኖች በአይሁዶች ልዩ ልዩ መከራ በደረሰባቸው ጊዜዩስቲያኖስ የተባለው የቁስጥንጥንያ ንጉስ ለኢትዮጵያው ገዥ ለንጉስ ካሌብ እርዳታ በመጠየቅ ንጉስ ካሌብከአይሁዶች ጋር ተዋግቶ ድል እንዳደረገና ቤተክርስቲያንም መስርቶ ለመቶ ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ስርእንደነበር የቤተ ክርስቲያኑ ፍርስራሾች እንደሚያረጋግጡ27 ተዘርዝሯል በዛጉዌ ዘመነ መንግስትም ግብጽ ከአረብ ሀገራት ጋር ጦርነት ላይ በነበረችበት ጊዜም ኢትዮጵያ የግብጽስደተኞችን ተቀብላ28 በጊዜው የዛጉዌ ዋና ከተማ በነበረው በላስታ መጠለያ አግዥተዋልከላይ እንደተዘረዘረው የኢትዮጵያውያን ጥንካሬና ሃይለኛነት በታሪክ የተረጋገጠ ሲሆን ወራሪው ጣሊያን ግን ይህንንሁሉ የታሪክ እውነታ በመጣስ የቅኝ ግዛትና የመስፋፋት ህልሙን ለማሳካት ለዘመናት መንግስት መስርታ ስትተዳደርየነበረችውን አፍሪካዊት ሀገር ኢትዮጵያን መውረሩ ያልሰለጠነ ሀገር ላሰልጥን ብሎ መዘባበቱ ለጣሊያንንና ለተባባሪዎቹበማያደግም ሁኔታ ለዘመናት ትልቅ ትምህርት የሰጠ ዓለም የማይረሳው ታሪክ ነው የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሃይላቸውየተፈሩና የተከበሩ እንደነበሩ በንግድ ስራቸውም የታወቁና የበለጸጉ ለሌላው እርዳታ እስከመስጠት የደረሱ ቢሆኑምእርዳታ እስከመስጠት የደረሰች ኢትዮጵያ ካጋጠምዋት ፈተናዎች ውስጥ ከክርስቶስ ልደት በኋላ ከስምንት መቶ አርባ ሁለት፰፻፵፪ ዓመተ ምህረት ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ያህል ዮዲት ጉዲት የተባለችው የፈላሻዎች ንጉስ የነበረውየጌዴዎን ልጅ ነግሳ ቤተክርስቲያኖችን በማቃጠልና ካህናትን በመግደል ያደረሰችው ጥፋትና ግራኝ አህመድ በቱርኮችተረድቶ ኢትዮጵያ ላይ የከፈተው ከባድ ጦርነት በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያው ንጉስ አጤ ልብነ ድንግል በፖርቱጋሎችእርዳታ ግራኝን ድል ቢያደረገውም ዮዲትና ግራኝ አህመድ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ፈተናዎች እንደነበሩ በሚገባተመዝግበዋል29የጥንቷ ኢትዮጵያ ኃይል ከነበረበት ጥንካሬው በየዘመናቱ እየተለዋወጠ የመጣበትን ምክንያት የታሪክ ዘጋቢዎችእንደሚዘግቡልን በመተማመን ብዙ የተነገረለት የመሳፍንት ዘመን አገዛዝ ግን የኢትዮጵያ ታሪክ ላይ መጥፎ አሻራ ትቶአልፏል ከአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ድረስ እንደ አውሮጳውያንነገስታት በግዛት በጥቅም በዙፋን ይገባኛልና በሃይማኖት እርስ በእርሱ ብዙ ውጊያ ያደረገ የለም30 ልከእንደአውሮጳውያን ነገስታትና እንደሌሎቹ በዓለም ላይ ያሉ ሀገሮች ሁሉ የኢትዮጵያ ገዢዎችም አንዱ እንዱን ለማስገበርበመሳፍንት ዘመን እርስ በአርሳቸው ብዙ ውጊያ አድርገዋል በመሳፍንት ዘመን ሁሉም ገዢ በየአካባቢው እየነገሰ ስልጣኑንለማደርጀትና ባላንጣውን ለመቋቋም አራሹ ገበሬን እርስ በእርሱ እያዋጋ ሌሎቹን በማስገበር አካባቢውን ይገዛ ነበር ከአስራስድስተኛው ዘመን የመሳፍንት አገዛዝ በኋላ የእርስ በአርስ ጦርነት በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ መጥፎ አሻራ ትቶስለነበር ኢትዮጵያ ለዘመናት ወደነበረችበት አንድነት እንድትመለስና የዘመናት ታሪኳን እንደገና በማደስ የተረጋጋች ሀገርለማድረግ በአጤ ቴዎድሮስ ስርወ መንግስት ንጉሰ ነገስቱ ባላንጣዎቻቸውን በሃይል ለማሳመን ብዙ ጦርነት ተካሂዷልኢትዮጵያን ለሰባ ዓመታት ያናቆራትን የመሳፍንት አገዛዝ በጦር ኃይል ደምስሰው ማህከላዊ መንግስት መስርተው ኢትዮጵያወደ ነበረችበት አንድነት31 ለመመለስና የመሳፍንት ዘመን የጣለውን መጥፎ አሻራ ለማደስ አጤ ቴዎድሮስ ታላቅ ተጋድሎያደረጉ መሪ ናቸውበመሳፍንት ዘመን ስልጣን የመጨበጫው ዋናው ዘዴ ውጭ ሀገር የሚሰራው የጦር መሳሪያ ጥይት ጠብመንጃናመድፍ ነበር ይህንንም ለማግኘት ከንጉስ ሳህለ ስላሴ ዘመን ጀምሮ ከየመንግስታቸው እየተላኩ ለንግድ ሀገር ለማየትአንዳንዶቹም በወንጌል መላክተኝነት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት መሀል በሺህ ስምንት መቶ ሰላሳ ሁለት ፲፰፻፴፪ ዓ.ም.25 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 3-1026 የሐዋርያ ስራ 8:20-40 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 11-1227 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 2028 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 3029 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 2830 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 33731 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. ገጽ 9139ከእንግሊዝ ቤተክርስቲያን በሺህ ስምንት መቶ ሰላሳ አራት ፲፰፴፬ ዓ.ም. ደግሞ ከእንግሊዝ የንግድ ወዳጅነት ውልለመፈጸምና ሌሎቹም ከተለያዩ መንግስታት ከሕንድ ከአየርላንድ ከፈረንሳይም32 በሚላኩት አማካኝነት እያንዳንዱ ገዢከእነዚህ የውጭ ሰዎች ጋር በመስማማት ባላንጣውን ለማስገበር ዘመናዊ መሳሪያዎችን ያገኝ ነበር ለምሳሌም ያህል የሸዋውገዢ ንጉስ ምኒልክ ከጣሊያን መንግስት ጋር በመቀራረብ ዘመናዊ መሳሪያ ሲያገኙ የትግሬው ገዢ ንጉስ ዮሐንስ ደግሞከእንግሊዞች ጋር በመዋዋል ነበር የሚያገኙት አጤ ቴዎድሮስ ሸዋን ለማስገበር በአስራ ስምንት መቶ አርባ ስድስት፲፰፻፵፮ ዓ.ም. ወደ ሸዋ በዘመቱበት ጊዜ የሸዋው ንጉስ ኃይለ መለኮት ሞተው ስለነበር ህጻን ልጃቸው ምኒልክንበአስር ዓመቱ አስረው33 ወስደው አሳድገው ህጻን ምኒልክ ግን ሲያድግ ጥሏቸው ወደ ወረይመኑ ገዢዋ ወደ ወይዘሮወርቂት ግዛት በገባበት ጊዜ አጤ ቴዎድሮስ ከወይዘሮዋ ጋር ከባድ ውጊያ አድርገዋል ንጉሰ ነገስቱ ከባላንጣዎቻቸው ጋርከሚያደርጉት የእርስ በርስ ጦርነት በተጨማሪ በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ ፲፰፻፷ ዓ.ም. በጊዜው የነበሩትን መቶ ሁለት፻፪ የውጭ ሀገር ሰዎችን መቅደላ ላይ ሲያስሩ34 ከታሰሩት አንዱ የእንግሊዝ ቆንስል ነበር በመሆኑም የእንግሊዝ ጦርየአጤ ቴዎድሮስን ተቀናቃኞች በመርዳትና መኳንንቱን በመደለል ንጉሰ ነገስቱ አጤ ቴዎድሮስን በቁጥጥሩ ስር ሊያደርጋቸውስላልቻለ ለእንግሊዝ ጦር እንዲጨመርለት በጠየቀው መሰረት የሕንድ ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ሁለቱ የአጤቴዎድሮስ ባላንጣዎች የትግሬው ደጃዝማች ካሳ በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው አጤ ዮሐንስ የተባሉትና የዋጉደጃዝማች ጎበዜ በኋላ ተክለ ጊዮርጊስ ተብለው በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ አንድ ፲፰፻፷፩ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሰነገስት ሆነው ለሶስት ዓመታት ከነገሱ በኋላ በዳጃች ካሳ የተሸነፉት ለእንግሊዝ ጦር እርዳታ ሰጥተው እስከ መቅደላ ድረስበመምጣት ንጉሰ ነገስቱን ሲወጉዋቸው አጤ ቴዎድሮስ ግን ለእንግሊዝ ጦር እጄን ከምሰጥ ብለው በራሳቸው እጅህይወታቸውን አጥፍተው ለሀገራቸው መስዋዕትነት የከፈሉ ንጉስ ናቸውልክ እንደ ሁለቱ የአጤ ቴዎድሮስ ባላንጣዎች ሁሉ የሸዋውን ንጉስ አጤ ምኒልክንም አጤ ቴዎድሮስን ለመውጋትእንግሊዞች እርዳታ ጠይቀዋቸው ነበር ነገር ግን ምኒልክ በአንድ በኩል እንግሊዞችና አጤ ዮሐንስ ጥሩ ግኑኝነትእንደነበራቸው ስለሚያውቁ በሌላ በኩል ደግሞ አጤ ቴዎድሮስ እንግሊዝን ያሸነፉ እንደሆነ እንዳይዋጉዋቸው በማሰብነገሩን በማመዛዘን ለሁለቱም ወገኖች ወዳጅ መስለው በዝምታ ምንም መልስም እርዳታም ባለመስጠታቸው በኋላ ግንእንግሊዝ በቀጥታ አጤ ቴዎድሮስን ለማጥቃት የምኒልክን እርዳታ ስትጠይቃቸው የሰጡት መልስ የምትመጡት ኢትዮጵያንአስገብሮ ለመያዝ ከሆነ በነገራቹ አልስማማም35 የሚል የማሻያማ ጽኑህ መልስ በሀገራቸው ሉሃላዊነት የማይደራደሩመሆናቸውን ነውከአጤ ቴዎድሮስ ሞት በኋላ የኢትዮጵያ ደቡባዊው ክፍል እያንዳንዱ ነገድ ከግራኝ አህመድ ወረራ በኋላ የየራሱንንጉስ ወይም ባላባት መርጦ እርስ በርሱ እየተዋጋም እየታረቀም በየአካባቢው በራሱ ሲተዳደር36 ከሺህ ስምንት መቶ ስልሳ፲፰፻፷ እስከ ሺህ ስምንት መቶ ስልሳ ሶስት ፲፰፻፷፫ ዓመተ ምህረት ድረስ ሶስት የኢትዮጵያ ገዥዎች የትግራዩ ደጃችካሳ ምርጫ በኋላ አጤ ዮሐንስ የተባሉት የላስታው ዋግ ሹም ጎበዜ ገበረ መድኅንና የሸዋው ንጉስ ምኒልክ አጤቴዎድሮስ በጣሉት የአንድነት መሰረት ላይ ማህከላዊ መንግስት ለመመስረት በየፊናቸው መዋጋት አላቆሙም ነበር እንደተክለ ጻድቅ መኩሪያ አገላለጽ የአጤ ቴዎድሮስን ፈለግ በመከተል ማህከላዊ መንግስት በመመስረት ኢትዮጵያንወደነበረችበት የአንድነት መንገድ በማህከላዊ መንግስት እንድትተዳደር ከአጤ ቴዎድሮስ ሞት በኋላ የንጉሰ ነገስቱን ቦታለመያዝና ዙፋኑን ለመውረስ ሶስቱም እርስ በአርሳቸው ክፉኛ ይሻኮቱ ነበርእንግሊዞቹ ከአጤ ቴዎድሮስ ሞት በፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ የየአካባቢው ባላንጣዎችን በመሳሪያና በሌሎች ጥቅማጥቅሞች ይደልሉ ስለነበር ለትግሬው ገዥ ለደጃዝማች ካሳ አጤ ቴዎድሮስን ለመውጋት ለእንግለዝ መንግስት ላደረጉትውለታ የጦር መሳሪያ ከአሰልጣኙ ጋር ሰጥቷቸው ስለነበር በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ ሶስት ፲፰፻፷፫ ዓ.ም. የኢትዮጵያንጉሰ ነገስት የነበሩትን አጤ ተክለ ጊዮርጊስን አሸንፈው ስማቸውን ዮሐንስ ብለው በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ አራት፲፰፻፷፬ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ሲነግሱ ከሶስቱ ተፎካካሪዎች ሁለቱ አጤ ዮሐንስና የሸዋው ምኒልክቀሩ37 በዚህ ጊዜ የኢትዮጵያ ገዢዎችን በየአካባቢው መከፋፈል ብቻ ሳይሆነ የኢትዮጵያን ኋላ ቀርነት በማየትና የስዊስቦይ መከፈቱ እንደሚጠቅመው ተረድቶ ኩዲቭ ኢስማኤል የተባለው የግብጽ መሪ አውሮጳውያንን በገንዘብ ቀጥሮኢትዮጵያን በጦር ኃይል ወርሮ ግዛቱን ከሜዲትራኒያን ባሕር እስከ ሕንድ ውቅያኖስ ለማስፋፋት በመመኘት ሐረርንወረረ ግብጽ ወረራ ያካሄደውና በቀላሉ ሐረር መግባት የቻለው ኢትዮጵያ በመሳፍንት ዘመን ሁሉም በየአካባቢው ግዛቱን32 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 7633 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 89-9234 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 102-10335 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 4736 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 1137 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. ገጽ 9-11140እያጠናከረ ተከፋፍሎ በነበረበት ሰዓት የውስጥ ሃይሎች መከፋፈላቸውን ተጠቅሞ በእንግሊዞችና በግብጾች ስምምነት38ነው ጣሊያንም ሐረርጌን ቀድሞ ለመያዝ ብዙ ሙከራዎች አድርጎ አልተሳካለትም ነገር ግን የግብጹ መሪ በአጤ ዮሐንስተቀናቃኞችም ሆነ በእንግሊዞች ግፊት ወደ ጦርነት ቢገባም ይህ ወረራ በናቀው በአጤ ዮሐንስ ጦር በሺህ ስምንት መቶስልሳ ስድስት ፲፰፩፷፮ ዓ.ም. በኅዳር ወር ጉንዲት ላይ እና በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ ስምንት ፲፰፻፷፰ ዓ.ም.ጉርዕ ላይ ሁለት ጊዜ ተሸነፈ ከሽንፈቱ በኋላም የእንግሊዝ መንግስት የራሱን የመስፋፋት ጥቅም በማሰብ ኢትዮጵያንናየተሸነፈውን ግብጽን በውል አስታረቀ በውሉም ግብጽ የያዘችው የኢትዮጵያ ግዛቶች የነበሩት ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱግብጾች ቱርኮችን በኢትዮጵያ ውስጥ አሳልፈው ወደ ምጽዋ ለመሰኘት እንዲረዱና የአጤ ዮሐንስ መሳሪያም በምጽዋ ወደብያለቀረጥ እንዲያልፍ ነበር ነገር ግን አጤ ዮሐንስ በእንግሊዝ መንግስት ተማምነው ኢትዮጵያ የተዋዋለችውን ስምምነትዋንከፈጸመች በኋላ የኢትዮጵያ ግዛቶች ሙሉ በሙሉ ሳይመለሱ በእንግሊዞች ገፋፊነትና ድብቅ ዓላማ አጤ ዮሐንስባላሰቡት መንገድ በሺህ ስምንት መቶ ሰባት ስምንት ፲፰፻፸፰ ዓ.ም. ጣሊያን በድብቅ ምጽዋን ያዘች39 ምክንያቱምበሺህ ስምንት መቶ ሰባ ሰባት ፲፰፻፸፯ ዓ.ም. የካቲት ሃያ ስድስት ፳፮ ቀን ጀርመን በርሊን ላይ ሃያላኑ የአውሮጳሀገራት አፍሪካን40 ለመቀራመት በተስማሙት መሰረት ጣሊያኖች ከሜትራድኒያን ባህር የሚዋሰኑ ሀገሮችን ለመያዝ ፈልገውፈረንሳዮች ቀድመዋቸው አልጄሪያንና ቱኒዚያን ስለያዙ ሞሮኮም ሱልጣኑ ኃይለኛ ስለነበር አብዛኛው የአፍሪካ ሀገሮችምበቀጥታም በተዘዋዋሪም በእንግሊዝ ስር ስለነበሩ41 የጣሊያን ፓርላማ ቀይ ባህርን በመመኘት ጣሊያኖች አሰብን ይዘውጣሊያንና እንግሊዝ በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ አራት ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ጣሊያን ወደ ምጽዋ ኢትዮጵያ ጠረፍ ወታደርልካ ለእንግሊዞች ከሱዳኖች እንድትከላከል ተስማሙ አጤ ዮሐንስ ከእንግሊዞች ጋር ጥሩ ግኑኝነት ስለነበራቸው እንግሊዝይከዳኛል ብለው ባላሰቡበት ሰዓት ነበር እንግሊዞች ጣሊያንን ረድተው ምጽዋ በጣሊያን የተያዘችው ምኒልክ ከጣሊያኖችጋር ወዳጅ ስለነበሩ ንጉሰ ነገስቱ በምኒልክ በኩል ሳይቀር በማጠያየቅ ላይ እንዳሉ ይባስ ብሎም ኢትዮጵያ በምጽዋ በኩልጦር መሳሪያ እንዳታስገባ ተከለከለች ምኒልክም በአጤ ዮሐንስ ትሕዛዝ ጣሊያንን ጦርነት ፈልጋ እንደሆነ ቢጠይቁ ምላሹግን ልክ ንጉሰ ነገስቱ አጤ ዮሐንስ እንዳዘዙ ተደርጎ ለማታለል ሞከሩ ለአጤ ዮሐንስም መሃዲስቶች ሀገር እንዳይዙልንከላከልላችሁ ነው በማለት አታለዋቸው ሸልመው ቢሸኙዋቸውም ጣሊያኖች ግን በፓርላማቸው የሀገር ክብር ጉዳይ ነውናየመረብ ምላሽ ገዥ ራስ አሉላ ሰሐጥን ልቀቁ ብሎናልና ሰሐጥን አንለቅም ብለው ወሰኑ የጣሊያን ፓርላማ ምጽዋ ላይ ጦርማከማቸት የጀመረው በዶጋሊው ጦርነት ራስ አሉላ ጣሊያንን ድል በማድረጋቸው የዶጋሊን ብድር ለመመለስ ነበር በዚህጊዜ ለጣሊያን ዛቻ ራስ አሉላ በእጃቸው ያሉትን አራት ጣሊያኖች አስረው ሰሐጥን በሶስት ቀን ባትለቁ እስረኞችን እገላለሁብለው ጣሊያንን ሲያስጠነቅቁ አጤ ዮሐንስም መቶ አምሳ ሺህ መቶ ፶ ሺህ ወታደሮች ይዘው ጣሊያኖችን ሊዋጉዘመቱ በሰሐጥ ግን ጣሊያኖች ከምሽጋቸው ሳይወጡና ሳይዋጉ ስለቀሩ መሀዲስቶች የጎጃሙን ንጉስ ተከለ ሃይማኖትንድል በማድረጋቸው ንጉሰ ነገስቱ ጣሊያንን ትትው በጎንደር የገባውን የደርቡሾች ጦር ለመውጋት ሰራዊታቸውን እየመሩአስመራ ላይ ራስ አሉላን ሽረው ከጣሊያኖችና ከደርቡሾች ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ጦርነት ገጠሙ ደርቡሾች ንጉስ ተክለ ሃይማኖትን ጎንደር ላይ ሲያሸንፉ የሸዋው ንጉስ ምኒልክ ጣሊያንን ለመውጋት ከሸዋ ወሎቢገቡም ንጉሰ ነገስቱ አጤ ዮሐንስ ለጣሊያኑ በቂ ሃይል ስላለ ተጨማሪ ጦር እንደማያስፈልጋቸው በመንገር ትእዛዝልከው ምኒልክን ወደ ሸዋ እንዲመለሱ አዘዙ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት ከደርቡሾች ጋር መጋፈጣቸው ምኒልክም ወደሸዋእንዲመለሱ በመታዘዛቸው የደርቡሽ ጦር ጎንደርን በመዝረፍና ቀሳውስቱን በማሰቃየት ላይ ስለነበር ንጉሰ ነገስቱ ደርቡሽንለመዋጋት ወደ መተማ ዘመቱ የምኒልክ በጦርነቱ አለመሳተፉ ብቻ ሳይሆን ዶጋሊ ላይ ጣሊያንን ያሸነፈው ራስአሉላንም42 ንጉሰ ነገስቱ በመሻራቸው በሰሜናዊ ምስራቅ በኩል ከጣሊያን ጋር በሰሜን ምዕራብ በኩል ደግሞ ከደርቡሾችጦር ጋር አጤ ዮሐንስ ብቻቸውን ጦርነት ስለገጠሙ በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ አንድ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. በጦርነት ላይሲዋጉ ንጉሰ ነገስቱ አጤ ዮሐንስ ህይወታቸው አለፈ43 መስከረም ሰላሳ ፴ ቀን ሺህ ስምንት መቶ ሰባ ስድስት38 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. ገጽ 4039 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 15640 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 337-338 Pearce, J. 2014. Prevail: The Inspiring Story of Ethiopias Victory over MussolinisInvasion, 19351941: New York, NY: Skyhorse Publishing. p. 27-2841 Pearce, J. 2014. p. 27-2842 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 161 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ.ም. ገጽ383-39043 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይት141፲፰፻፸፮ ዓ.ም. ጸሐፊው ተክለ ጻድቅ መኩሪያም ቁጭታቸውንበጉንዲትና በጉንዳጉንድ በጉራዕና በዶጋሊ በግብጻውያን ላይ ተደጋጋሚ ድል አድራጊነት ያገኘውየኢትዮጵያ ጦር በሰለጠነውም የኢጣልያ ጦር ላይ በዶጋሊ አሸናፊነትን የተጎናጸፈው የኢትዮጵያ ጦርድርጅታቸውና ስልጣኒያቸወ በዝቅተኛ ደረጃ በሚገኘው በደርቡሽ ጦር በዚህ ጊዜ መሸነፉ ከማሳዘንአልፎ የሚያስቆጭ ነው.. በማለት ነበር የገለጹት አጤ ዮሐንስ ሲሞቱ ራስ መንገሻ ዙፋኑን እንዲወርሱ በመናዘዛቸው ዙፋኑ ለራስ መንገሻ አይገባም የሚሉት ተቀናቃኝየሆኑት የትግራይና የሀማሴን መኳንንት አካለ ጉዛይን አስመራንና አካባቢዋን ከርንና ቦገስን ለጣሊያን በማስረከባቸውእነሱም ከጣሊያን ጋር መስራት ስለጀመሩ ጣሊያን እነሱን መጠቀሚያ አደረጋቸው በሌላ በኩል ደግሞበየመኳንንቱ አማካሪ መስለው የተቀመጡት ጣሊያኖችም ወዳጅ መስለው አየሰለሉ መኳንንቶችን ከማጋጨት አልፈውየጣሊያንን ድብቅ ዓላማ ያካሂዱ ነበር ከምኒልክ ጋር የሚሰራው ኮንት አንቶኔሊ የተባለውም ለአጤ ምኒልክ ያሰበይመስል አጤ ምኒልክ ሀገራቸውን ለማረጋጋት እየተዘዋወሩ በነበሩት ሰዓት ወሎ ድረስ ሄዶ ውጫሌ ላይ ሰፍረውስላገኛቸው እዚያው በጉዞዋቸው ላይ እንዳሉ ሚያዝያ ሀያ አምስት ፳፭ ቀን ሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ አንድ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. ውል እንዲፈርሙ አደረጋቸው ከውሉም አስራ ሰባተኛው ፲፯ኛው አንቀጽ በአማርኛው ላይ ባለውመስልዋቸው ተፈረመ ለአድዋው ጦርነት ምክንያት የሆነውም ውል ውጫሌ ድረስ በመሄድ በጉዞ ላይ እያሉ ያስፈረማቸውይኸው የውጫሌ ውል አስራ ሰባተኛው ፲፯ኛው አንቀጽ በመሆኑ በቦታው ስም የውጫሌ ውል ተብሎ ተጠራ44 አጤ ዮሐንስ መተማ ዘምተው መሞታቸውን ጣሊያኖች ሲሰሙ ሰሜናዊው የኢትዮጵያን ግዛት መረብ ምላሽን ኤርትራብለው ሰይመው ቅኝ ግዛታቸው በማድረግ ተቆጣጠሩት እንደ ጳውሎስ ኞኞ አጻጻፍ45...የዛሬዋን ኤርትራ ጣልያን በቅኝ ግዛትነት ሊይዙ የቻሉት ኢትዮጵያውያን መኳንንት በማህከላዊውመንግስት ላይ እየሸፈቱ ለወንድም ጠላታቸው ጠላት ለሆነው ለውጭ መንግስት በመርዳታቸው ነውከእነዚህም ጥቂቶቹ ደጃዝማች ወልደ ሚካኤል ሰሎሞን የአካለ ጉዛይ ገዥ የነበሩት ደጃዝማች ደበበአርአያና የከረን ገዥ የነበሩትና ባላንባራስ ክፍለ ኢየሱስ ናቸው......በአጤ ዮሐንስ ሞት ምክንያት የኢትዮጵያ መኳንንት በስልጣን ይገባኛል ሲራኮቱ ... አጋጣሚውይበልጥ ለጠላት አመችቶ እነሱን ጭምር በመሳሪያነት በመጠቀም ባህረ ነጋሽን ኤርትራ ብሎ በመሰየምወደ ትግራይ ሲዘልቅ ለምኒልክ ታላቅ ራስ ምታት ሆነ...በደርቡሾችና በመሀዲስቶች መነሳት ኢትዮጵያ ባልተረጋጋችበት ወቅት የምኒልክና የዮሐንስ መከፋፈልም ለግብጹ በርከፈተና ንጉሰ ነገስቱ አጤ ዮሐንስ ጦርነት ላይ ሲገደሉ በነሐሴ አስራ ሁለት ፲፪ ቀን በሺህ ስምንት መቶ ሰላሳ ስድስት፲፰፻፴፮ ዓ.ም. አያታቸው ቤት የልጆች ሞግዚት ከነበሩት ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ46 ከሚባሉት የተወለዱት በአጤቴዎድሮስ ስርወ መንግስት ደግሞ አጤ ቴዎድሮስ ሸዋን ለማስገበር ለጦርነት ወደ ሸዋ በዘመቱበት ጊዜ የሸዋው ንጉስ ኃይለመለኮት ሞተው ስለነበር በአስር ዓመቱ አስረው ያመጡት ህጻን ልጃቸው ምኒልክ በሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ ሰባት፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአጤ ቴዎድሮስ ሞት ቀደም ብሎ ከታሰረበት ያመለጠው በሺህ ስምንት መቶ ሰባ ፲፰፻፸ ዓ.ም.ከንጉሱ ከአጤ ዮሐንስ በተሰጣቸው ዘውድ ንጉስ የሆኑና ንጉሰ ነገስት ምኒልክ የሚል ማህተም በመጠቀም የሸዋንየወሎን የቤጌምድርን የጎጃምንና የሳይንትን ባላባቶች በሃይልም በስምምነትም ለአስር ዓመታት የገዙት ንጉስ ምኒልክ47በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ሁለት ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. ከአጤ ዮሐንስ ሞት በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ነገሱአጤ ምኒልክ መላው ኢትዮጵያን በተቆጣጠሩ ጊዜ ማህተማቸው ንጉስ ነገስት ምኒልክ መሆኑ ቀርቶ በምትኩ ንጉሰነገስት ዘኢትዮጵያ በሚል ቀይረው መላው ኢትዮጵያን መግዛት ጀመሩአጤ ምኒልክ በነገሱ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ፲፰፻፹ እስከ ሺህ ስምንት መቶሰማንያ አራት ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ድረስ ከጣሊያን48 በመጡ ከብቶች ምክንያት ከባድ የከብት በሽታ ተነስቶ ለአምስትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 186 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 11-1544 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያውእትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 139-14045 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 13846 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 1147 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 89-92 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 9448 Pearce, J. 2014. Prevail: The Inspiring Story of Ethiopias Victory over Mussolinis 142ዓመታት ያህል ታላቅ ረሀብ በመከሰቱ ከባድ የረሀብ ዘመን ነበርና ብዙ ከብቶችን በትግራይ በጎጃም በቤጌምድርና በላስታስለጨረሰ ሰዉም የሚበላው በማጣቱ ከባድ የሕዝብ እልቂት አስከተለ ይህ ረሀብ የተከሰተው ሀገሪቱ ከነበረውየእርስ በእርስ የየአካባቢው ንጉሶች ጦርነት ፋታ እግኝታ አጤ ምኒልክ ሀገራቸውን አረጋግተው በስርዓት ለማስተዳደርበሚሯሯጡበት ጊዜ መሆኑን በርካታ ጸሐፊዎች ዘግበውታል ከነዚህም ውስጥ የምኒልክ ጸሐፊ አለቃ ገበረ ስላሴናየጣሊያኑ መልህክተኛ ኮንት እንቶኔሊ ጥቂቶቹ ናቸው በጽሑፋቸውም ረሀቡ የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚበላ እንዳሳጣውሰብል በመጥፋቱ የሰውም የከብትም እልቂት ማስከተሉን በዝርዝር ዘግበዋል በሀገሪቱ የሚበላም የሚታረስም በመጥፋቱሕዝቡ አዲሱን የምኒልክን መንግስት እንደገደቢስ ዕድለ ቢስ ቆጥሮት ነበር በተለይም በዘመነ መሳፍንት አብዛኛው ሰውከግብርና ይልቅ ስራው ወታደርነት በመሆኑ በአጤ ቴዎድሮስና በአጤ ዮሐንስ ዘመንም ወታደሩ የባላንጣውን ከብትእየዘረፈ በማረዱ በአጤ ተክለ ጊዮርጊስና በተክለሃይማኖት አገዛዝም ባላንጣዎቻቸውን ካለወታደር ማስገበር ስለማይችሉገበሬውን ሁሉ ጦረኛ አድርገውት ነበርና በምኒልክ ዘመን ለአምስት ዓመታት ያህል በነበረው ከባድ ረሀብ ምክንያት ንጉሱለጎጃሙ ለወሎውና ለጎንደሩ ገዥዎች ከብት በረሀብ በማለቁ በዶማና በመጥረቢያ መኳንንቱም ሆኑ ተከታታዮቻቸውእንዲያርሱ መልህክት እንደጻፉላቸው ተጠቅሷል ከረሀብ ዘመን በኋላ49 የኢትዮጵያ ሕዝብ በረሀብ ደቅቆ ገና ማገገም ሲጀምርደግሞ የማይሸሸው ሌላ ሀገራዊ ችግር ገጠመው የጣሊያን ወረራ ከእርስ በእርስ ጦርነት በኋላ አጤ ምኒልክ ኢትዮጵያንአረጋግተው በስርዓት ከማስተዳደር በተጨማሪም የገጠማቸውን ፈተና ጸሐፊው ጳውሎስ ኞኞ ሲገልጸው ታላቅ ረሀብ ተነስቶሕዝቡ እንደ ቅጠል ይረግፍ ነበርና ምኒልክ ጠላታቸው ጣሊያን ከያዘው በላይ እንዳያገኝ ለዋናው ጦርነት መዘጋጀትጀመሩ ብሏልበመሆኑም ምኒልክ ለጦርነቱ ለመዘጋጀት ሲያስቡ በረሀቡ ምክንያት የሚሞተው ቀባሪ ያጣበት የጋማ ከብት ስጋየተበላበት ሰራዊቱ የተመናመነበት ባህላዊ መሳሪያዎችን ወይም ጊዜው ያለፈበት ዘመናዊ መሳሪያ በመጠቀም ጣሊያንንለመከላከል አቅም የመነመነበትና ሌላው ደግሞ መኳንንቱም ተከፋፍለው በነበረበት ሰዓት በመሆኑ ቅኝ ግዛት ለማስፋፋትለጣሊያን የተመቸ ጊዜ ነበር የራስ መንገሻ ተቀናቃኞችም ወደ ጣሊያን መግባታቸው ብቻ ሳይሆን በየአካባቢው ያሉየመኳንንቱ ረዳት የነበሩት ጣሊያኖችም በስለላ ተጠምደው መኳንንቱን እርስ በእርስ የሚያጋጩበት ጊዜ ነበርና ራስመንገሻም በማህከላዊ መንግስት ላለመታዘዝ በመወሰናቸው ከጣሊያኖች ጋር የተዋዋሉበት ጊዜ ነበር አጤ ምኒልክ ይህንንሁሉ ለማስተካከል ጊዜ ስለሚያስፈልጋቸው የመጀመሪያዎቹን የተወሰኑ የንግስና ዓመታት ጥሩ ግኑኝነት ለመፍጠርና ሃይልለማጠናከር ተጠቀሙበት በሶስትና በአራት የንግስና ዓመታት ከጣሊያን ጋር ያለውን ግኑኝነት እያለሳለሱ ግኑኝነታቸውን ያጠናክሩ ጀመርትህትና በተሞላበት መንገድ ለጣሊያን ደብዳቤ እየጻፉ ጣሊያኖችን በሁለቱም በኩል የክርስቲያን ደም መፍሰስንእንደማይፈልጉ ያሳውቁዋቸው ነበር በተለይም ችግር ካለባችሁ ለእኔ መጻፍ ስትችሉ የዮሐንስን ሀገር መውረርይገባ ነበርን የመንገሻን ከተማ መውረር ይገባ ነበርን ደም መፍሰስን አልወድም ብለው ጻፉላቸው ሌላው ደግሞ አንዳንዶቹ መኳንንትም ተደልለው ስለነበር የተጣመመውን እያቃኑ የውስጥ ችግሮቻቸውንሲያስተካክሉ መኳንንቶቻቸውን በዘዴ በመያዝ ማረጋጋት ጀመሩ በአራቱ ዓመታት ጊዜ የትግራዩን ራስ መንገሻንታረቁ የጎጃሙን ተክለ ሃይማኖትን አዲስ አበባ ጋብዘው አነጋግረው በፍቅርና በደስታ ተቀብለው ታማኝነታቸውንአረጋገጡላቸው ለራስ ሚካኤል ልጃቸውን ድረው አማች አደረጉዋቸው የዋግሹም ከጣሊያኖች ጋር ስለነበርዋግሹም ብሩን ሽረው ጓንጉልን ሾመው ግዛታቸውን ሰጡና የዋግሹም መኳንንቶች ሁሉ ከምኒልክ ጎን ቆሙ አጤ ምኒልክ የውስጥ ችግሮቻቸውን እያቃለሉ በዚህ ሁሉ መሀል መሳሪያ ማደራጀታቸውን ቀጠሉ የዉሉአለመስተካከል ብቻ ሳይሆን ሌሎቹም የአውሮጳ መንግስታት የጣሊያንን መንገድ በመቀበላቸው ክፉኛ አዝነውምኒልክ ጣሊያኖች በሙሉ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ከሀገሬ ይውጡልኝ ወደፊትም አይምጡብኝ ብለውደብዳቤ ሲልኩ ጣሊያኖች ምኒልክን ለመደለል የላኩትን ሁለት ሚሊዮን ጥይት በመቀበል መታለል እንደማይችሉምበማረጋገጥ ባገኙዋቸው የጦር መሳሪያዎች ሃይላቸውን ማጠናከር ያዙ ጣሊያኖች ሀገር ለመውረር በተዘጋጁበትጊዜ ምኒልክ እራሳቸውን በመሳሪያም በሰው ሀይልም አጠንክረው ብርቱ ሆነው ባላቸው ሀይል ተማምነው ብልህነትየተሞላበት ዝግጅት በማድረግ ብርቱ ሆነው ቀረቡ ያታለልዋቸውን ጣሊያኖች እያታለሉ በስነ ልቦናው የተነቃቃሕዝብ በማሰባሰብ ጠንካራ ክንድ ያላቸው ብርቱ መሪ ለመሆን በቁ ከሶስትና ከአራት የንግስና ዓመታት በኋላ ያልተከፋፈለና የተነቃቃ ሕዝብ በረቀቀ ጥበብ በመሳሪያ የተደራጀበመሪው በምኒልክ ላይ ከፍተኛ ግምት የሚሰጥ ሰራዊት ጠንካራ ክንድ ያለው ብርቱ መሪ ሆነው በተሻለ የጦርመሳሪያ በማደራጀትና አንዳንድ የውጭ ሀገር መንግስታትንም ወዳጅ በማድረግ ጦርነቱ ሲዳረስ የጣሊያን ወራሪነትበቀላሉ እንደማይገታ ሲያውቁ ንጉሰ ነገስቱ የጦርነት ነጋሪት አስጎስመው አዋጅ አውጀው ለዘመቻ ተነሱInvasion, 19351941: New York, NY: Skyhorse Publishing. p. 27-2849 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 126-130143የአጤ ምኒልክ ታሪካዊው አዋጅ50አሁንም ሀገር የሚያጠፋ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚሃብሐር የወሰነልንን የባህር በር አልፎመጥቷልና እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድክም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈእንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር አሁን ግን በእግዚሃብሔር ረዳትነት ሀገሬን አሳልፌአልሰጠውም ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁ አይመስለኝም አንተም እስካሁን አላስቀየምኽኝምጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለምሽትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሀዘንህእርዳኝ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም ዘመቻዬበጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህብለው አወጁእግዚሃብሔር በቸርነቱ እስካሁን ድረስ ጠላት አጥፍቶ ሀገር አስፍቶ አኖረን እኔም እስካሁን ገዛሁከእንግዲህ ወዲህ ግን ስለ ሀገሬ ስለ ኢትዮጵያ ብሞትም ሞት የሁሉ ነውና አላዝንም ደግሞእግዚሃብሔር እስካሁን በጠላት ፊት አሳፍሮኝ አያውቅም ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም51ምኒልክ ጣሊያን ጦሩን አምባላጌ ድረስ ይዞ መግባቱን ባወቁበት ጊዜ ነው ይህንን ታሪካዊ አዋጅ በማወጅየኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር በአመራራቸው ተማምኖበት እንዲነሳ በአዋጁም ምኒልክ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕዝብልብ ውስጥ የሚገባ ጥሪ ፈሪሃ እግዚሃብሔር በተሞላበት መንገድ ሕዝቡም ለዳር ድንበሩ በወራሪው ጠላት ላይ በቆራጥነትለመነሳት የሚያደፋፍር አይበገሬ መሆኑን የሚያረጋግጥበት ታላቅ የአንድነት ጥሪ ነበር ያደረጉት በእርግጥም ከምኒልክአዋጅ እንደምንረዳው ሕዝቡ በረሃብ ምክንያት ተጎድቶ ስለነበር ምንም ምርጫ ስለሌለ ብቻ ሀገሪቱን ከወራሪው ሃይልለመከላከል ሁሉም በቻለው መንገድ በጉልበቱም ሆነ በጸሎቱ እንዲከተላቸው እምነታቸውን በእግዚሃብሔርና በሕዝባቸውላይ አድርገው ነበር ያወጁት ምኒልክ የጣሊያንን የግፍ ወረራና ትዕቢት አስቀድመው የተረዱ ነበሩና ለሕዝባቸውምለሀገራቸውም ሉሃላዊነት በድፍረትና በብቃት ሕዝብን እንዲነሳ ያደረጉት የጣሊያንን የቅኝ ግዛት ህልም በቅጡ የተረዱ መሪበመሆናቸው ነው በእርግጥም አንዳንድ ከድቶ የነበረ ሰው ቢኖርም ከአዋጁ በኋላ ምኒልክ ላይ ሽፍተው የነበሩ እንደደጃማች ጓንጉል ዘገየ ዓይነቱ የውጭ ጠላት ስለመጣ የእርስዎና የኔ ጉዳይ ይቅር ማሩኝ መጥቼ ጠላት ልውጋ በማለትከምኒልክ ጎን በመሰለፍ ጣሊያንን ተዋግተዋል ጣሊያኖች በትግራዩ ራስ መንገሻና በምኒልክ መሃልም ጠብ ለማጫር ራስመንገሻን ቢያባብሉም የጣሊያኖች ሀሳብ ትግራይን ለመውሰድ መሆኑን ራስ መንገሻ በተረዱ ጊዜ አሳባችሁ እንደዚህከሆነስ እኔ የዮሐንስ ልጅ ነኝና ከናንተ ጋራ ሆኜ አጤ ምኒልክን ከመውጋት አገሬንም በእናንተ እጅ ሆና ከማየት ሞት ይሻለኛልከጣሊያኖች ጋር አልተባበርም በማለት በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስድስት ፲፰፻፹፮ዓ.ም, ምኒልክን ምሕረት በመጠየቃቸው ከምኒልክ ጎን ጣሊያኖችን ተዋግተዋል52 አንዳንድ የምኒልክ መኳንንቶቻቸውምበዘመናዊ መሳሪያዎች ታጥቆ የመጣን ጣሊያንን መግጠም ከባድ እንደሆነ ሲነግርዋቸው የምኒልክ ምላሽ ግንአንፍራ እኔ እንደሆንሁ መዝመቴን አልተውምና ስለኢጣሊያ ዘመናዊ መሳሪያና ገናናነት አትንገሩኝ ኃይልየእግዚአብሔር ነውና እጋጠማለሁ ብትዘምቱም ብትቀሩም ሬሳዬን ከጦር ሜዳ ፈልጉት ጠላትን በኋላአስቀምጦ መዝመት አይቻልምና በየግዛታችሁ ያሉትን ኢጣሊያኖች53አባርሩ...ብለው ትህዛዝ የሰጡ ቆራጥ መሪ መሆናቸውን ነው ያረጋገጡት54የክተት ዘመቻጣሊያኖች እንደርታን አጋሜን አክሱምንና አድዋን እንደያዙ አንዳንዶች ቁጥሩ ከሰባ እስከ ሰማንያ ሺህ ብለውሲመዘግቡ ዌልቤ የተባለው ጸሐፊ ደግሞ ከመቶ ሺህ በላይ ሕዝብ ጣሊያንን ለመውጋትና ለሀገሩ ለመሞት እንደተነሳ50 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 156-15951 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 234 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ 15652 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤትገጽ 23153 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 22254 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ165144ዘግቦታል በመሆኑም ምኒልክ ከአዲስ አበባ በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. ጥቅምት ሁለት፪ ቀን ህጻን አዋቂው ቄሱ አዝማሪው ሴቱ ወንዱ ወታደር ገበሬው መኳንንቱ ሳይቀር ሰራዊታቸውን አስከትለውወደ ትግራይ ለመዝመት ጉዞ ተጀመረ ፓውሌቲ የተባለው ጸሐፊ ጉዞውን ሲገልጸው ሴቶች ሽማግሌዎች አንካሶችቆማጣዎች ሕፃናት ቄሶች ሁሉ ሳይቀሩ ዳገት ሲወጡ ቁልቁለቱን ሲወርዱ ሸለቆውን ሞልተው በአንድነት ሲጓዙመመልከቱንና ህዝቡ በሙሉ በአንድነት ተነቅሎ ለወረራ የሚሄድ ይመስላል ሲል ሞልቴዶ የተባለው ጸሐፊ ደግሞአህያው በቅሎው ፈረሱ ሰዉ ሁሉ በአንድነት ሲጉዋዝ የጦር ወታደሮች አይመስሉም መንገዱ ሲጠብ መንገድ ይሰራሉማለታቸውን ጠቅሶ ጳውሎስ ኞኞ ዘግቦታል55በእርግጥም ይህ የምኒልክ ጥሪ ሕዝቡ ጾታ ዕድሜ የስራ ዓይነትና የማህረግ ደረጃን ሳይመርጥ እንዲቀላቀላቸውያደረጉበት የአመራር ውጤት መሆኑን በሚገባ ያረጋግጣል በመሆኑም ለሀገር ሉሃላዊነት ለመሞት የዘመቻውን ጥሪተቀብለው አብሮዋቸው ሊዘምቱ ወረይሉ ድረስ ከመጡት ባላባቶች ውስጥም ሀገር እንዲጠብቁ የወላሞ ወላይታ ባላባትካዎ ጦናን የወለጋ ባላባት ደጃች ጆቴን የጅማው ባላባት አባ ጅፋርን የሌቃ ባላባት ደጃች ገብረእግዚአብሔርንበመመደብ የመላ ሀገሪቱን መረጋጋት ያረጋገጡ መሪ ናቸው56 እቴጌ ጣይቱም የኢትዮጵያን ነጻነት ለመጋፋት የጣሊያኖችንበህብሪት የተሞላ የተቀነባበረ እቅድ ስለሚያውቁ ምንም ቢሆን ከዘመቻው አልቀርም ብለው የግል ሰራዊታቸውን በአዛዥዘአማኑኤል አስከትተው ከምኒልክ ጋር ባንድነት የዘመቱ ሴት ናቸውየአምባላጌውና የመቀሌው ጦርነቶችከአድዋው ጦርነት በፊት ትንሽ ቀደም ብሎ ከጣሊያኖች ጋር በአምባላጌና በመቀሌ ሁለት ከፍ ያሉ ጦርነቶችተካሂደዋል የአምባላጌው ጦርነት በጣሊያን ወታደሮች ኅዳር ሃያ ስምንት ፳፭ ቀን ሲጀመር በጦርነቱም የኢትዮጵያሰረዊት የጣሊያንን ጦር ምሽጉ ድረስ በመሄድ ብዙ ጉዳት እያደረሰ የተናቀው የኢትዮጵያ ሰራዊት እየሞተም እየቆሰለምየጣሊያንን ጦር ከቦ መድረሻ በማሳጣቱ የሚሸሽበት መንገድ እስኪያጣ ድረስ እያስጨነቀው ይህ ጦርነት የተካሄደው ገናአጤ ምኒልክ ሳይደርሱ መንገድ በጉዞ ላይ ጉሊማ የተባለው ቦታ እንዳሉ ነበር ስድስት ቀናት የፈጀው የአምባላጌውጦርነት ሶስት ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንና ከሺህ የሚበልጡ የጣሊያን ወታደሮች ያለቁበት ጦርነት በኢትዮጵያ ድልአድራጊነት በመጠናቀቁ ጣሊያን ሰራዊቱን በመቀሌ ምሽግ አከማቸ የአምባላጌው ጦርነት ላይ የኢትዮጵያው ጦርየጣሊያንን ሰራዊት ምሽጉ ድረስ እየሄደ ብዙ የጣሊያን ወታደሮች በመግደሉ ጳውሎስ ኞኞ ቮልቪቼልምን57 ጠቅሶዘመናዊ የጦር ትምህርት የሌለው የኢትዮጵያ ወታደር ምሽግ ውስጥ ያሉ የጣሊያን ወታደሮችን ምሽጋቸው ድረስበመሄድ በያዘው መሳሪያ ይዋጋ እንደነበርና የጣሊያን የጦር መኮንኖችም የናቁት የኢትዮጵያ ጦር ለነፍሱ ሳይሳሳ በያዘውጎራዴና ጦር ካሉበት ድረስ በመሄድ ስላጠቃቸው በመቀሌው ውጊያ ላይ ጣሊያኖች የውጊያውን ስልት በመቀየር ጋሊያኖየተባለው የጦር ጄኔራል ቤተ ክርስቲያን ደፍሮ ታቦት አውጥቶ አጥሮ ምሽጉን ድማሚት እንዲጠመድበት በማዘዝመሽጎ የመቀሌው ጦርነት ታህሳስ አስራ ስምንት ፲፰ ቀን ተጀመረ ጣሊያኖች የኢትዮጵያ ጦር በባዶ እግሩ እንደሚዋጋስለሚያውቁም ምሽጋቸውን ዙሪያውን በሽቦ አጥር መክበቡ ሳያንሳቸው ምድሩንም የጠርሙስ ስብርባሪ ስላነጠፉበትፈረሰኛና እግረኛው የኢትዮጵያ ጦር ወደምሽጉ ሲጠጋ የጣሊያን ጦር በጥይት ይቀበለው ነበር በኋላ ግን እቴጌ ጣይቱመላ ፈጥረው የጣሊያኑ ሰራዊት ውሃ እንዳያገኝ ከውሃው ተኝታችሁ ዉሃ እንዳይቀዳ ጠብቁ ብለው መከሩና ጣሊያኖቹውሃው ይያዝብናል ብለው ስላላሰቡ አስራ አምስት ፲፭ ቀንና ሌሊት እየተዋጉ ውሃውን እንዳይቀዳ አድርገውት ጣሊያኖችበውሃ ጥም ከመሽጉበት ሊወጡና መቀሌ ላይ ሊሸነፉ የቻሉት በሴት ብልሃት ነውጣሊያኖች ውሃ ጥም ሲያደክማቸው ውሃ መጠጣት የተፈቀደላቸው እርቅ ብለው በመጠየቃቸው ነው የኢትዮጵያሰራዊት መቀሌ ላይ የጣሊያንን ጦር የተዋጋው ከምሽግ ሳይወጡ ነው የተረፉትም ጣሊያኖች የተለቀቁት አጤ ምንክልክከጣሊያን ንጉስ በተጠየቁት የእርቅ ስምምነት ውል መሰረት ነበር እርቁም የእውነት እርቅ ባለመሆኑ ጣሊያኖችየመስፋፋት እቅዳቸውን ለማሳካት ነገሩን ለማጓተትና ሽንፈታቸውን ላለመቀበል የኢትዮጵያን ጦር ለማዘናጋት ያደረጉትበመሆኑ ንጉሰ ነገስቱ የጣሊያን ሙከራ መስፋፋትዋን ለማጠናከር በመሆኑ በሀገሬ በኢትዮጵያ የጣሊያንን ባንዲራእንዲተከልበት አልፈቅድም ብለው በመመለስ ነው ጣሊያኖችን ያሳፈሩዋቸው58 የጣሊያን ጋዜጦች የዘገቡትን ጠቅሶጳውሎስ ኞኞ እንደጻፈው ጣሊያን ሁለት ጊዜ አምባላጌና መቀሌ ላይ በአፍሪካውያን መሸነፏ ውርደት በመሆኑ መቀሌላይ ጦርነቱ እንዳያቆም ቢገፋፋም ምድር ላይ የነበረው ሃቅ ግን የኢትዮጵያ መንግስት የጣሊያንን ጦር መፈናፈኛ በማሳጣቱድብቅ የእርቅ ጥያቄው የቅኝ ግዛት ማስፋፊያውን መንገድ ለማጠናከር የታሰበ ተንኮል በመሆኑ ንጉሱ አጤ ምኒልክ55 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ160-16256 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 236-23757 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ16858 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ገጽ172-175145ስምምነቱ የጣሊያንን ባንዲራ ለመትከል ስላልሆነ ግፍ የማይወደውን አምላክ ጨምሬ በመጣችሁበት መንገድአቀበላችኋለሁ ብለው መልሰውለት አስራ አምስት ፲፭ ቀንና ሌሊት እየተዋጉ ውሃውን እንዳይቀዳ አድርገውት ነውጣሊያኖች በውሃ ጥም ከመሽጉበት ሊወጡና መቀሌ ላይ ሊሸነፉ የቻሉትየአድዋው ጦርነትበአድዋ ጦርነት ጊዜው የሁዳዴ ጾም ስለነበር ሰራዊቱ ራቱን በልቶ በሚቀጥለው ቀን ሳይመሽ በፊት ምንም ነገርአይበላም ነበርና ልክ ግራኝ አህመድ የተነሳ ጊዜም አጤ ገላውዲዎስ ሲዋጉ ጊዜው ጾም ስለነበረ ጾሙ በአዋጅ በመሻሩምኒልክም እንደ ግራኝ አህመድ ዘመን ጳጳሱን አቡነ ማቴዎስን ሰራዊቱ ከጦርነት በኋላ ይጹም ይፍቱት ያገኘውን እንዲበላቢሏቸው የጳጳሱን መልስ ጳውሎስ ኞኞ የገለጸው ጳጳሱ ግብጻዊ ነበሩና የኢትዮጵያ ጉዳይ ጉዳያቸው ስላልሆነ አልፈታምብለው እምቢ አሉ ምኒልክም እግዚሃብሔር የየዋህ አምላክ ይርዳው አሏቸው በማለት ነበርአጤ ምኒልክና ጦር ሰራዊታቸው ሀገር ለመከላከል ወደ አድዋ ጉዞ ሲጀምሩ ጥቂት መኳንንት ወደ ትግራይተልከው ከቻሉ የጣሊያንን ጦር እንዲወጉት ካልቻሉም እንዲጠብቋቸው በምኒልክ ታዘው ሄደው ነበር በአጤ ምኒልክበኩል ኢትዮጵያውያን አሰላለፋቸውን አስተካክለው ሰልፉ የተመራው በየመኳንንቱ59 የራስ መንገሻ የዋግ ሹም ጓንጉልየከፊል የራስ መንገሻ የራስ መኮንን በከፊል የደቡብና የዋግ ሹም ጎበዜ ጦር በጄኔራል ደባ ግንባር በቀኝ በኩልየወሎው የአማራ ሳይንቱ የሐረሩ የየጁው የቀኝ አዝማች ታፈሰ አባይነህና በከፊል ደቡብ የሚመራው ጦር በጀኔራልአርሞንዴ ግንባር በኩል ሌላው የቀኝ አዝማች በሻህ አቦዬ የከፊል ደቡብ በፊታውራሪ ገበየሁ የሚመራው የጨቦናጉራጌው በደጃዝማች ጫጫ የሚመራው የጎላ በፊታውራሪ ዳምጠው የሚመራው የጊሸንና በንጉስ ተክለ ሃይማኖትየሚመራው ጦር በጄኔራል አርቤርቶኒ ግንባር በኩል በንጉሰ ነገስቱ በእቴጌ ጣይቱ የከፊል በጌምድር የአፈ ንጉስነሲቡና በደጃዝማች ወልዴ አሻጋሪ የሚመራው የይፍራታ ጦር በደጀንነት ተሰልፎ የጠላትን ጦር በመጠባበቅ ከሰባ ፸ሺህ በላይ ሰራዊት አርባ ሁለት ፵፪ መድፎች ብዛት ያላቸው ጥይቶች ጦርና ጎራዴ በመያዝ የኢትዮጵያው ሰራዊትተሰለፈ በጣሊያኖች በኩል በቀኝ በሜጄር ጄኔራል አማኑኤል የሚመራው ግንባር መካከል ላይ በሰመአታ በኩል በሜጄርጄርኔራል አርሞንዲ የሚመራው ግንባር በግራ በሜጄር ጄኔራል አርቤርቶኒ የሚመራው ግንባርና በጀኔራል ጁሽሴፔ ጋሊኖየሚመራው ደጀን በመሆን አስራ ሰባት ሺህ60 የሰለጠነ ዘመናዊ የጦር ሰራዊት አምሳ ስድስት ፶፮ መድፎች ብዙ ሺህጥይቶችና ዘመናዊ ወጨፎችን በመያዝ ለጦርነት ተዘጋጀ61አድዋ ላይ ባራቲዬሪ የያዘው ምሽግ አደገኛ ቦታ ላይ በመሆኑ ባንድ በኩል የኢትዮጵያ ሰራዊትን በግላጭለማጥቃት ስለሚመቸው በሌላ በኩል ደግሞ የሰራዊቱ ስንቅ የከብቱም ቀለብ እያለቀ በመሆኑ አጤ ምኒልክ ከበውለመቀመጥ ከሰባ ሺህ በላይ የሚጠጋው ሰራዊታቸውን የሚቀልብ ስንቅ ስለሌላቸው አጤውና ሰራዊቱን አጣብቂኝ ውስጥከትዋቸው ነበር ምክንያቱም ዘማቹ ከቤቱ ከወጣ ከሰባት ወራት በላይ በማለፉ የቻለ ግማሹ በትከሻው ግማሹ በአህያበከብት የጫነው ዱቄት ጥራጥሬና በሶም እያለቀ ነበርና የፈረስና የአህያውም ቀለብ እንዲሁ እያለቀ በመሆኑ አጤ ምኒልክበዚህ ምክንያት ሰራዊታቸውን ላለማስጨረስ ጦርነቱ ቶሎ እንዲካሄድ ፈልገው ባራቲዬሪ በሰላዮቹ የኢትዮጵያውያንንእንቅስቃሴ ለማወቅ ሲሞክር ከሀገር ተወላጅ የውስጥ አርበኞች ለባራቲዬሪ የኢትዮጵያን ጦር አሳንሰው በመግለጽመኳንንቶቹም እንደታመሙ በማስመሰል የራስ መንገሻ ስንቅ እንዳለቀና ንጉሱም ወደኋላ ለመመለስ አስበዋል መባሉንባራቲዬሪ እንዲሰማ በማድረግ የውሸት መረጃ በመስጠት እነባራቲዬሪ ወጥተው እንዲዋጉ የውስጥ አርበኞች አነሳስተውጣሊያኖችን ከምሽጋቸው ወጥተው እንዲዋጉ በማድረግ አታለዋቸዋል ባራቲዬረ ለውጊያ ሲወስንም ለአጤ ምኒልክ በውስጥአርበኞች በኩል የባራቲዬሪ ህቅድ በምስጢር ስለደረሳቸው ለመዘጋጀትም ጠቀማቸው እነባራቲዬሪም በሰላዮቻቸው ካጣሩበኃላ በጄኔራሎቹና በሰላዮቹ ግፊት ለጦርነት በመዘጋጀት አጤ ምኒልክ ጦርነቱን በፈለጉት መንገድ እንዲመራ በውስጥአርበኞቻቸው በሀገር ወዳድ የኢትዮጵያ ልጆች የጠላትን ዝግጅት አስቀድመው ለማወቅ አስችልዋቸዋል ክፍተታቸውንለማስተካከልም ጠቅምዋቸዋል አቋማቸውን ደብቀው በሙሉ ልብ ጦርነቱን እንዲመሩም አስችልዋቸዋል የአድዋው የመረጃቅብብል በተሳካ ሁኔታ የተካሄደው በብዙ የሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የነደደ የሀገር ፍቅር ስሜት ነበርበጣሊያኖች62 በኩል አንዳንዶች አስራ አራት ሺህ ስልሳ ዘጠኝ ፲፬፻፷፱ ብለው የዘገቡት ሌሎች ደግሞ አስራሰባት ሺህ ብለው የዘገቡት ነጭ ወታደሮችና አንድ ሺህ አራት መቶ ፩ ሺህ ፬ መቶ የጭነት ከብት የሚነዱ ዘመናዊመሳሪያ የታጠቁ ወታደሮችና አምሳ ስድስት ፶፮ መድፎች ብዙ ሺህ ጥይቶችና ዘመናዊ ወጨፎችን ታጥቆ የካቲት ሃያ59 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራል ማተሚያቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 25960 61 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. ገጽ 25962 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 196-197146ሁለት ፳፪ ቀን ሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. በአስራ ሁለት ፲፪ ሰዓት ሰራዊቱክእንኪጨው እንዳአባ ገሪማ ገባ ሁለቱም በመጠባበቅ ላይ እንዳሉም ባራቲዬሪ ከመሽገበት ሆኖ በደረሰው የተሳሳተ መረጃየኢትዮጵያውያን ጦር መሪዎች ቀለብ ሊያመጡ ሄደዋል ግማሹም ታመዋል የሚለውን አምኖ የሀገሬው ሰራዊት ሀገሩንለመከላከል ከከተመበት ስፍራ ድረስ በመሄድ መዋጋት ሲጀምር ኢትዮጵያውያን የጠላትን ጦር ከምሽቱ አምስት ፭ ሰዓትበሶስት ግንባር በጨረቃ አንደኛው ለሌላው እንዳይደረስለት በተለያየ ግንባር ከበው የጠላትን ጦር በመለያየት እንዲዳከምከማድረግ አልፎ እንደአልቤርቶኒ ዓይነቶቹም እንዲማረኩ አድርገዋል በእርግጥ የጣሊያን ጦር በተደጋጋሚ ከተደበቀበትምሽግ ደፍሮ ስላልወጣ ከአንዴም ሁለቴ ጦርነት የጀመረ እየመሰለ ኢትዮጵያውያን ሲመጡበት ይሸሽና ወደ ምሽጉይመለስና ያናድዻቸው ስለነበር አጤ ምኒልክ በከንቱ ሊያሰልፈን ነው እንጂ እንደወትሮው እሱ ከሰፈሬ ድረስ መጥቶተኩስ ካልከፈተ አልወጣም ይሉ ነበርና ኢትዮጵያውያኑ ጣሊያንን ሰልለው ስላረጋገጡላቸው ንጉሱ እቴጌይቱና መነኮሳቱታቦት ይዘው በመነሳት ውጊያውም ከለሊቱ የጀመረ ጠዋት እስከ አራት ሰዓት ድረስ ሲዋጉ ከቆዩ በኋላ የአርቤርቶኒ ጦርለቁርስ ሲበተንና ሲሸሽ የአርሞዲን ምሳ ሰዓት ሲደርስ ክፉኛ እየወደቀ መሸሻ እስኪያጣ ኢትዮጵያዊው ወታደር የቀረበውንበጦር በጎራዴ እራስ እራሱን የራቀውን በጠብመንጃ ጣለው የጣሊያን ምሽግ ውስጥ የቀረው የጣሊያን ሰራዊት ምሽጉእንዳለም መድፍ ሲለቁበት ሁለት ሺህ የሚሆን የጠላት ሰራዊት ከምሽጉ እንዲለቅ አድርገዋልከምኒልክ ጋር አብረው የነበሩት ጸሐፊ ትህዛዝ ገብረ ስላሴም ስለአድዋው ጦርነት እንደተረኩት የካቲቱ ሀያ ሶስት፳፫ ቀን የጊዮርጊስ ዕለት የጣሊያን ጦር መንቀሳቀሱን እንደሰሙ የሐረሩ ራስ መኮንን አድዋን የወሎው ራስ ሚካኤልሰላዶ ተራራን የጎጃሙ ንጉስ ተክለሃይማኖት የጣሊያንን ምሽግ የትግራዩ ራስ መንገሻ አዲ አቡን በመያዝ ራስ ጓንጉልራስ ወሌና አጤ ምኒልክ ከኋላ ደጀን በመሆን ወታደሩ እየሸለለ እዝማሪው እያዜመ መነኮሳትና ቄሶቹ በመስቀላቸውእያማተቡ ግፋ ወደፊት ሲሉ የኦሮሞ ፈረሰኞች ያሉትን የዉሃ ምንጮች እየፈለጉ ከበው በመጠባበቅ ሁሉም ቦታቦታቸውን በተጠንቀቅ ይዘው ጠላትን ለመጋፈጥ ለጦርነቱ ሲዘጋጁ አጤ ምኒልክ እቴጌ ጣይቱ ራስ ወሌና ዋግሹም ጓንጉልበስተኋላ ደጀን በመሆን ራስ መንገሻ ዮሐንስ የትግራይን ራስ መኮንን የሐረርጌን ራስ ሚካኤል የወሎን ሰራዊትአስከትለው ንጉስ ተክለሃይማኖት የጎጃሙን ጦር ፊት ለፊት ወደ ጣሊያኖች ሲያመሩ ወታደሩ ለሊቱን በሙሉጠብመንጃውን በጫንቃው ኮሮጆውን በጀርባው የጥይት ከረጢቱን በቀኝ ጎኑ የዉሃ ታኒካውን ከግራ ጎኑ ተሸክሞበጭንጫና በሙቀት አቀበትና ቁልቁለት ሲወጣና ሲወርድ ሲንገላታ ሲደክም አድሮ ሲነጋጋ እንዳአባ ገሪማ አስር ሰዓትገብቶ መድፉን በመጥመድ ነው ጦርነቱ የተጀመረው63 የፕሮፌሰር አፈወርቅ ገብረየሱስን መጽሐፍ ዋቢ በማድረግ ጳውሎስኞኞ እንደጠቀሰው ኢትዮጵያዊውም አደጋ እንደተጣለበት ባየ ጊዜ እየፈከረየትግሬ ነፍጠኛ የሸዋ ፈረሰኛ የጎጃም እግረኛ የአማራ ስልተኛ ከብ ይቀላው ያናፋው ያንደገድገው ጀመርከእንዝርት የቀለለ የጁየ ከነብር የፈጠነ ቤጌምድሬ ከቋንጣ የደረቀ ትግሬ ከአሞራ የረበበ ሽዌ ከንብ የባሰጎጃሜ እያባረረ በየጎዳናው ዘለሰው አውሬ የነጨው ነጭ መንጋ እየመሰለ በየዱር ሆዱን ገልብጦ ወደቀና የአሞራቀለብ ሆነ የመጣው መድፍ ሁሉ ከጥይቱ ከነመንኮራኩሩ በየመንገዱ እየወደቀ ተገኘ...እንኳን በመከራበደስታ ቢሆን ሁለት ለሊትና አንድ መአልት ከራብና ከጥም ጋራ አይቻልምየባራቲየሪን መሸሽና የጦሩን መመታት ባየ ጊዜ ያ ሁሉ ወደኋላ የነበረ የጣሊያን መድፈኛ መጫኛውን በጎራዴእየቆረጠ መድፉን እየጣለ በመድፉ ስፍራ እሱ እየተተካ በአጋሰሱ እየጋለበ አስመራው ገባ ካንድ ላይ ብቻ አስራስምንት ፲፰ መድፍ አንድ ጊዜ ሳይተኮስ እስከ ጥይቱ እስከ መንክራኩ ወድቆ ቀርቶ ተያዘ...በማለት ነውአለቃ ተከለ ስላሴ እንደጻፉት64 በጦርነቱም ሃላፊውና ወታደሩ ጌታና ሎሌው ጭፍራው ከአለቃው ማንምከማንም እንዳልተገናኘና ወታደሩ እሞታለሁ ብሎ ልቡ እንዳልፈራ የቆሰለውም በመሓይም ቃሌ ገዝቼሃለኡ ኋላ ስትመለስታነሳኛለህ ይለው እንደነበር ነው የተጠቀሰው ኢትዮጵያዊው አስቀድሞ የተራራ ጫፍ ላይ በመውጣት የጣሊያን ጦርእየተማረከም እየወደቀም መሽሻ እስኪያጣ ድረስ ተዋግቶ ድሉ የሀገር ወዳዱ የኢትዮጵያዊ ሆነ የጣሊያን ጦር መሸሽቢጀምርም ኢትዮጵያዊው ምርኮኞችንና ቁስለኞችን እየለየ ከተዋጋ በኋላ የቆሰሉትን በየድንኳኑ እያከሙና ውሃ እያጠጡተንከባከቧቸው ንግስቲቱና የምኒልክ ልጅ ዘውዲቱም ለተጠማውና ለቆሰለው ውሃ ያጠጡ ጦሩንም ያበረታቱ ነበር ድልቢቀናም ከጦርነቱ በኋላ ብዙ መኳንንትና የኢትዮጵያ ወታደሮችም ህይወታቸውን ለሀገራቸው ስለሰው በዕለቱ ኀዘንም ነበርበጠቅላላው ሰባት ሺህ አምስት መቶ ስልሳ ፯ ሺህ ፭፻፷65 የጣሊያን ወታደሮች ሰባት ሺህ አንድ መቶ ፯ሺህ፻መቶ የጣሊያን ቅኝ ግዛት ጥቁር ወታደሮች ሲሞቱ አንድ ሺህ አራት መቶ ሃያ ስምንት ፲፬፻፳፰ የጠላት ወታደሮችሲቆስሉ ዘጠኝ መቶ አምሳ አራት ፱፻፶፬ የጣሊያን ወታደሮች ጠፍተዋል አስራ አንድ ፲፩ ሺህ ጠብመንጃዎችናአምሳ ስድስት ፶፮ መድፎች ተማርከዋል ከኢትዮጵያውያን በኩል አስር ሺህ ፲ ሲቆስሉ ሰባት ፯ሺህ ሞተዋል6663 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ. ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 208-21064 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ገጽ 21065 66 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ገጽ 211147ኢትዮጵያውያኖች ጣሊያንን አድዋ ላይ ድል ያደረጉት የአድዋው የመረጃ ቅብብል በተሳካ ሁኔታ በአንድነትና በብዙ የሀገርወዳድ ኢትዮጵያውያኖች የነደደ የሀገር ፍቅር ስሜት የተካሄደ ስለነበር የአድዋ ድል የመላው ኢትዮጵያዊ ድል ነውአድዋና ሴቶችየአድዋ ጦርነት ጾታ ወንድ ሴት አልለየም በአድዋው ጦርነት ከየግዛቱ የተሰበሰቡ ሴቶች ከንጉሰ ነገስቱ እስከታችኛው ድረስ ያሉት ሁሉም ድንኳን ውስጥ ሴቶቹ ቀን በስንቅ አቀባይነትም በቅስቀሳም በውጊያም በጦር መሪነትምጦር መርተው ወታደር አዘው መድፍ አስተኩሰው ውጊያ አድርገዋል ማታም ስንቅ በማዘጋጀት ሁለትዮሽ አስተዋጽዖነበራቸው ከጦርነት በፊትም ሴቶቹ ከእቴጌዪቱ ጋር ወደዘመቻው የሚጓጓዝ ሸክላ ምጣድ አክንባሎ ድስት ቋንጣውንበሶውን ደረቅ ምግቦቹን በብዛት በማዘጋጀት በጦርነቱም ሜዳ ባደሩበት ድንኳንም ሴቶች በዝግጅታቸው ለስንቅም ለዕለትምግብም ለወጥ ለቅቤው ለበርበሬው ለቅመሙ ለዕለት ምግብ ማዘጋጂያ ድልሁን ከከፍተኛ እስክዝቅተኛ ለግብርየሚሆነውን በሙሉ እያዘጋጁ ለመጠጥ ድፍድፉን ለጠላ ለጠጅ የሚሆነውን ማር በማዘጋጀት ድርብ ተግባር ነበራቸውማታ እንጀራ ሲጋግሩ አድረው የጋገሩትን እንጀራ ያስጭናሉ ከመኳንንቱም ጋር ለድርጎኛውም ለሰራዊቱም የዘማቹ ስንቅየሚሆነውን ምግብ ወጥ ሰርተው ግብር ያዛጋጃሉ ጠላ ቤቶችም በእንስራ ጠላቸውንና ጠጃቸውን ያቀርባሉ እቴጌናዘውዲቱም ለተጠማውና ለቆሰለው ውሃ ያጠጡ እቴጌዪቱም ወደ አምስት ፭ ሺህ ገደማ ሰራዊት ነበራቸውና ጦሩንምእያበረታቱ ነበር በአድዋው ጦርነት67 ምንም ሴት ብሆን በዛሬ ቀን በድንኳን ውስጥ ተቀምጬ አልውልም ብለው በሰልፉመካከል ሆነው አይዞህ በርታ ይሉ ነበር የአድዋ ድል የህጻን የአዋቂው የሴቱም የወንዱም የመላው ኢትዮጵያዊ ድልነውከድል በኋላም ምኒልክ ለሙሴ ሽፍኔ መጋቢት ሃያ ሶስት ፳፫ ቀን በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት፲፰፻፹፰ ዓ.ም. ስለአድዋ ድል የጻፉለት ደብዳቤ68...በጥጋባቸው አድዋ ላይ ተዋግተው ድል ሆኑ እኔ ግን በድንቁርናቸው ብዛት የህነዚያን ሁሉክርስቲያን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኋቸው ብዬ ደስ አይለኝም... በማለት ነበርቤርክሌይ የተባለው ጸሐፊ ደግሞ ስለአድዋ ታላቅነት የጻፈው እንዲህ በማለት ነበር...ሃያ ሺህ ያህል ወታደሮች ያሉበት የአውሮጳ ጦር በአፍሪካ ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ተሸነፈ በኔእምነት መሰረት በዘመናችን ታሪክ ውስጥ እንድ አድዋው ያለ ጦርነት የለም በእልቂቱ በኩል ሃያአምስት ፳፭ ሺህ ሰዎች በአንድ ቀን ጀምበር የሞቱበትና የቆሰሉበት ነው ፓለቲካና ታሪክአበቃ በአፍሪካ ውስጥ ታላቅ የተወላጆች ሃይል መነሳቱ ታወቀ የአፍሪካ ተወላጆች ታሪክ ተለወጠጥቁሩ ዓለም በአውሮፓውያን ላይ ሲያምጽና ሲያሸንፍ የመጀመሪያው መሆኑ ነው አበሾች አደገኛሕዝቦች መሆናቸው ከኦሪት ዘፍጥረት ጀምሮ ተጽፎላቸዋል የኛ ዓለም ገና ቶር እና ኦድዮንበሚባሉ አማልክት ሲያምን በነበረበት ጊዜ አበሾች የክርስትናን ሃይማኖት የተቀበሉ ናቸው...አሁንሁሉንም ፍላጎት አድዋ ዘጋው ... ቤርክሌይ በተቃራኒው ኃያላኑ የአውሮጳ ሀገራት አንዲት አፍሪካዊት ሀገር ጣሊያንን ድል ማድረጓ ስላስደንገጣቸውሽንፈታቸውን ላለመቀበል በኢትዮጵያ ላይ የወሰኑት ውሳኔ ከሰለጠነና ካደገ ማህበረሰብ የሚጠበቅ ሳይሆን በምትኩበኢትዮጵያ ላይ የወሰዱት እርምጃ የተዘገበው የበቀል ይመስላልመላ እውሮጳ በምኒልክ ላይ አድሟል አንድ ጥይት እንዳይገባ እንግሊዝና ፈረንሳይ በየቅኝ ግዛቶቻቸውበኩል ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ተስማምተዋል በአፍሪካ ቅኝ ግዛት የነበራቸው መንግስታት በሙሉየምኒልክን መንግስት ለማጥፋት ፕላን አውጥተዋል ...ጥቁሮች አሜሪካን ውስጥ አፍሪካ አውሮጳን ድልአደረገች በሚል ሰልፍ በመውጣታቸው አውሮጳውያን ተባብረው የአድዋ ድል በአፍሪካም በእስያምእንዳይወራ አስከለከሉ6967 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ. ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ሴንትራልማተሚያ ቤት ወይዘሮ ሰናይት ተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ገጽ 25668 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 15969 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 226148ምኒልክ በጊዜው ወዳጃቸው ለነበረው ለጂቡቲው ቅኝ ገዥ ለፈረንሳዊው ለሙሴ ላጋርድ መጋቢት ሃያ ሰባት፳፯ ቀን ሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. በጻፉለት ደብዳቤም...ዳሩ ግን እንደ እውነት ፍርድ ቢሆን ጣሊያኖች ከጦርነት ቢሉ ውጊያ እልፈልግኋቸውም ከሀገሬምየመጡብኝ እነሱ የወጉኝም እነሱ ሆነው በዚሁ ላይ ላይ መሳሪያ ሊያስከለክሉኝ ፍርድይሰጣቸዋል ብዬ ተስፋ አልነበረኝም እኔ ከነጻነቴና ከወዳጅነቴ በቀር የፈለግኋቸው ነገርአልነበረኝም ... በግፍየመጡ ሰዎች ናቸውና በጦርም በድንጋይም ቢሆን እግዚሀብሔር ሳይረዳን አይቀርም ... እኔ የክርስቲያንደምና ገንዘብ ፈላጊ አይደለሁም የምፈልገው የሀገሬን ነጻነት ብቻ ነውበማለት ነበርበእርግጥም የኃያላኑ አውሮጳውያን አድማ በርሊን ላይ አፍሪካን ለመቀራመት ካደረጉት ስምምነታቸው ጋርተመሳሳይ ይመስላል ነገር ግን አድማው ከድል ጀምሮ ከነበር የሚያበቃበትንስ ጊዜ ተስማምተው ነበር ይሆን የሚለውንጥያቄ ያስነሳል አጤ ምኒልክ ከድል በኋላ ለተለያዩ መንግስታትም ለሩሲያው ንጉስ ዊልያም ለሮም ሊቀ ጳጳስ ሊዮን፲፫ኛ ለእስፓኙ ንጉስ እልፎንሶ ፲፬ኛ ለፖርቱጋሉ ንጉስ ለቀዳማዊ ቄርልስ ለስዊስ መንግስት ርፑብሊክ ፕሬዘዳንትለቤልጅግ ንጉስ ዳግማዊ ሎዎ ፖልድ ለፈረንሳይ መንግስት ፕሬዚዳንት ለሙሴ ፊሊክስ ፎርና ለሌሎችም መንግስታትተመሳሳይ ደብዳቤ በመላክ የጣሊያንን ወረራ በተመለከተ የተሰማቸውን በመግለጽ ጽፈው ነበር70ኢትዮጵያ ነጻነትዋን ራስዋን የቻለች መንግስት ባጠገዋም ጎረቤት የሌላት መህንዋ አስቀድሞ በአውሮጳ ነገስታትሁሉ የታወቀ ነው ከግራኝ ጀምሮ እስካሁን በአህዛብ እጅ ተከባ ዘወትር በጦርነት ድካም ነው ኑራችንከአውሮጳ ጦር መሳሪያ አመጥቼ በጦርነት ድካም ነው አሳርፋሉ ስል ክንጉስ ኡምቤርቶ አባት ጋር የፍቅርን ነገርጀመርኩ... ኮንት እንቶኜሊ የሚባል የኢጣሊያ ሰው በገንዘብህ ጠመንጃ ልግዛልዎ ቢለኝ ብዙ የዝሆንጥርስና ወርቅ ሰጥቸው ይዞ ሄደ ... ጥንት ከአህዛብ ካረመኔ አገራችንን ጠብቋት የሚኖር አምላክ ከኛ ባይለይበእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረግኋቸው ከዚያ ሄጄ አስመራንም የኔ ሀገር ሁሉ በሙሉ አስለቅቃለሁ ብዬተጉዤ ሳለሁ ጄኔአራል ባልዲሴራ በጣሊያን ሰራዊት ሁሉ ላይ ተሹሜ መጥቻለሁ ...የጣሊያን ገንዘብ በላያችን ላይ የለብን ለሀገራቸውም ድንበራችን የራቀ ነው ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ነጻነቷንራስዋን የቻለች መንግስት የሆነውን በተንኮል ሊወስዱት እንዴት የቻላቸዋል በማለት ነበርመጋቢት ፳፫ ቀን መቀሌ በ፲፰፻፹፰ ዓ.ም. እንቲጮአድዋ ላይ ኢትዮጵያን ለድል ያበቃው የሰራዊቱ የንጉሰ ነገስቱና የሕዝቡ በወራሪው ጠላት ላይበአንድነት መነሳት መቻሉ ነው በብዙ የሀገር ውስጥ ተወላጆችና የውጭ ሀገር ሰዎች አገላላጽ የንጉሱና የንግስቲቱ ታላቅአመራር ሕዝባቸውን በአንድነት እንዲቆም በማድረጉ ነው አጤ ምኒልክ ጣሊያንን ለሚያህል ለገጠማቸው ጠላትተመጣጣኝ የሆነ የሰለጠነ የጦር ኃይል ዘመናዊ መሳሪያና ወታደር ባይኖራቸውም ተፈጥሮ የቸራቸው ባህሪያቸው ለአድዋውጦርነት ውሳኔዎቻቸው እንደጠቀማቸው ጄፍ71 ፒርስ ሲገልጸው ምኒልክ ባይማሩም አዋቂ ብልህና ዘመናዊ ስልጣኔያነቃቃቸው መሪ ናቸው በማለት ነበር ብዙ የሀገር ውስጥና የውጭ ሰዎችም ስለምኒልክ ያሉትን ጳውሎስ ኞኞም ሲጠቅስየአድዋው ድል ምኒልክብልህ አርቆ አሳቢነታቸውን ተጨባጭ ሁኔታ የማመዛዘንና የመገምገም ችሎታቸውን የአመራርብቃታቸውን በሚገባ አረጋግጧል በሚል ብዙዎች መጻፋቸውን72 ነውየታሪክ ጸሐፊው ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ደግሞ70 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 21171 Pearce, J. 2014. Prevail: The Inspiring Story of Ethiopias Victory over MussolinisInvasion, 19351941: New York, NY: Skyhorse Publishing. p. 27-2872 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ገጽ 141149ምኒልክ በጉልበታቸውና በኃይላቸው የመመካት ጦር የማጫር ሁኔታ አይታይባቸውም ተዋግተው ካሸነፉ በኋላበእጃቸው በወደቀው ምርኮኛ ላይ በለው ቁረጠው ግረፈው የሚባል የጭካኔና የዕብሪት ስራ አያሳዩም73የሚል ነውየዓለም ስልጣኔ እጅግ በጣም በዝቅኝተኛ ደረጃ ላይ በነበረበት በአስራ ስምንተኛው ፲፰ኛው ክፍለ ዘመንዓለማችን ላይ በደብዳቤም ሆነ በአካል ሀሳብ ለመለዋወጥ ወራትና ሳምንታት በሚወስድበት በዚያ ዘመን የተለያዩ የሀገርውስጥና የውጭ ሰዎች ምኒልክና የአድዋን ድል የገለጹበትን መንገድ በጊዜው ከወሰዱዋቸው እርምጃዎቻቸው ጋርብናነጻጽራቸውአጤ ምኒልክ ተቀናቃኞቻቸውን የሚይዙበት መንገድ እንግሊዞቹ ከአጤ ቴዎድሮስ ሞት በኋላ ለትግሬው ገዥ ለደጃዝማች ካሳ ለእንግሊዞቹ ላደረጉት ውለታ የጦር መሳሪያከአሰልጣኙ ጋር ሰጥቷቸው ስለነበር ደጃዝማች ካሳ የጎጃሙን ንጉስ ተክለ ጊዮርጊስን አሸንፈው በሺህ ስምንት መቶስልሳ አራት በ፲፰፻፷፬ ዓ.ም. ስማቸውን አጤ ዮሐንስ ብለው በመላው ኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ከነገሱበኋላ የሸዋው ገዢ ምኒልክ የጦር ሃይላቸው ባልተደራጀበት ጊዜ አጤ ዮሐንስ ከተክለ ጊዮርጊስ የማረኩትናከእንግሊዞቹ በስጦታ ያገኙትን መሳሪያዎች ተማምነው ሸዋን ለማስገበር ጦርነት ሲያውጁ ምኒልክ ግን አቅማቸውንበማመዛዘን ለንጉሰ ነገስቱ ለአጤ ዮሐንስ ገብተው እየገበሩ የራሳቸውን ግዛት በማጠናከር ቀስ በቀስ በብልሀትሃይላቸውን ማደራጀት የቀጠሉ መሪ ናቸው74 በተመሳሳይ ሁኔታም የጎጃሙ ራስ አዳልን ጦር ለመግጠም ደበረ ታቦር ከገቡ በኋላ ምኒልክ ከተቀናቃኛቸውየሚበልጥ ብዛት ያለው የጦር ሰራዊት ቢይዙም ቦታውን ዓባይ ዳር ቆላና ደጋ ዳሞትን ራስ አዳልናሰራዊቶቻቸው ያገሩ ተወላጆች ይበልጥ ስለሚያውቁት ለምኒልክ ግን ለጦርነት የማይመች መሆኑን በማወቅ ወደሸዋ የተመለሱ75 መሪ ናቸው በሌላ በኩልም ከአጤ ዮሐንስ ጋር ባላንጣነታቸው እንዳለ ሆኖ የንጉሰ ነገስቱ ታዛዥ መሆናቸውን ለማሳየት ብቻየምኒልክ ግዛት የነበረውን የከፋን ግዛት ለጎጃሙ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አሳልፈው እንደሰጡባቸው እያወቁ ለአዳልንጉስ የንግስና ዝግጅት በሺህ ስምንት መቶ ሰባ ሶስት ፲፰፻፸፫ ዓ.ም. የጎጃሙን ራስ አዳልን አጤ ዮሐንስሲሾሙ ምኒልክ ጥሪ ሲደረግላቸው የንጉሰ ነገስቱን ግብዣ ተቀብለው መሄዳቸው ተባብረው ጉዳትእንዳያደርሱባቸው ለጥንቅቄም ጭምር ነው76 ከአድዋው ጦርነት በፊት ምኒልክ የዉሉ አለመስተካከል ብቻ ሳይሆን ሌሎቹም የአውሮጳ መንግስታት የጣሊያንንመንገድ በመቀበላቸው ክፉኛ አዝነው በኢትዮጵያ የሚኖሩትን ጣሊያኖች በሙሉ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡከሀገሬ ይውጡልኝ ወደፊትም አይምጡብኝ ብለው ዶክቶር ትራቬርሲ የተባለውን ሰው ደብዳቤ አስይዘውሲልኩ የጣሊያን መንግስት ግን ምኒልክን ለመደለል ለመልህክተኛው ሁለት ሚሊዮን ጥይት በስጦታ መልክ አስይዞቢልከው ምኒልክ እናንተ ጠብ ፈለጋችሁኝ እንጂ እኔ ወዳጅነታችንን ነው የምፈልገው በማለት ስጦታውንአመስግነው ተቀብለው ጣሊያኖች በሙሉ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ያደረጉ በስጦታው እንደማይደለሉ77ያስመሰከሩ ለነጮች ያልተበገሩ መሪ ነበሩምኒልክና ሀገርንና ሕዝብን የሚመለከቱ ውሳኔዎቻቸው በአጤ ቴዎድሮስ ስርወ መንግስት እንግሊዞች ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ እንዱን ንጉስ በሌላው ላይ በማስነሳትም ሆነመሳሪያ በመስጠት የራሳቸውን ዓላማ ያሳኩ ነበር በአስራ ስምንት ስልሳዎቹ መጀመሪያ ላይ እንግሊዞች አጤቴዎድሮስን ለመውጋትና እስረኞቻቸውን ለማስለቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ባሰቡት ጊዜ ምኒልክን ከጎናቸውእንዲሰለፉ ጠይቀዋቸው ነበር ምኒልክ ግን ነገሩን በማመዛዘን የእንግሊዞችንና የአጤ ዮሐንስን ጠንካራ73 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 219-22174 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 113 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ገጽ 49-5075 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. ገጽ 10776 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 6577 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 113 ገጽ 222-223 150ወዳጅነትም ስለሚያውቁ አጤ ቴዎድሮስ እንግሊዝን ያሸነፉ እንደሆነም እንዳይዋጉዋቸው በማሰብም ለሁለቱምወገኖች ወዳጅ መስለው በዝምታ ምንም መልስ ሳይሰጡ ቆይተው በኋላ ግን እንግሊዝ አጥብቃ ስትጠይቃቸውየሰጡት መልስ የምትመጡት ኢትዮጵያን አስገብሮ ለመያዝ ከሆነ በነገራቹ አልስማማም78የሚል የማሻያማጽኑህ መልስ በሀገራቸው ሉሃላዊነት የማይደራደሩ መሆናቸውን ነው በአጤ ዮሐንስ ስርወ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ የእስልምና ሃይማኖት እንዳይኖርና ያሉትም የእስልምና ሃይማኖትተከታዮች እንዲጠመቁ ብለው ንጉሱ ሲያውጁ ምኒልክ ግን በተቃራነው መንገድ ነበርና የሚሰሩት በሺህ ስምንትመቶ ስልሳ ስምንት ፲፰፻፷፰ ዓ.ም. ግብጽ ጦርዋን በአስመራ በኩል ባመጣች ጊዜ አጤ ዮሐንስ እስላሞችንእናጥፋ ብለው ቄስ ሳይቀር እንዲዘምት ባዘዙበት ጊዜ የወሎ ሕዝብ ከዮሐንስ ይልቅ እስላሙንምክርስቲያኑንም በአንድ ዓይን በማየታቸው ለምኒልክ79 ገብቶ ገብሯል አጤ ዮሐንስ ፈላሻውን እስላሙንናአረመኔውንእምነት የሌለውን በግድ ተጠመቅና ክርስቲያን ሁን እያሉ እያስገድዱ እምቢ ያለውንም በሞትይቀጡት ነበርና በሺህ ስምንት መቶ ሰባ ፲፰፻፸ ዓ.ም. ትህዛዛቸውበኢትዮጵያ ያለው እስላም ሁሉ በክርስትና እንዲጠመቅ በየአውራጃው ትሕዛዝ ስለአስተላለፉ በዚሁበሺህ ስምንት መቶ ሰባ ፲፰፻፸ ዓ.ም. በያለበት ያለው እስላም ሁሉ በጭቃ ሹምና በመልከኛወደየአቅራቢያው ቤተክርስቲያን እየተነዳ በግድ እንዲቆርብ ተደረገ80እንደ ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ገለጻ በዚሁ ምክንያት ብዙ እስላሞች ከወሎ ዋጅራት ራያና አዘቦ ወደ ሱዳንተሰደው በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ አንድ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. አጤ ዮሐንስን መተማ ላይ በጦርነትእንደተበቀሏቸው ነው የጻፉት81 በተቃራኒው አጤ ምኒልክ ግን ሰው በራሱ ፈቃድ ፈልጎ ካልሆነ በስተቀርሃይማኖት መቀየርን ያስቆሙ ሰራዊታቸውም በየባላገሩ ቤት እንደአጤ ዮሐንስ ሰራዊቶች እንዳይዘርፍ በአዋጅየከለከሉ ትምባሆ ማጨስም እንደማያስቀጣ በመንገር ባላገሩን ከጎናቸው እንዲቆም ያደረጉና ሕዝቡ በአጤ ዮሐንስየተማረረባቸውን ነገሮች ያስወገዱ መሪ ናቸው ልክ እንደ አጤ ዮሐንስ ምኒልክም ኢትዮጵያን አጠቃላይ መግዛት ስለነበረ ሀሳባቸው በሺህ ስምንት መቶ ሰባ፲፰፻፸ ዓ.ም. አጤ ዮሐንስ የወሎውን ኢማም መሐመድ ዓሊን በኋላ ሚካኤል የተባሉትን ክርስትና ሲያነሱምኒልክ ለአጤ ዮሐንስ ታማኝ መስለው ቢገብሩም አንዳቸው ለአንዳቸው አልተኙም ነበርና ሌላውን የወሎኢማም አባ ዋጠውን በኋላ ኃይለ ማርያም የተባሉትን ክርስትና ከማንሳት በተጨማሪም የደጃዝማችነት ማዕረግሰጥተዋቸው የወሎ ገዥ በማድረግ ሚዛኑን ለመጠበቅ የሰሩ ናቸው በኋላ ግን በሺህ ስምንት መቶ ስልሳ ስምንት ፲፰፻፷፰ ዓ.ም. ምኒልክ ክርስትና ያነሱት አባ ዋጠው በከዳቸውጊዜ ተዋግተው ድል ካደረጉት በኋላ ወሎን በሙሉ ዮሐንስ ክርስትና ላነሱት ለመሐመድ ዓሊ በኋላ ንጉስሚካኤል ተብለው ለተሰየሙት ሰጥተው ይማም ብለው ሾመው82 በሕዝብ ፊት ከወሎው ገዥ ከመሐመድ ዓሊጋር አብረው ተቀምጠው ሲበሉ በመታየት በጊዜው ከእስላም ጋር መብላት እንደ ኃጢሃት ይቆጠር ስለነበርሰራዊቶቻቸው ቅር ቢላቸውም የወሎ ሕዝብ ግን ምኒልክን ተቀብሎ ገበረላቸው ይልቁንም ለመሐመድ ዓሊያልተለመደውን እስላሙን ክርስቲያን ከሆነችው የቀድሞ ሚስታቸው የባፈናን ልጅ ወይዘሮ ማናለብሽን በማጋባት83የሃይማኖት ልዩነት ያልበገራቸው በሳል አመራራቸውን ያሳዩበትና ትልቅ የሀገር መሪነት ችሎታቸውን ያረጋገጡበትወቅት ነው ከአድዋ ጦርነቱ በኋላ ብዙ ሺህ የጣሊያን ምርኮኞች ስለነበሩ ጣሊያኖች እነኚህን ሁሉ ብዛት ያላቸውን ምርኮኞችለማስለቀቅ የመጀመሪያው ሙከራቸው ምኒልክን እንታረቅ ብለው በማታለል ምርኮኞች ሊያስለቅቁና ከተለቀቁ በኋላጄኔራል ባልዲሴራ የተባለው ኢትዮጵያን በአዲስ መልክ ሊወጋቸው ማቀዱን በመጠርጠራቸው ምኒልክ በትዕቢትናበንቀት የተሞላውን የጣሊያንን ድፍረት ሲመልሱለት አዲስ ውል ተዋውለን የውጫሌ ውል መፍረሱን ለዓለምነገስታት ሁሉ ካላሳወቃችሁ ምርኮኞችን አልለቅም84 ብለው በድፍረት በመንገር ጣሊያንን መፈናፈኛ ያሳጡ መሪእንደነበሩ ጣሊያኖችም የጻፍዋቸው መረጃዎች ያረጋግጣሉ ጣሊያን ምርኮኞችን አስለቅቆ ውጊያ የመግጠም እቅዱ78 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 4779 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ገጽ 49-5080 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. ገጽ 20181 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 20182 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግስተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል ወይዘሮ ሰናይትተክለማርያም በ1999 ዓ. ም. እንዳሳተሙት ሴንትራል ማተሚያ ቤት ገጽ 105-10783 ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ስላሴ 1927-1928ዓ.ም. ገጽ 10584 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 222151ስላልተሳከለት ሀገር ሲወረርና ንጹሃን ሲያልቁ ያላወገዙት የሮማው ጳጳስ ሊዎን አስራ ሶስተኛው ፲፫ኛውወራሪው ጦር ከተማረከ በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፈሪሃ እግዚሃብሔር ያለው መሆኑን ስለሚያውቁ ምርኮኞችንእንዲለቁ እ.ኤ.አ. በሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት እ.ኤ.አ. በ፲፰፻፺፮ ዓ.ም. ጳጳሱ ለምኒልክ መንፈሳዊደብዳቤ ጻፉላቸው ምኒልክ ግን የኢትዮጵያ ጦር ሳያገግም ምርኮኞቹን አስፈትተው ጣሊያኞች እንደገና ጦርነትለመግጠም ማቀዳቸውን ስላወቁ ጳጳሱን በጣሊያኖችም በኩል ያለውን እንዲያስተካክሉ ጠይቀው ምርኮኞቹን ግንእንደማይለቁ በድፍረት ያሳወቁ መሪ ነበሩ በመጨረሻም ጣሊያን ምርኮኞቹን ለማስለቀቅ ምኒልክ የጠየቁትን በሙሉ ለመፈጸም ሁኔታዎች ስላስገደዷት እዲስየውጫሌውን ውል የሚሰርዝ ውልና ለጦርነቱም ካሳ የሚከፍል ተካቶበት ምርኮኞቹ እንዲለቀቁ ቢስማሙምምኒልክ ግን በአንድ በኩል የአውሮጳ መንግስታት እንግሊዝ ፈረንሳይና ሌሎቹም ማወቃቸውን ለማረጋገጥናየሚሉትንም መስማት ስለፌለጉ በሌላ በኩል ደግሞ ጣሊያንም በወረቀት ፊርማ ብቻ ሳይሆነ የጣሊያን መንግስትማህተም ያለበት እዲስ የውል ሰነድ እስኪደርሳቸው ድረስ ምርኮኞቹን ከአምስት ወራት በላይ አቆይተው የጠየቁትበሙሉ ሲሟላላቸው ምርኮኞቹን የለቀቁ ለሃያላኖቹ ነጮች ያልተበገሩ ምኒልክ ታላቅ አፍሪካዊ መሪ ነበሩምኒልክና ስብህናቸውብዙዎች የምኒልክ ስብህናቸው ለአመራራቸውና ለውሳኔዎቻቸው ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል ይላሉ ለዚህም ማሳያከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከመጡ ተቀናቃኞቻቸው ጋር ከተዋጉ በኋላ ባላንጣዎቻቸው ተሸንፈው ሲማረኩ በምግብምበጤናቸውም እንክብካቤ ያደርጉ ነበር ይህንን በሚመለከት ተክለጻድቅ መኩሪያ85ያሰፈሩትን ብናይምኒልክ በጉልበታቸውና በኃይላቸው የመመካት ጦር የማጫር ሁኔታ አይታይባቸውም ተዋግተው ካሸነፉ በኋላ በእጃቸው በወደቀው ምርኮኛ ላይ በለው ቁረጠው ግረፈው የሚባል የጭካኔና የዕብሪት ስራ አያሳዩም የሚል ነው በእርግጥም በአጤ ዮሐንስ ስርወ መንግስት የጎጃሙ ነጉስ ተክለ ሃይማኖትና የሸዋው ንጉስ ምኒልክ የአጤ ዮሐንስንየአስታራቂ ሃሳብ ሳይጠብቁ ተክለ ሃይማኖት ከምኒልክ ጦር በፊት የኔ ጦር በወለጋ ስለገባ ክንጉሰ ነገስቱምበጎጃም ላይ የከፋ ንጉስ ተብዬ ስለተሾምሁ ከፋና አካባቢው ጉማ ሊሙ ከወለጋ ጋር የኔ ግዛት ነውሲሉ ምኒልክ ደግሞ ጎጃሞች ከአባይ ወንዝ ወዲህ ምንም ግዛት የላቸውም በማለት አጤ ዮሐንስ ለንጉስ ተክለሃይማኖት የጨመሩላቸውን የከፋ ገዢነታቸውን ስላልተቀበሉት በሺህ ስምንት መቶ ሰባ አራት ፲፰፻፸፬ ዓ.ም.እምባቦ ላይ ጦርነት ተደረገና ንጉስ ተክለ ሃይማኖት ተሸንፈው ሲማረኩ ቆስለው ስለነበር ምኒልክ ቁስላቸውንእንደተንከባከቡላቸውና በበቅሎ ለመሄድ ስላልቻሉም በቃሬዛ በአልጋ ላይ አስተኝተው ጉዞው ወደ እንጦጦእንደተደረገ ያገሩ ባላባቶችም የተማረከውን የጎጃሙን ሰራዊት የቆሰለውንና የደከመውን ተቀብለው በየቤታቸውአስታመው ሲድኑ እንዲሸኙ አድርገዋል በእርግጥም ተክለ ሃይማኖትን አሸንፈው ያሳዩት ርህራሄና ይልቁንምለባላንጣቸው ያሏቸው አባባል እኔ ሳልፈልጋችሁ እናንተ ፈልጋችሁኝ መጣችሁ እግዚአብሔር ግን በትዕቢታችሁጣላችሁ እሁንም በየሀገራችሁ ግቡ86 በማለት የተናገሩት ባህሪያቸውን በትክክል ይገልጻል እምዬ ምኒልክየሚለውን ቅጽል ስም ያገኙት በዚህ ስብህናቸው ይሆን? በአድዋው ጦርነት ላይም የጣሊያን ወታደሮች በተማረኩበት ጊዜ ምኒልክ በአዋጅ ምርኮኞችን ሰው እንዲያበላበየመኳንንቱና በየሰው ቤት ምርኮኞችን የሰጡ ናቸው ጳውሎስ ኞኞ ቄስ ዎርዝዊዝ የተባሉትን ጠቅሶእንደዘገበው ሸዋ ውስጥ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ስልሳ አራት ፪፰፻፷፬ ያህል ምርኮኞች እንደነበሩ መግለጻቸውንናከጦርነቱ ጥቂት ወራቶች ቆይቶ አዲስ አበባ የመጣው ዌልዲ ደግሞ ...ጣሊያኖቹ ምርኮኞች አራት ሺህ ፬ሺህያህል ይሆናሉ ጣሊያን ከቅኝ ግዛቶቿ ካሰለፈቻቸው ወታደሮችም የተማረኩት87ያንኑ ያህል ይሆናሉ.. ማለቱንአስፍሮታል ምርኮኞችም ለመንገዳቸው ምግብና መድሃኒት ይሰጣቸው እንደነበር የቆሰሉትም ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙበትበቅሎ ሲሰጣቸው ያልቆሰሉት በእግራቸው ተጉዘው አዲስ አበባ ሲደርሱ ጥሩ ኑሮ ይኖሩ እንደነበር ተዘግቧል ምኒልክይህንን በማድረጋቸው የተናቀው የኢትዮጵያ መንግስት የሰለጠነ መሆኑን በስራዎቹ አስመስክርዋልከአድዋ ድል በኋላም ምኒልክ ለሙሴ ሽፍኔ መጋቢት ሃያ ሶስት ፳፫ ቀን በሺህ ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት85 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. አጤ ዮሐንስና የኢትዮጵያ አንድነት ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ገጽ 21986 ተክለ ጻድቅ መኩሪያ1982 ዓ. ም. ገጽ 219-22187 ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የመጀመሪያው እትም ቦሌ ማተሚያ ቤት ገጽ 225-226152፲፰፻፹፰ ዓ.ም. ስለአድዋ ድል የጻፉለት ደብዳቤ88...በጥጋባቸው አድዋ ላይ ተዋግተው ድል ሆኑ እኔ ግን በድንቁርናቸው ብዛት የህነዚያን ሁሉክርስቲያን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኋቸው ብዬ ደስ አይለኝም...በማለት ነበር አጤ ምኒልክ ወራሪው ጣሊያንን የሚያህል አሸንፈው ድሉን የገለጹበት ሁኔታ ምን ያህል ፈሪሃእግዚሃብሔር የነበራቸው እንደነበሩ ይገልጻልም በጣምም ያስደምማልማጠቃለያየአድዋ ድል የመላው ኢትዮጵያዊ ድል ነው አንዲት እፍሪካዊት ሀገር በዘመናዊ የጦር መሳሪያ በታጠቀና በሰለጠነየጦር ሃይል የተደራጀን ተስፋፊና ቅኝ ገዢ የወራሪውን የጣሊያንን ሃይል በባህላዊ የእጅ ጥበበበኞች ስራ በምታፈራውየጦር መሳሪያ በጦርና በጋሻ በጩቤና በአንካሴ በጦርና በጎራዴ በመመከት ከመቶ ሃያ ዓመታት በፊት ዓለምንያስደመመች ምህራባውያንን ያስደነገጠች ጣሊያንን ያስበረገገች በርሊን89 ላይ አውሮጳውያን አፍሪካን ለመቀራመትያቀዱትን ዕቅድ ደጋግመው እንዲያጤኑት ያደረገች90 ብቸኛዋ በዓለም ታሪክ ጸሐፊዎችና ሊቀ ሊቃውንቶች አድዋ ላይ ድልማድረጓ የተመሰከረላት ድል የተቀናጀችበትን የድል በሃሏን ከአጋሮችዋና ከነጻነት ናፋቂው የዓለም ሕዝብ ጋር በጋራየምታከበረው የአድዋው ድል ባለቤት ኢትዮጵያ የአፍሪካውያን የነጻነት አርማ ስትሆን ኢትዮጵያዊነት የዘር ሐረግቆጠራ ሳይሆን...ኢትዮጵያዊነት ታሪክ ሕግ ፍልስፍናና ማህበራዊ ስነ ልቦና መሆኑ91 የተረጋገጠበት የአድዋ ድልየሁሉም የነጻነት ናፋቂ ሕዝቦች ድል ነው ኢትዮጵያውያኖች ጣሊያንን አድዋ ላይ ድል ያደረጉት በአንድነትና በብዙ የሀገርወዳድ ኢትዮጵያውያኖች የነደደ የሀገር ፍቅር ስሜት የተካሄደ ስለነበርና ኢትዮጵያን ለድል ያበቃው ታላቅ አመራርምኢትዮጵያውያኖችን ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምህራብ እስከ ምስራቅ ከዳር እስከዳር በአንድነት ማንቀሳቀስ ስለቻለም ነው
ዓድዋ ለብልፅግና ጉዟችን ልንጠቀምበት የምንችለው ታላቅ ሀብታችን ነው - ጠሚ ዐቢይ አሕመድMon, Mar 02, 2020ዋልታ የሀገር ዉስጥ ዜናጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 124ኛውን የዓድዋ በዓል አስመልክቶ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ዓድዋ በየትውልዱ እየተመነዘረ ለብልፅግና ጉዞአችን ልንጠቀምበት የምንችለው ታላቅ ሀብታችን ነው ብለዋልጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የዐድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን በተመለከተ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተላለፉት ሙሉ መልዕክት-ዐድዋ በየትውልዱ እየተመነዘረ ለብልጽግና ጉዟችን ልንጠቀምበት የምንችለው ታላቅ ሀብታችን ነውበባህል በቋንቋ በብሔር በፖለቲካ አመለካከት በዕምነት የራሳችን ማንነት አለን ይህ ማንነታችን በሃገራችን ውስጥ ተገቢውን ቦታ እንዲያገኝ ታግለናል እንታገላለን ከዚህ በላይ ደግሞ ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያዊ ያሰኘን አንድነትም አለን ጣልያኖች ወደ ዓድዋ ሲመጡ የታያቸው ልዩነታችን ነው በልዩነታችን ላይ ሠርተው ኢትዮጵያን በማዳከም ቅኝ ግዛትን ሊጭኑብን አስበው ነበር የኢትዮጰያውያን ልዩ ልዩ ፀጋዎች መከፋፈያዎች የሚሆኑ መስሏቸው በተለያየ መንገድ ሞክረው ነበር ወደ ዓድዋ ሲመጡ ግን ያሰቡትን አላገኙምኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ በሉዓላዊነታቸው ጉዳይ በነፃነታቸው ጉዳይ የማይደራደሩ መሆኑን አዩኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ ፀጋ እንጂ መለያየት እንደሌላቸው ዐድዋ አሳያቸው ኢትዮጵያውያን ሕብራዊ አንድነት እንዳላቸው ዐድዋ መሰከረልዩ ልዩ ፀጋዎቻችንን የመለያያ ምክንያት የማድረግ ዘመቻ ፈፅሞ እንደማይሳካ ዐድዋ ሕያው ምስክር ነውኢትዮጵያውያን በዐድዋ ዘመቻ ዋዜማ ያልተመለሱ ጥያቄዎች ነበሯቸው ከወቅቱ መሪዎች ጋር በሁሉም ነገር የሚስማሙ አልነበሩም የዘመኑ አስተዳደር ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ አልነበረምእነዚህን ሀገራዊ ችግሮች አቀጣጥለው ሀገር የማዳከሚያ መሣሪያ ለማድረግ ጣልያኖች ሞክረዋልቁስሉን ለማዳን ሳይሆን በቁስሉ ለማስለቀስ ጥረዋል ኢትዮጵያውያን ግን ችግራችንን እንፈታለን ሀገራችንን እንጠብቃለን ብለው አልተቀበሉትም ጥያቄዎች ሁሉ የሚመለሱት ሀገር ስትኖር መሆኑን ኢትዮጵያውያን ያውቁ ነበር ኢትዮጵያውያን ለቁንጫ ሲሉ ቤት የሚያቃጥሉ ለአረም ሲሉ ማሳውን የሚያጠፉ አልነበሩምኢትዮጵየውያን ሀገራቸውን በተመለከተ ዘላቂ መርሕ አላቸው ዋልታና ማገሩን እጠብቃለሁ ውስጡንም አፀዳለሁ የሚል ቤቱ ቤት ሆኖ እንዲኖር ዋልታና ማገሩን ማጥበቅ ያስፈልጋል ቤቱን ለማፅዳት መጀመሪያ ቤቱ ቤት መሆን አለበት ቤቱ በሌለበት የቤቱ ፅዳት አይኖርምቤቱ ግን ሊቆሽሽ ወይም ተባይ ሊያፈራ ይችላል ቤቱን እየጠበቅን እያፀናን ውስጡን ደግሞ እናፀዳለንዐድዋ ሌላም ትምህርት ሰጥቶናልችግሮቻችንን እንዴት ማየት እንዳለብን ዐፄ ምኒልክና የዐድዋ ዘማቾች ለዘመኑ ችግር በቂ ዝግጅት አድርገው ነበርያዘጋጇቸው መድፎች ከጣልያን መድፎች የተሻሉ ነበሩጣልያን ወታደሮቹን ካንቀሳቀሰበት አቅም በላይ ሕዝቡን ለማንቀሳቀስ ችለዋልየት ቦታ እንዴት ጠላታቸውን ገጥመው ሊያሸንፉ እንደሚችሉ አቅደዋል የዐድዋ ድል የዚህ የላቀ ዝግጅት ውጤት ነውከአርባ ዓመት በኋላ ጣልያን ለሁለተኛ ጊዜ ሲመጣ ልንቋቋመው ያልቻልነው በዐድዋ ዘመቻ ያደረግነውን ነገ ተኮር ዝግጅት ስላላደረግን ነውጣልያን በአየር ሲመጣ በመሬት ገጠምነው ጣልያን የምድር ላይ መሣሪያዎቹን አዘምኖ ሲመጣ እኛ ያለንን ይዘን ጠበቅነው ከዘመኑ ቀድመን አልተገኘንምዛሬ ከትናንት የተሻልን መሆናችን ብቻ በቂ አይደለም ሥልጣኔ ማለት ከነገ መቅደም ነው ነገ ከሚመጣው ችግር በልጦ መገኘት ነውከዐድዋ የምንማረው አንዱ ትልቅ ትምህርት ይህ ነው ትናንት ለገጠመን ችግር መፍትሔ የመስጠት ችሎታ ነው ዛሬ ለሚገጥመን ችግር መፍትሔ ማስቀመጥ ብልሀት ነው ወደፊት ከሚመጣው ችግር በልጦ መገኘት ግን ጥበብ ነውየዐድዋ ዘመቻ የጦርነት ዘመቻ ብቻ አልነበረም የቴክኖሎጂ የዲፕሎማሲ የትዕግስት የፖለቲካ የሎጀሰቲክ የፍቅርና የይቅርታ ዘመቻ ጭምር ነበርዘመኑ የተሻሉ መሣሪያዎችን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን መሣሪያዎቹን አውቆ መጠቀም ለመቻል ዝግጅት ተደርጓልጦርነትን ለማስቀረት እንዲቻል ብቻ ሳይሆን ለዝግጅት ጊዜ ለማግኘት እንዲቻል ዲፕሎማሲያዊ ሥራ ተሰርቷልችግር በትክክለኛው ጊዜና ሁኔታ ለመግጠም ሲባል በፈታኝ ትዕግስት ውስጥ ታልፏል ለዚያ ሁሉ ሠራዊት የሚሆን ስንቅና ትጥቅ ለማዘጋጀት ሕዝቡን አንቀሳቅሰዋል ውስጣዊ ቅራኔዎች ሀገራዊ አደጋ እንዳያስከትሉ የዕርቅና የመቻቻል ሥራዎች ተሰርተዋልዛሬም እንደ ሀገር የገጠመንን ችግር ለመፍታት የዐድዋ ዘማቾች የተጠቀሙባቸውን ዘርፈ ብዙ መፍትሔዎች መጠቀም አለብን ቴክኖሎጂን መጠቀም ዲፕሎማሲያዊ ትግል ማድረግ በትዕግስት ጊዜ መስጠት የፖለቲካ መፍትሔዎችን መስጠት አቅም ማጠራቀም በፍቅርና በይቅርታ መንገድ መጓዝ ሌሎችም ያስፈልጉናልየዐድዋ ዘመቻ ድል እንዴት መጠናቀቅ እንዳለበት ያስተማረ ታላቅ ታሪካችን ነው ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነው የመጣባቸውን ወራሪ መክተዋል መክተዋል ብቻ ሳይሆን አሳፍረው መልሰዋል ነገር ግን የውጭ ጠላታቸውን ድል ያደረጉበትን አቅም የራሳቸውን ጉዳይ ለመፍታት አላዋሉትም አንድ ታላቅ ሀገራዊ ድል ካገኘን በኋላ ውስጣዊ ጥንካሬያችንን በድላችን ልክ ለማድረግ ካልሰራን ድላችንን የሚያሳጣ ዕጣ ፈንታ ሊገጥመን ይችል ይሆናል ለምን አሸነፍን ያሸነፍንበትን ምስጢር ለውስጣዊ የሀገር ግንባታ እንዴት እንጠቀምበት የዛሬውን ጠላት አሸነፍን ነገር ግን ኢትዮጵያ ነገ ከሚመጣው ጠላት የተሻለች አድርገን እንዴት እናቆያትእነዚህን ጉዳዮች አለማየት ከዐድዋ ድል አርባ ዓመት በኋላ በማይጨው ዘመቻ የገጠመንን እንዲገጥመን መፍረድ ነውያ እንዲሆን ዛሬ ፈፅመን አንፈቅድም በዐድዋ ድል የተነሳሱ ብዙ ሕዝቦች ሮጠው ቀድመውናል የተሻለ ሀገረ መንግሥት ገንብተዋል የተሻለ ብሔረ መንግሥት አዳብረዋል ዴሞክራሲያቸውን የፍትሕ ሥርዓታቸውንና ኢኮኖሚያቸውን አዘምነዋል ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ሲቆረጥ ለምን ዝም እንላለን የመደመር ጎዳና ኢትዮጵያ የዐድዋ ድሏን በሚመጥን ደረጃ እንድትጓዝ የተገነባ መንገድ ነው ለዐድዋ ድላችን የሚመጥነው የኢትዮጵየ ከፍታ ብልፅግና ነው እኛ ከሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝቦች የመጣን የዐድዋ ዘማቾች ነን አንድ ሆነን ጠላታችንን ተዋግተን ድል እንዳደረግነው ሁሉ አንድ ሆነን ሀገር እንገነባለን አንድ ሆነን ሀገራችንን ወደ ብልፅግና እናደርሳለንየትናንት እናቶቻችንና አባቶቻችንን ድል ዛሬ እንዳከበርነው ሁሉ የእኛንም ድል ነገ ልጆቻችን ያከብሩታል እነርሱ የቅኝ ግዛት ቀንበር ሰብረው ነው እኛ ደግሞ የድህነትን ቀንበር እንሰብራለን እነርሱ ነፃ ሀገር ፈጥረዋል እኛ ደግሞ ዴሞክራሲያዋፍትሃዊና ሰላማዊ ሀገር እንፈጥራለን እነርሱ በመደመር ተጉዘው የዐድዋን ድል አስገኝተዋል እኛም በመደመር ተጉዘን የብልፅግናን ድል እናስገኛለን
በደቡብ ክልል ከ 20 ሺህ በላይ አባወራ አርብቶአደሮች በመንደር ሊሰባሰቡ ነው, .._2011__. 0 324 243 ; 5; ሀዋሳ ታህሳስ 162004 ዋኢማ -በደቡብ ክልል ከ 20 ሺህ በላይ አባወራ አርብቶአደሮችን በመንደር ለማሰባሰብ የሚያስችለውን መሰናዶ ማጠናቀቁን የክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነትና የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ጌቱ ዓለሙ ለዋልታ እንዳስታወቁት አርብቶአደሮችን በመንደር የማሰባሰቡ ሥራ የሚካሄደው በደቡብ ኦሞ እና በቤንች ማጂ ዞኖች ነው የመንደር ማሰባሰቡ የሚካሄደው በዞኖቹ በሚገኙ በዳሰነች በሐመር በኛንጋቶም በፀማይ በማሌ በሰላማጎ በቤሮ በማጂ በሜኒትሻሻ እና በሜኒትጎልዲያ ወረዳዎች መሆኑን ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪው አብራርተዋል ቢሮው ባለፉት ሦስት ወራት በሰፈራ ፕሮግራም ለመካተት ፍቃደኛ የሆኑ አባወራዎችን መለየቱን የገለጹት የሥራ ሂደቱ አስተባባሪ ከተያዘው የበጀት ዓመት አጋማሽ ጀምሮ አርብቶአደሮቹን የማስፈር ሥራ እንደሚጀመር ጠቁመዋል እንደ አቶ ጌቱ ማብራሪያ አርብቶአደሮቹ የሚሰባሰቡባቸው መንደሮች ተፋሰሶችን ተከትለው የተዘጋጁ በመሆናቸው ቀደም ባሉት ጊዜያት አርብቶአደሩ በዝናብ እጥረት ምክንያት ግጦሽ ፍለጋ ከቦታ ቦታ በመጓጓዝ ይደርስበት የነበረውን ድካም ያስቀራሉ በአንድ አካባቢ ተረጋግቶ የመኖር ባህልን እንድያዳብርም ያስችላል ለሠፈራ በተመረጡት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች የውሃና የጤና አገልገሎቶች የተዘጋጁ ሲሆን ቀሪ የመሠረተ ልማት ተቋማትን በሂደት የማሟላት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አመልክተዋል ከመሠረተ ልማት ሥራዎች በተጨማሪ ለሠፋሪ አባወራዎች በነፍስ ወከፍ ሁለት ነጥብ አምስት ሄክታር የእርሻ መሬት የግብርና መገልገያ ቁሳቁሶችና ግበዓቶች እንደሚቀርቡላቸው የሥራ ሂደት አስተባባሪው ገልጸዋል በደቡብ ክልል በ 2003 የበጀት ዓመት በመንደር የተሰባሰቡ 10 ሺህ 995 አባወራ አርብቶአደሮች በአሁኑ ወቅት የተረጋጋ ኑሮ በመምራት ላይ እንደሚገኙ ከሥራ ሂደት አስተባባሪው ገለጻ ለመረዳት ተችሏል ,
በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ያስችላሉ አቶ ጁነዲን ሳዶ, .._2012__. 0 195 146 ; 0; 5; አዲስ አበባ የካቲት 22 ቀን 2004 ዋኢማ - በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር አስታወቁ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲ ሳዶ 640 ሚሊዩን ብር በጀት ግንባታው በመፋጠን ላይ ያለውን የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ሰሞኑን ከጎበኙ በኋላ እንደተናገሩት በሃገሪቱ ሶስተኛ የሆነው ይኽው ፋብሪካ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር ሥራ አጥነትን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ያስችላልከፋብሪካው ግንባታ በተጓዳኝ የሚከናወነው የተንደሆ ወጣቶች ልማት ፕሮጀክትም የአካባቢው ህብረተሰብ የልማት ተጠቃሚነት የተረጋገጠበት ነው ብለዋልእንዲሁም በ40 ሚሊዩን ብር በጀት በመከናወን ላይ ያለው የአፋር ከተሞች የኤሌትሪክ ሃይል ፕሮጀክት የከተሞች የእድገት ፖኬጅ ለማፋጠን ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋልበተጨማሪ በ98 ነጥብ 7 ሚሊዩን ብር በጀት በመከናወን ላይ የሚገኘው የሰመራ ዩኒቨርስቲ የማስፋፊያ ሥራም ዩኒቨርስቲውን ተጠቃሽ የምርምርና ስርፀት ማእክል ለማድረግ ያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል ከዚህም ሌላ ከአዩዲን ጋር የተቀላቀለ ጨው ማምረት የጀመረው የአፍዴራ ጨው አምራች ኩባንያ የአርብቶ አደሩን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት የተሰጠበት መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል ንፁህ የመጠጥ ውሃ የጤና የመንገድና የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀሙን አበረታች መሆኑ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ያስችላሉ አቶ ጁነዲን ሳዶ ,
አርብቶ አደሩን የዘላቂ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ክልል አስታወቀ, .._2012__. 0 307 230 ; 0; 5; አዲስ አበባሚያዚያ 192004 ዋኢማ - በደቡብ ብሔሮችብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አርብቶ አደሩንና ከፊል አርብቶ አደሩን የዘላቂ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ መሆኑን የክልሉ አርብቶ አደሮች ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ የክልሉ አርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅሩ ኛካል ለዋልታ እንደገለፁት ቢሮው አርብቶ አደሩም ሆነ ከፊል አርብቶ አደሩ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ከቦታ ቦታ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት በአንድ ቦታ ተረጋግቶ እንዲኖር የማድረግ ሥራ እየሰራ ነው እንደ አቶ ፍቅሩ ማብራሪያ አርብቶ አደሩ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ሲንቀሳቀስ በውስጥም ሆነ ከውጭ ለተለያዩ ግጭቶች የመጋለጡ እድል የሰፋ ነበር ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የሚያጋጥሙትን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ድርጅትኢጋድ እና ከአዋሳኝ አገሮች ጋር በመተባበር አርብቶ አደሩን ያሳተፈ ጥናት ተከናውኗል በጥናቱም አርብቶ አደሩ በአንድ አካባቢ ተወስኖ የተረጋጋ ሕይወት በመምራት የዘላቂ ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ ለመሆን ሙሉ ፍላጎቱን አሳይቷል ብለዋል የኢፌዲሪ መንግስትም ሆነ የክልሉ መንግስት የአርብቶ አደሩን ፍላጎትና አገሪቱ የነደፈቻቸውን የልማት ዕቅዶች መነሻ በማድረግ አርብቶ አደሩንና ከፍል አርብቶ አደሩን በልማት ለማሳተፍ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሩ ተናግረዋል በአሁኑ ወቅት በደቡብ ብሔሮችብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በተለይም በደቡብ ኦሞ ዞን የኩራዝ ስኳር ኮርፖሬሽን ወደ ሥራ መግባቱን ተከትሎ አርብቶ አደሩን የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል የኩራዝ ስኳር ኮርፖሬሽን መቋቋሙን ተከትሎ አርብቶ አደሩ በመስኖ በመታገዝ በሰብልና ቋሚ ተክሎች ልማት ላይ በመሳተፍ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ የድጋፍና ክትትል ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል እንደ አቶ ፍቅሩ ገለፃ አርብቶ አደሩ ቶሎ ወደ ልማቱ እንዲገባም የመስኖ ውሃና የእርሻ መሬት የሚያገኝበት ሁኔታ ተመቻችቷል በአካባቢው እየተስፋፋ ያለውን የመሠረተ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት በአግባቡ ከተጠቀመ አርብቶ አደሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ ወደ ባለሀብትነት እንደሚሸጋገርም አቶ ፍቅሩ ተናግረዋል በአሁኑ ሰዓት የክልሉ መንግስት አርብቶ አደሩን በመንደር በማሰባሰብ በመስኖ ውሃ በመታገዝ የሸንኮራ አገዳ አልምቶ ለፋብሪካው በማቅረብ ገቢ እንዲያገኝ ለማስቻል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል የኦሞ ወንዝን ተከትለው ለሚቋቋሙ ስድስት የስኳር ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግል የሸንኮራ አገዳ ተከላ ከተያዘው ዓመት መጀመሪያ አንስቶ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትን ጠቅሰን በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል የፕሮጀክቱ ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው በስኳር ፋብሪካዎቹ የግንባታ ሂደት የአካባቢው አርብቶ አደሮች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉ ፋብሪካዎቹ የምርት አገልግሎት ሲጀምሩ ደግሞ የሸንኮራ አገዳ ቅጠሎችን እና የሞላሰስ ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ሥራዎችን ማከናወን ይችላሉ ,
በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሰፈራ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ የአርብቶ አደሩን የተንቀሳቃሽ ህይወት ወደ ተረጋጋ ቋሚ ኑሮ ለመመለስ ለም በሆኑ አካባቢዎች በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሰፈራ ማካሄድ እንደሚያስፈልግ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ገለጹ ሚኒስትሩ አቶ አባይ ጸሀዬ ዛሬ በድሬዳዋ ከተማ የተጀመረውን የአርብቶ አደር አካባቢ ህዝቦች ልማት ኮንፈረንስ በንግግር ሲከፍቱ አርብቶ አደሮችን በወንዞች አካባቢ በማስፈርና መስኖን መሰረት ያደረገ ልማት ማከናወን የአርብቶ አደሮችን ዘላቂ ኑሮ መመስረት እንደሚያስችል ገልጸዋል ውሃና ግጦሽ ባለባቸው ቦታዎች በራሱ ጊዜ እና ፍላጎት መስፈር የጀመረው አርብቶ አደሩ ሁኔታዎች ከተመቻቹለት ከሚታየው በበለጠ የመንግስትን ፍላጎት ማሳካት እንደሚችል ተናግረዋል እንዲሁም መሰረተ ልማት ማሀበራዊ አገልግሎት ከአርብቶ አደሩ ነባራዊና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በመንደፍ የአርብቶ አደሩን ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚቻል ጠቁመዋል በዚህም በርካታ የሚፈሱ ትላልቅ ወንዞች ለም አፈር ድርቅን መቋቋም የሚችሉና ምርጥ የእንስሳትና የግጦሽ ሀብት እንዳሉ አቶ አባይ አመልክተዋል እስከ ዛሬ የተሰሩት ስራዎች በተጨባጭ የአርብቶ አደሩን ችግር ባለመፍታታቸውና ብቃት ያለው ፖለቲካዊ አመራር አለመኖሩ አሰራሩ ትርጉም ባለው ደረጃ ሊራመድ እንዳልቻለ ገልጸዋል የመልካም አስተዳደር ልማት ራእይ እውን ሊሆን የሚችለው የአርብቶ አደሩ አካባቢ ያለው የመስተዳድር አካል አቅም ሲጠናከር በመሆኑ በአቅም ግንባታው ዘርፍም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል እስከ ሚያዝያ 5 በሚቆየው በዚሁ ኮንፈረንስ ላይ ከኦሮሚያ ሶማሌ ደቡብ ከአፋር ክልሎች ከፌዴራል መስሪያ ቤቶችና ከልዩ ልዩ የሀብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 113 ተሳታፊዎች ሆነዋል
በኦሮሚያ በአርብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች አካባቢ እየተካሄዱ ያሉ የሰፈራ ፕሮግራሞች ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆኑ ተገለፀ , .._2012__19. 0 254 191 ; 5; አዲስ አበባ ግንቦት 12 2004 ዋኢማ - በኦሮሚያ ክልል በአርብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች አካባቢ እየተካሄዱ ያሉ የሰፈራ ፕሮግራሞች የማህበረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በምፍታት ተጨባጭ ለውጥ በማምጣት ላይ እንደሚገኙ የክልሉ አብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች ልማት ኮሚሽን አስታወቀ የኦሮሚያ አርብቶአደሮችና ከፊልአርብቶ አደሮች ልማት ኮሚሽን የኮሚዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መገርሳ ቀነኒሳ ለዋልታ እንዳስታወቁት በክልሉ እየተካሄደ ያለው የሰፈራ ፕሮግራም የአርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን ማህበረሰብ የውሃ የመሰረተልማት አቅርቦት ችግሮችን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት እያስቻለ ነው እንደ ባለሙያው ማብራሪያ በክልሉ አርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን በማስፈር በርካታ የመስኖና የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተከናውኗልበፈንታሌ ወረዳ ብቻ የተከናወኑት የመስኖ ፕሮጀክቶች ከስምንት ሺ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ እንዳደረጉ የጠቆሙት ባለሙያው በወረዳው የተከናወኑ የትምህርት ቤቶች የጤና ማዕከላትና የእንስሳት ህክምና መስጫ ክሊኒኮች የንጹህ ውሃ የኤሌከትሪክና የስልክ መሠረተ ልማቶችም አርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል በወረዳው እየተካሄዱ ያሉ ፕሮጀክቶች አርብቶአደሩም ሆነ ከፊል አርብቶአደሩ በአንድ ቦታ ሰፍሮ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልክና ቀድሞ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ የሚያባክነውን ጊዜና ጉልበት በልማት ሥራ ላይ እንዲያውል እንዳስቻሉትም አቶ መገርሳ ገልጸዋልእንደ አቶ መገርሳ ማብራሪያ በፈንታሌ ወረዳ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ዘርፍ ለአፈርና ውሃ እቀባ ለእርከን ሥራና ደንን መልሶ ለማልማት ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራው ሥራም በወረዳው በስድስት ቀበሌዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ አድርጓል የፈንታሌ ወረዳን ተሞክሮ በመወሰድ በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አቶ መገርሳ ጠቁመው በቦረና ዞን ድሬ ወረዳ የውሃ ጉድጓድ በማውጣት እንዲሁም በጉጂ ዞን የገናሌን ወንዝ ተፋሰስ ተከትሎ አርብቶአደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋልበአርብቶአደሩ አካባቢዎች ቀደም ሲል ከውሃና ከግጦሽ ቦታዎች እጥረት የተነሳ በተወሰኑ ቦታዎች ተደጋጋሚ ግጭቶች ይስተዋሉ እንደነበር ያሰታወሱት አቶ መገርሳ አሁን በሰፈራ ፕሮግራሙ ምክንያት ችግሩ መፈታቱን አብራርተዋል,
የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር ውጤታማ እየሆነ ነው, - ; .._2014. 0 272 203 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 12 2006 ዋኢማ - በአራት ክልሎች ተግባራዊ የተደረገው የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር እስከአሁን ያለው አፈጻጸም ስኬታማ እንደነበር የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ገለጸ - ; የመርሐ ግበሩ ሁለተኛ ምዕራፍ አጠቃላይ አፈጻጸም የሚገመግም ጉባኤ በአዳማ ሲካሄድ በመርሐ ግብሩ 2ኛ ምዕራፍ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል - ; የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው በጉባኤው ላይ በመርሐ ግብሩ ሁለተኛው ምዕራፍ የበርካታ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ሕይወት መቀየር መቻሉን ተናግረዋል - ; በጉባኤው ላይ የመርሐ ግብሩ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የመርሐ ግበሩ ተጠባባቂ አስተባባሪ አቶ ሰይድ ይመር በሁለተኛው ምዕራፍ የትግበራ ወቅት ለማከናወን ከታቀደው ውስጥ 99 በመቶውን መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል - ; የአርሶ አደሩን የኑሩ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የትምህርት የሰው እና የእንስሳት ጤና የመጠጥ ውሃ እና የአነስተኛ መስኖ ብሎም የማሕበረሰብ መንገድ ሥራዎች በመርሐ ግብሩ የተከናወኑ ናቸው - ; ይህም በሚሊየን ለሚቆጠሩ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮች የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ በጉባኤው ላይ ተነስቷል - ; በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ከክልሎች የመጡ የሥራ ኃላፊዎች ሁለተኛው ምዕራፍ መርሐ ግበሩ ሴቶችን ማሳተፉ ማህበራትን በማደራጀት የህብረተሰቡን ተሳትፎ ያማከለ መሆኑ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል - ; መርሀ ግብሩ በአራቱ ክልሎች በሁለተኛው ምዕራፍ ከመንግስትና ከተለያዩ ለጋሽ አካለት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተሰራ ሲሆን ከ139 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጭ ተደርጓል - ; የአርብቶ አደር መርሀ ግብሩ በአፋር በኢትዮጵያ ሶማሌ በኦሮምያ እና በደቡብ ክልሎች የሚገኙ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ኑሮ ማሻሻል የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን መሰረት አድርጎ የሚሰራው ነው - ; የ15 ዓመታት የቆይታ ጊዜ እንዲኖረው ተደርጎ የተቀረጸው መርሀ ግብሩ በየአምስት አመት ጊዜ ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን ሁለት ምዕራፎችን ተሻግሯል ,
በክልሉ ያሉ አርብቶ አደሮችንና ከፊል አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ ተገለፀ, .._2012_. 0 253 190 ; 5; ብርቆት ነሃሴ 82004ዋኢማ - የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲኢሶህዴፓ በሶማሌ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት የአርብቶ አደሩንና ከፊል አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባካሄዳቸው እንቅስቃሴዎች አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን አስታወቀ ፓርቲው 7ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በጀረር ዞን ብርቆት ወረዳ ሰሞኑን ባካሄደበት ወቅት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር እንደተናገሩት ኢሶህዴፓ ባለፉት ሁለት ዓመታት የክልሉን አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማህበረሰብ በማሳተፍ ባካሄዳቸው እንቅስቃሴዎች በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች አበረታች ውጤት አስመዝግቧል በክልሉ የትምህርት ጤና ንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ሽፋንን ለማሳደግና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው ጥረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን የገለጹት አቶ አብዲ በአሁኑ ወቅት የክልሉ የአንደኛ ደረጃ የትምህርት ሽፋን ከ80 በመቶ በላይ መድረሱንና ይህም አገሪቱ በ2015 እ.ኤ.አ. በትምህርቱ ዘርፍ የሚሊኒየም ደቨሎፕመንት ጎልን ለማሳካት የምታደርገውን ግስጋሴ ሊያሳካ የሚያስችል ውጤት ነው ብለዋል እንዲሁም የክልሉ የከተማና የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ62 በመቶ በላይ ማድረስ የተቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በ68ቱም ወረዳዎች የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የእናቶችንና የህጻናት ሞትን መቀነስ እየተቻለ መሆኑን ተናግረዋል ለአካባቢው ህብረተሰብ የኢኮኖሚው መሰረት የእንስሳት ሃብት ልማት በመሆኑ የክልሉ መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው በማለት በዘርፉም በርካታ አርብቶ አደሮች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል ከዘርፉ የክልሉ አርብቶ አደሮች ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል በወንዝ ዳርቻዎችና ለልማት አመች በሆኑ ቦታዎች በመንደር በማሰባሰብ የዘላቂ ልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው ጥረት ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ ከ144ሺ በላይ ቤተሰቦችን በመንደር በማሰባሰብ ተጠቃሚ እንዲኑ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል እንዲሁም በአካባቢው ያለውን ልማት ለማረጋገት አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው በዚህም በ68 ወረዳዎች አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል የኢሶህዴፓ 7ኛ ጉባኤም በጀረር ዞን ብርቆት ወረዳ መደረጉ አካባቢው ከዚህ ቀደም የጸረ-ሰላም ሃይሎች መከማቻ ቦታ ሆኖ የቆየ መሆኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት ጉባኤውን ያለምንም የጸጥታ ችግር በአካባቢው ማካሄድ መቻሉ የክልሉ ጸጥታ አስተማማኝ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል እንዲሁም በክልሉ ከተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም በተጨማሪ እንደ መንገድ መብራትና የኮሙኒኬሽን አውታሮች ከቅርብ ዓመት ወዲህ በመንግስት ጥረት በመስፋፋታቸው የክልሉ የኢንቨስትመንትና የከተሞች እድገት አበረታች ውጤት የተመዘገበበት ዘርፍ መሆኑን አስረድተዋል በውጭ የሚኖሩ የክልሉ ተወላጆችና ሌሎች ባለሃብቶችም በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ወደ ክልሉ እየመጡ መሆኑንም ተናግረዋል በጉባኤው 677 ድምጽ ያላቸውና 404 ድምጽ የሌላቸው ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ግንባር ኢህአዴግ ብአዴን ኦህዴድ ህወሃትና ዴህዴን ተወካዮች እንዲሁም ከተላዩዩ የአውሮፓና አሜሪካ አገሮች የተጋበዙ እንግዶች ተሳትፈዋል የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኢሶህዴፓ 7ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን ያካሄደው ቀደም ባሉት ዓመታት የአገሪቱን ህገ-መንግስት በሚጻረር ሁኔታ የክልሉን ልማትና ሰላም ለማደናቀፍ ራሱን የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ብሎ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴውን ሲሸርብበት በነበረው ቦታ ላይ ነው በዚህ ቦታ የተደረገውም የጸረ-ሰላም ሃይሉ ሙሉ በሙሉ መሰረቱ የተበጣጠሰ መሆኑንና በክልሉ አስተማማኝ ሰላም የሰፈነ መሆኑን ለማሳየት ታስቦ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ,
የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትና የመንደር ማሰባሰብ ተግባር ተጠናክረው እንዲከናወኑ አርብቶአደሮች ጠየቁ , - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 222005 ዋኢማ -የአርብቶ አደሩ የልማት ተጠቃሚነት ዘላቂና ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እና በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የመንደር ማሰባሰብ ተግባር ትኩረት እንዲሰጠው አርብቶ አደሮች ጠየቁ 14ኛው የአርብቶ አደሮች ቀን በዓል ማጠናቀቂያ ፕሮግራም ላይ በተደረገው ውይይት አርብቶ አደሮቹ ባወጡት የአቋም መግለጫ ላይ እኛም አርበቶ አደሮች ለፕሮግራም ምቹ ስኬት በባለቤትነት እና በቁርጠኝነት ለማከናወን ቃል እንገባለን ብለዋል አርብቶ አደሮቹ በአካባቢያቸው የሚታዩ የግጭት መንሰኤዎች በመለየት አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህልን በማሳደግ በአካባቢው አስተማማኝ ሠላም እንዲፈጠር የድርሻቸውን እንደሚወጡም አስገንዝበዋል - ; የአየር ንብረት ለውጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ስጋት እየፈጠረ የመጣ ክስተት በመሆኑ በአርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እንክብካቤና የመሬት አጠቃቀም ላይ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ በአቋም መግለጫው ላይ አበክረው ጠይቀዋል - ; እንዲሁም በአርብቶአደር አካባቢ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የቅርብ ክትትል እየተደረገ በወቅቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ጥረት መደረግ እንዳለበት አስታውቀዋል አርብቶአደሮች ከእንስሳት ሃብትና ከግብርና ምርት ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የገበያ ማዕከላት ማስፋፋት የአገር ውስጥና የውጭ ገበያ ሰንሰለትና ስርዓት እንዲሁም የብድር አገልግሎት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል - ; የአጎራባች ክልሎች ትብብር ለአርብቶ አደሩ ዘላቂ ልማትና ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ባለፉት 14 ዓመታት የትምህርት የጤና የእንስሳት ኃብት የመሠረተ ልማት እና የገበያ ልማት ጥያቄዎች በመንግስት ከፍተኛ ትኩረት በማግኘታቸው ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸውን አርብቶአደሮች ገልፀዋል - ; ከበዓሉ ተሳታፊዎች ጋር የተደረገው ውይይት በአርብቶ አደሩ አከባቢዎች ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን የሚያሣይ አውደ ርዕይ የመስክ ጉብኝትና የመልካም ተሞክሮ ሲነሱ ለነበሩ ጥያቄዎችና የተቀመጡ ግቦች እየተሳካ ስለመሆናቸው አመላካች ናቸው ብለዋል - ; የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በውይይቱ ማጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት አርብቶ አደሮች በአካባቢያቸው እያከናወኑ ያሉት የልማት ተግባራት የሚያስመሰግን ነው ብለዋል የእድገትና ትራንስፎርሜሸን አቅድ ሊሳካ የሚችለው አርብቶ አደሩ በሚፈጥረው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አለመግባባቶችንና ግጭቶችን በመፍታት መሆኑንም ተናግረዋል በመሆኑም በአካባቢያችው በመደራጀትና በመረባረብ ውጤት ማምጣት እንደሚቻልም ጠቁመዋል,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
የዋቤ ሸበሌ ወንዝን በመጠቀም 13ሺ ሄክታር መሬት ለማልማት ጥረት እየተደረገ ነው , - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 142005 ዋኢማ -የሱማሌ ክልል አርብቶ አደሮችን ኑሮ ለመለወጥ የዋቤ ሸበሌ ወንዝን በመጠቀም 13ሺ ሄክታር መሬት ለማልማት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ዲዛይንና ቀጥጥር ቢሮ አስታወቀ የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ጉሌድ አውዓሊ ለዋልታ እንደገለጹት በመስኖ ልማቱ ከ8ሺ በላይ የቤተሰብ መሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ እስካሁን በተደረገውም ጥረት ወንዙን በመጠቀም ከ4ሺ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ምክትል ሃላፊው አስረድተዋል ልማቱ በአከባቢው ለሰፈሩ አርብቶ አደሮች ዘመናዊ አስተራረስና የመስኖ ልማት በማስተማር እንደ ማሽላ ጥጥና ሰሊጥ የመሳሰሉትን በማምረት ራሰቸውን ለማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል ,
ክልሉ 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን አስታወቀ, .._2013_. 0 262 192 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 212005 ዋኢማ - የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አስታወቀ በክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት ኩይሳ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንደር ለተሰባሰቡት አርብቶ አደሮች አስፈላጊውን የማህበራዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ 83 ተቋማት በግንባታ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል የአገልግሎት መስጫ ተቋማቱ ትምህርት ቤቶች ጤና ኬላዎች የባለሙያ መኖሪያ ቤቶች የእህል ወፍጮዎች መጋዘኖች የቀበሌ ጽህፈት ቤቶችና የአርብቶ አደር ማሰልጠኛዎችን እንደሚያካትቱ ሃላፊው ተናግረዋል በክልሉ በሶስት ዞኖች በሚገኙ 12 ወረዳዎች የሚኖረው ግማሽ ሚሊየን አርብቶና ከፊል አርብቶ አደርን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የክልሉ መንግስት እየሰራ መሆኑንም ሃላፊው ተናግረዋል ያለፉት ስርዓታት ለአርብቶ አደሮቹ ምንም ዓይነት ትኩረት እንዳልሰጡ የጠቆሙት አቶ ዳዊት መንግስት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ የአርብቶ አደሮች የልማት ፓኬጅ ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር ከተወሰዱ እርምጃዎች አንዱ በሰፈር ማሰባሰብ መሆኑን የገለጹት አቶ ዳዊት በቀጣይ ዓመታትም በመንደር የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል አርብቶ አደሩ በመንደር ማስፈር ጋር ተያይዞ እየተነሳ ያለው አሉባልታ የአርብቶ አደሩ ህይወት እንዲቀየር በማይፈልጉ ግለሰቦች የመሚነዛ መሆኑን ሃላፊው ጠቁመው ፕሮግራመሙ እየተፈጸመ ያለው ፈቃደኝነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን አስረድተዋል ,
በአፋር ክልል አርብቶአደሩን ለማሰፈር ከ10 ሺ በላይ ሔክታር የአርሻ መሬት ዝግጅት ተጠናቋል, .._2013. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ሐምሌ 82005 ዋኢማ - በአፋር ክልል በዱብቲ ወረዳ ከተንዳሆ ስኳር ልማት ፋብሪካ ጋር በተያያዘ ከቦታቸው ለተነሱ አርብቶአደሮችን ለማስፈር ከ10 ሺ በላይ ሔክታር የአርሻ መሬት ዝግጅቱ እየተፋጠነ ነው የክልሉ አርብቶአደርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል ሜኤስ እንደገለጹት በወረዳው በተመረጡ 10 ቦታዎች የማህበራዊ የልማት አገልግሎት መስጫ ተቋማትን በመገንባት አርብቶ አደሩን በቋሚነት ለማስፈር ዝግጀቱ ተጠናቋል በወረዳው ከተመረጡ የሠፈራ ጣቢያዎች መካከል አራቱ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ አምስት ቦታዎች የእርሻ መሬት ዝግጅትና ተያያዥ ሥራዎች 95 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል በተለይም በሁለቱ የሰፈራ ጣቢያዎች ካለፈው ዓመት ጀምሮ ከ1ሺ 500 በላይ አባወራዎች መሬት ተከፋፍለው ማምረት የጀመሩ መሆኑን ጠቁመዋል የእርሻ መሬትና ተያየዥ ሥራዎች የክልሉ መንግስት ከፌዴራል ውሃ ሃበት ሚኒስቴርና ከስኳር ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ከ2003 ጀምሮ እየተከናወነ ነው ብለዋል ለዚህም በአፋር ውሃ ሥራዎች ኮነስትራክሽን ድርጅት በመከላከያ ኢነጅነሪንግና በአዋሽ ተፋሰስ ድርጅት ተቋራጭነት እየተሠራ መሆኑን አመልክተዋል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እስማኤል አሊሴሮ በወረዳው እየተሠራ ያለውን የመንደር ማሰባሰብ ጣቢያዎች ተዘዋውረው ከጎበኙ በኋላ የክልሉን አርብቶአደር ችግር በዘላቂነተ ለመቅረፍ ህብረተሰቡ ወደ ዘመናዊ አርብቶአደርነት ለማሸጋገር በወረዳው እየተሠራ ያለው መንደር ማሰበሰብ ወሳኝ ነው ብለዋል ሠፈራው በተለይም በህብረተሰቡ ውስጥ ከፍተኛ የሥራ ጫና የነበረባቸውን የሴቶች ማሀበራዊ ችግሮች ከማቃለሉም በላይ የመሬት ማከፋፈሉ ሒደት የሴቶችን የንብረት ባለቤትነት መብት ባረጋገጠ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ በክልሉ ከ2003 ዓም ጀምሮ በተመረጡ ዘጠኝ ወረዳዎች በተከናወነው የመንደር ማባሰብ ፕሮግራም ከ8 ሺ በላይ አርብቶአደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው ታወቋል,
ሶስተኛው ምዕራፍ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ነው, - ; .._2014_2. 0 201 179 ; 5; አዲስ አበባ ታህሳስ 14 2007 ዋኢማ - ሶስተኛው ምዕራፍ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት በ210 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ - ; የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ወርቁ ለዋልታ እንደገለጹት ከባለፈው በጀት ዓመት አጋማሽ ጀምሮ ፕሮጄክቱ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው በሶማሌ አፋርኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ነው - ; ፕሮጀክቱ ባጠቃላይ በ113 ወረዳዎች ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን በሶማሌ ክልል 54 ወረዳዎችበአፋር 23 ወረዳዎች በኦሮሚያ 26 ወረዳዎችና በደቡብ ደግሞ 10 ወረዳዎች ውስጥ ነዋሪ የሆኑ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል - ; እንደ አቶ አበበ ማብራሪያ ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡን ችግሮች መሠረት ያደረጉ የልማት ሥራዎች የገጠር ኑሮ ማሻሻያዎች የአቅም ግንባታና የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ያተኮረ ነው - ; ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከተመደበው 210 ነጥብ 2 የአሜሪካን ዶላር ውስጥ የዓለም አቀፉ የልማት ማህበር 110 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም የዓለም የግብርና ልማት ፈንድ ደግሞ 85 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ቀሪው በክልሎችና በተጠቃሚ ማህብረሰብ የሚሸፈን መሆኑን አቶ አበበ ተናግረዋል ,
የአርብቶ አደሩ በመንደር መሰባሰብ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ አስችሎታል, - ; .._2015_26. 0 261 145 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 182007 ዋኢማ - አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰቡ ፕሮግራም በስኬት ለማጠናቀቅ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ሃይለ ማርያም ደሳለኝ አሳሳቡ - ; 15ኛ የአርብቶ አደሮች ቀን በዓል የአርብቶ አደሩ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለህዳሴያችን በሚል መሪ ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትላንት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ተከብሯል - ; ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማያም ደሳለኝ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር አርብቶ አደሩን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተደረጉት ጥረቶች ውጤታማ ሰራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል - ; መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢዎች የሚከተለው የልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ የዉሃና እንስስት ሃብትን መሰረት በማድረግ በየክልሎቹ አቅም የሚሰሩት እንደተጠበቁ ሆነው በፌዴራልና በአጎራባች ክልሎች ትብብር የሚከናወኑ የተፋሰስ ልማትና በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመንደር ማሰባሰብ ላይ መሆኑን ተናግረዋል - ; ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት በአፋርና በሱማሌ ክልሎች የምዕተ አመቱን የልማት ግብና የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ግቦችን የሚያሳኩ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል - ; በተጨማሪም አርብቶ አደር በሚገኝባቸው የደቡብና የኦሮሚያ አካባቢዎች ጭምር ውጤታማ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል - ; ይሁንና አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰብ ተግባር ያላስደሰታቸው አንዳንድ የወስጥና የውጭ ሃይሎች ከመንግስት በላይ ለህዝብ የተቆረቆሩ በመምሰል ልማቱን ለማደናቀፍ ቢጥሩም እናንተ አርብቶ አደሮቹ በሰራችሁት ስራና በተገኘው ውጤት ተራ አሉባልታና መሰረተ ቢስ መሆኑን ለማረጋገጥ ችላችዋል ብለዋል - ; የመንደር ማስባሰቡ ፕሮግራም ተጠናክሮ በመቀጠል አርብቶ አደሩ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ እንዳስቻለውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል - ; በአርብቶ አደር አካባቢ የተመዘገቡት የልማት ዉጤቶችና ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት በተለይ አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰቡ ፕሮግራም በስኬት ለማጠናቀቅ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አሳስበዋል - ; የፌዴራል መንግስት አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በማካሄድ የአርብቶ አደሮች አካባቢን ልማት እያቀላጠፈ ይገኛል ብለዋል የአርብቶ አደር አከካባቢዎች መዳረሻና ከአጎራባች ክልሎች ጋር ሊያስተሳስሩ የሚችሉ የመንገድ የስልክ የኤሌክትሪክና አዉሮፕላን ማረፊያ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውንም ገለጸዋል - ; በልማቱም አካባቢዎቹ የኢንቨስትመንትና ቱሪስት መዳረሻ መሆናቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም ሀገሪቱ የእኩል ተጠቃሚነት መርህ የምትከተልና ሁሉም ህዝቦች የህዳሴዉ ጉዞ አካል መሆናቸውን እንደሚያሳይ አብራርተዋል - ; የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እስማኤል ኢሊሴሮ በበኩላቸው መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዋና የኑሮ መሰረቱ በሆነው የእንስሳት ሃብቱ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆን በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል - ; የተጀመረዉ የተፋሰስ ልማትና በመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረግ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ምቹ ሁኔታ የፈጠረለት መሆኑን ተናግረዋል - ; ባለፉት 3 አመታት ዉስጥ በክልሉ16 ሺህ አርብቶ አደሮች በመንደር ተሰባሰቡ የልማቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጠይነትም ህብረተሰቡን በመንደር የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚጠጥል ገልጸዋል ባለፉት ሁለት አስርተ አመታት የአፋር ክልል ከምንም ተነስቶ የንጽሁ መጠጥ ውሃ ትምህርት የጤና አገልግሎቶች ተደራሽ በመሆን ላይ ይገኛል - ; በግብርና መስክም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስተናችን ለማረጋገጥ የሚያስችለው አቅም በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል - ; የፌደራል መንግስትና የአጎራባች ክልሎች የልማት ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጠልም ጠይቀዋል - ; በስራቸው የተሻለ ውጤት አስመዝግበው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚዳሊያ ሽልማት ከወሰዱት አርብቶ አደሮች መካከል ከኦሮሚያ ክልል የመጡት አቶ ኢብራሂም አሊ ይገኙበታል - ; ሽልማቱ ለበለጠ የስራ ውጤት መነሳሳት እንደፈጠረላቸውና በቆይታቸውም ከተለያዩ ክልሎች ከመጡ አርብቶ አደሮች ጠቃሚ ልምድ ማግኘታቸውን እኚሁ ተሸላሚ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል - ; ከአፋር ክልል ተሸላሚ የሆኑት አርብቶ አደር አቶ ሃመዱ ሁመድ በበኩላቸው ያገኙት ሽልማት ለቀጣይ የልማት ሰራቸው ማደግ እንደሚያበረታታቸው ጠቁመው ሌሎችንም ለዉጤት ለማብቃት እንደሚጥሩ ተናግረዋል በበዓሉ ላይ የፌዴራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን በውጤታማነታቸው ከየክልሉ የተመረጡ 229 አርብቶ አደሮች ሜዳሊያ ተሸልመዋል ኢዜአ,
በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከሶስት መቶ ሺሕ በላይ አርብቶ አደሮች በመንደር ተሰባስበዋል, - ; .._2015_15. 0 262 198 ; 5; አዲስ አበባ ግንቦት 62007ዋኢማ - በአምስት መቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከሶስት መቶ ሺሕ አርበቶና ከፊል አርብቶ አደር ቤተሰቦች በመንደር መሰባሰባቸውን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ ባለፉት አራት ዓመት ከዘጠኝ ወራት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመናት 304 ሺሕ 541 አባውራና እማውራ አርብቶ አደሮችንና ከፊል አርብቶ አደሮችን በመንደር በማሰባሰብ የማህበራዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ወርቁ ለዋልታ እንደገለጹት በአምስት ዓመቱ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በአራቱ የታዳጊ ክልሎች በሆኑት አፋርሶማሌ ጋምቤላና ቤኒሻንጉል ክልሎች 360 ሺሕ አርብቶ አደሮችን በመንደር ለማሰባሰብ ታቅዶ ባለፉት አራት ዓመት ከዘጠኝ ወራት 304 ሺሕ 541 አርብቶአደሮችን በመንደር ለማሰባሰብ ተችሏል ብለዋል ከ2003 ዓም ጀምሮ በተካሄደው የመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም አርብቶ አደሩን በልማት ማዕከላት በማደራጀትና የአስተዳደር መዋቅርና የአቅም ግንባታን በማከናወን አርብቶ አደሩን ግብርናን እንዲላመድ በመደረጉን ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት የተቀየረ ሲሆን የገበያ ትስስር እየተፈጠረለት በመሆኑ ተጠቃሚነቱ ማደጉን አቶ አበበ አያይዘው ገልጸዋል በተለይ 11 ዓመት ሲከናወን በቆየው የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮግራም አርብቶ አደሩ ውይይት እንደሚያደርግ የጠቆሙት አቶ አበበ በአካባቢው የሚያስፈልገውን የልማት አይነት ጭምር በመምረጥ የተለያዩ የልማት ዘርፎች ተጠቃሚ መሆን ችሏል ብለዋል ከ24 ዓመታት በፊት በአራቱን ታዳጊ ክልሎች ምንም አይነት የመሠረተልማት እንዳልነበረ የጠቀሱት አቶ አበበ በአሁኑ ወቅት ከባዶ በመነሳት ክልሎቹ በማህበራዊ አገልገሎት ሽፋን ብቻ 80 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል በክልሎቹ ቀደም ሲል ይታይ የነበረውን ተከታታይ ግጭቶች ሙሉ ለሙሉ ጠፍተው በክልሎቹ ዘላቂ ልማት መረጋጋጡ ትልቅ እመርታ መሆኑን የገለጹት አቶ አበበ በአገሪቱ ባለፉት 24 ዓመታት ተግባራዊ የሆነው የዘላቂ ሰላም ማምጣት ፖሊሲ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን በቀሩት ሦስት ወራት ውስጥ በመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም የማሰባሰቡትን አርብቶ አደሮች 95 በመቶ ለማድረስ ጥረት እንደሚደረግ ዋልታ ኢንፎሜሽን ማዕከል ዘግቧል ,
የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር ውጤታማ እየሆነ ነው, - ; .._2014. 0 272 203 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 12 2006 ዋኢማ - በአራት ክልሎች ተግባራዊ የተደረገው የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር እስከአሁን ያለው አፈጻጸም ስኬታማ እንደነበር የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ገለጸ - ; የመርሐ ግበሩ ሁለተኛ ምዕራፍ አጠቃላይ አፈጻጸም የሚገመግም ጉባኤ በአዳማ ሲካሄድ በመርሐ ግብሩ 2ኛ ምዕራፍ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል - ; የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው በጉባኤው ላይ በመርሐ ግብሩ ሁለተኛው ምዕራፍ የበርካታ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ሕይወት መቀየር መቻሉን ተናግረዋል - ; በጉባኤው ላይ የመርሐ ግብሩ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የመርሐ ግበሩ ተጠባባቂ አስተባባሪ አቶ ሰይድ ይመር በሁለተኛው ምዕራፍ የትግበራ ወቅት ለማከናወን ከታቀደው ውስጥ 99 በመቶውን መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል - ; የአርሶ አደሩን የኑሩ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የትምህርት የሰው እና የእንስሳት ጤና የመጠጥ ውሃ እና የአነስተኛ መስኖ ብሎም የማሕበረሰብ መንገድ ሥራዎች በመርሐ ግብሩ የተከናወኑ ናቸው - ; ይህም በሚሊየን ለሚቆጠሩ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮች የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ በጉባኤው ላይ ተነስቷል - ; በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ከክልሎች የመጡ የሥራ ኃላፊዎች ሁለተኛው ምዕራፍ መርሐ ግበሩ ሴቶችን ማሳተፉ ማህበራትን በማደራጀት የህብረተሰቡን ተሳትፎ ያማከለ መሆኑ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል - ; መርሀ ግብሩ በአራቱ ክልሎች በሁለተኛው ምዕራፍ ከመንግስትና ከተለያዩ ለጋሽ አካለት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተሰራ ሲሆን ከ139 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጭ ተደርጓል - ; የአርብቶ አደር መርሀ ግብሩ በአፋር በኢትዮጵያ ሶማሌ በኦሮምያ እና በደቡብ ክልሎች የሚገኙ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ኑሮ ማሻሻል የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን መሰረት አድርጎ የሚሰራው ነው - ; የ15 ዓመታት የቆይታ ጊዜ እንዲኖረው ተደርጎ የተቀረጸው መርሀ ግብሩ በየአምስት አመት ጊዜ ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን ሁለት ምዕራፎችን ተሻግሯል ,
የአፍሪካ ግብርናን ማሳደግ ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጀመረ , - ; .._2014 . 0 262 196 ; 5; አዲስ አበባ 26 ነሐሴ 2006 ዋኢማ - የአፍሪካ የግብርና ዘርፍን ለማሳደግ አለም አቀፍ ጉባኤ ዛሬ በሸራተን አዲስ ተጀምሯል - ; የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት መድረክ የተሰኘው ይህ ጉባኤ የአፍሪካን አርሶአደሮች ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና ችግርን በማቃለል ዙሪያ ትኩረቱን አድርጎ ይመክራል - ; ጉባኤው አፍሪካ እ.ኤ.አ በ2025 የግብርና ምርትን በእጥፍ ለማሳደግና በአንፃሩ ድህነትን በግማሽ ለመቀነስ የምታደረገው ጥረት አካልም ነው - ; በጉባኤው እንደተመለከው በአፍሪካ ከሚገኙ አገራት አስር ያህሉ ብቻ ናቸው ከአጠቃላይ ዓመታዊ በጀታቸው 10 በመቶ ያህሉን ለግብርና የመደቡት - ; ይህም አፍሪካ በሚፈለገው ደረጃ የምግብ እጥረት ተጋላጭነትን እንድትቀንስ አላስቻላትም ተብሏል - ; የአሁኑ አለም አቀፍ የምክክር መድረክም የአፍሪካ ገበሬዎች ድርቅን የሚቋቅሙ ሰብሎችንና የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ ይመክራል - ; ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ከ1000 በላይ የሚሆኑ የአለማችን ታላላቅ የግብርና ኩባንያዎች ስራ አስኪያጆች የገበሬዎች ማህበራት እንዲሁም ታላላቅ ጥናት አቅራቢዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ,
የአርብቶ አደሩ በመንደር መሰባሰብ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ አስችሎታል, - ; .._2015_26. 0 261 145 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 182007 ዋኢማ - አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰቡ ፕሮግራም በስኬት ለማጠናቀቅ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ሃይለ ማርያም ደሳለኝ አሳሳቡ - ; 15ኛ የአርብቶ አደሮች ቀን በዓል የአርብቶ አደሩ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለህዳሴያችን በሚል መሪ ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትላንት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ተከብሯል - ; ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማያም ደሳለኝ በበዓሉ ላይ ባደረጉት ንግግር አርብቶ አደሩን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተደረጉት ጥረቶች ውጤታማ ሰራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል - ; መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢዎች የሚከተለው የልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ የዉሃና እንስስት ሃብትን መሰረት በማድረግ በየክልሎቹ አቅም የሚሰሩት እንደተጠበቁ ሆነው በፌዴራልና በአጎራባች ክልሎች ትብብር የሚከናወኑ የተፋሰስ ልማትና በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመንደር ማሰባሰብ ላይ መሆኑን ተናግረዋል - ; ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት በአፋርና በሱማሌ ክልሎች የምዕተ አመቱን የልማት ግብና የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ግቦችን የሚያሳኩ ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል - ; በተጨማሪም አርብቶ አደር በሚገኝባቸው የደቡብና የኦሮሚያ አካባቢዎች ጭምር ውጤታማ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል - ; ይሁንና አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰብ ተግባር ያላስደሰታቸው አንዳንድ የወስጥና የውጭ ሃይሎች ከመንግስት በላይ ለህዝብ የተቆረቆሩ በመምሰል ልማቱን ለማደናቀፍ ቢጥሩም እናንተ አርብቶ አደሮቹ በሰራችሁት ስራና በተገኘው ውጤት ተራ አሉባልታና መሰረተ ቢስ መሆኑን ለማረጋገጥ ችላችዋል ብለዋል - ; የመንደር ማስባሰቡ ፕሮግራም ተጠናክሮ በመቀጠል አርብቶ አደሩ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ እንዳስቻለውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል - ; በአርብቶ አደር አካባቢ የተመዘገቡት የልማት ዉጤቶችና ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት በተለይ አርብቶ አደሩን በመንደር የማሰባሰቡ ፕሮግራም በስኬት ለማጠናቀቅ ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባም አሳስበዋል - ; የፌዴራል መንግስት አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በማካሄድ የአርብቶ አደሮች አካባቢን ልማት እያቀላጠፈ ይገኛል ብለዋል የአርብቶ አደር አከካባቢዎች መዳረሻና ከአጎራባች ክልሎች ጋር ሊያስተሳስሩ የሚችሉ የመንገድ የስልክ የኤሌክትሪክና አዉሮፕላን ማረፊያ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውንም ገለጸዋል - ; በልማቱም አካባቢዎቹ የኢንቨስትመንትና ቱሪስት መዳረሻ መሆናቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም ሀገሪቱ የእኩል ተጠቃሚነት መርህ የምትከተልና ሁሉም ህዝቦች የህዳሴዉ ጉዞ አካል መሆናቸውን እንደሚያሳይ አብራርተዋል - ; የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እስማኤል ኢሊሴሮ በበኩላቸው መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዋና የኑሮ መሰረቱ በሆነው የእንስሳት ሃብቱ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆን በርካታ ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል - ; የተጀመረዉ የተፋሰስ ልማትና በመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረግ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ምቹ ሁኔታ የፈጠረለት መሆኑን ተናግረዋል - ; ባለፉት 3 አመታት ዉስጥ በክልሉ16 ሺህ አርብቶ አደሮች በመንደር ተሰባሰቡ የልማቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጠይነትም ህብረተሰቡን በመንደር የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚጠጥል ገልጸዋል ባለፉት ሁለት አስርተ አመታት የአፋር ክልል ከምንም ተነስቶ የንጽሁ መጠጥ ውሃ ትምህርት የጤና አገልግሎቶች ተደራሽ በመሆን ላይ ይገኛል - ; በግብርና መስክም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስተናችን ለማረጋገጥ የሚያስችለው አቅም በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል - ; የፌደራል መንግስትና የአጎራባች ክልሎች የልማት ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጠልም ጠይቀዋል - ; በስራቸው የተሻለ ውጤት አስመዝግበው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚዳሊያ ሽልማት ከወሰዱት አርብቶ አደሮች መካከል ከኦሮሚያ ክልል የመጡት አቶ ኢብራሂም አሊ ይገኙበታል - ; ሽልማቱ ለበለጠ የስራ ውጤት መነሳሳት እንደፈጠረላቸውና በቆይታቸውም ከተለያዩ ክልሎች ከመጡ አርብቶ አደሮች ጠቃሚ ልምድ ማግኘታቸውን እኚሁ ተሸላሚ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል - ; ከአፋር ክልል ተሸላሚ የሆኑት አርብቶ አደር አቶ ሃመዱ ሁመድ በበኩላቸው ያገኙት ሽልማት ለቀጣይ የልማት ሰራቸው ማደግ እንደሚያበረታታቸው ጠቁመው ሌሎችንም ለዉጤት ለማብቃት እንደሚጥሩ ተናግረዋል በበዓሉ ላይ የፌዴራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን በውጤታማነታቸው ከየክልሉ የተመረጡ 229 አርብቶ አደሮች ሜዳሊያ ተሸልመዋል ኢዜአ,
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በድርቅ ጉዳት ከደረሰባቸው አርብቶ አደሮች ጋር ተወያዩ , - ; ..1_2015_16. 0 261 195 ; 5; አዲስ አበባ ጥቅምት 04 2008 ዋኢማ- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በአፋር ክልል በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች አንዱ የሆነውን የአሚባራ ወረዳን ተዘዋውረው ጎበኙ - ; ጠቅላይ ሚኒስትሩ በድርቁ ጉዳት ከደረሰባቸው አርብቶ አደሮች ጋርም ዛሬ ወይይት አካሂደዋል - ; በዚህም መንግስት በድርቅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል - ; በድርቁ ምክንያት በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት ባይኖርም የኑሯቸዉ መሠረት የሆኑት ከብቶቻቸው በመሞታቸው ከእንስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ ያገኙት የነበረው ገቢና ምግብ ቀንሷል በተለይ ህፃናትና እናቶች እንዳይጎዱ ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል - ; ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ከነዋሪዎቹ ለተነሱ ጥያቄዎች በሠጡት ምላሽ ድርቁ በህብረተሰቡ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል የሚያደረጉ ልዩ ልዩ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል - ; በተለይም በእናቶችና ህጻናት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከእንስሳት ተዋፅኦ የሚያገኙትን ምግብ የሚተኩ የአልሚ ምግብ ድጋፍ ይደረጋል ነው ያሉት - ; ነዋሪዎቹ ፕሮሶፒስ የተባለው መጤ አረም የእርሻና ግጦሽ መሬቶችን በመውረር በእንስሳት ምርትና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ መፍትሄ እንዲፈለግለት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል - ; መጤ አረሙን በቴክኖሎጂ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመቀየር ስራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ኃይለማርያም የበሰቃ ውሃ የሚያደርሰውን ጉዳት መቀነስ የሚቻልበትና ከተቻለም ለልማት የሚውልበትን ሁኔታ ለመፍጠር መንግስት በአለም አቀፍ ድርጅት ጥናት እየስጠና መሆኑን ገልጸዋል - ; የሃላይደቤ ጥልቅ የከርሰ- ምደር ውሃን በቅርቡ ጥቅም ላይ በማዋል የአካባቢው ህብረተሰብ ለእርሻ ስራ እንዲጠቀምበትና አካባቢዉን ወደ ለምነት ለመቀየር መንግስት ቁርጠኛ መሆኑንም ተናግረዋል ኤፍ. ቢ. ሲ,
በአፋር የአርብቶ-አደሩን ኑሮ ለመለወጥ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል -ርእሰመስተዳድሩ, .._2012. 0 260 195 ; 5; - ; አዲስ አበባ ጥቅምት 302005 ዋኢማ - በአፋር ብሄራዊ ክልል የሚገኘዉን የአርብቶ-አደር ኑሮ ለማሻሻል በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አካላት በቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አስገነዘቡ በክልሉ በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሳተፉበትና በ2005 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ የሚወያይ ሰብሰባ በሰመራ ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እስማኤል ዓሊሴሮ ስብሰባዉን ሲከፍቱ እንደተናገሩት ታላቁ መሪያችን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻልና ህይወቱን ለመቀየር ያስቀመጡትን ራእይ ከዳር በማድረስ ረገድ ሁሉም በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀስ ይገባል ለዘመናት የከብትን ጭራ ተከትሎ ውሃና ሳር ፍለጋ ከቦታ ቦታ ሲንከራተት የኖረዉ አርብቶ-አደር ህብረተሰብ በመንደር ተሰባስቦ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ታላቁ መሪያችን የነበራቸዉን ጽኑ ፍላጎትና እምነት ለማሳካት የእያንዳንዱ የክልሉ ህብረተሰብ ሃላፊነትና ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል የአርብቶ-አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመቀየር ብሎም ወደ ዘመናዊ አርብቶ-አደርነትና ግብርና እንዲሸጋገር በአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የተያዘዉ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አስገንዝበዋል በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በትምህርት በግብርናና ገጠር ልማት በጤናና ውሃ ሃብት ልማት በመንገድና በሌሎች የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ የተቀመጠዉን አቅጣጫ በመፈጸም የአርብቶ አደሩን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሌት ተቀን ተግቶ መስራት እንደሚገባም አቶ እስማኤል ተናግረዋል ከአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎሜሸን እቅድ አንፃር በያዝነው የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት የተመለከተ ሪፖርት በክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ቀርቦ ዉይይት ተካሄዶበታል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስብሰባው ላይ የ32ቱም የወረዳ መስተዳድር አመራሮች የአምስቱም የዞን መስተዳድር አመራሮችና በክልሉ የሁሉም የሴክተር እና ቢሮ ሃላፊዎችና የስራ ሂደት ባለቤቶች ተሳታፊ ሆነዋል ,
በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው, - ; .._2012. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ህዳር 42005 ዋኢማ - በአገሪቱ አርብቶ አደር አካባቢዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የልማት ፕሮጀክቶች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትሩ አስታወቁ - ; ሚኒስትሩ ዶክተር ሺፈራው ተክለማርያም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአርብቶ አደሮች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የ2005 በጀት ዓመትን ዕቅድ በገመገመበት ወቅት እንዳስረዱት ፕሮጀክቶቹ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ በሚኖርባቸው አራት ክልሎች እየተከናወኑ ነው በዚህም በክልሎቹ ተመጣጣኝ ልማት ለማምጣት በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም በማካሄድየተፋሰስ ልማት በማከናወንየወረዳዎችን አቅም በመገንባትና በሌሎችም መስኮች ላይ ያተኮሩ ፕሮጀክቶች በመተግበር ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል በያዝነው ዓመት 98ሺህ አርብቶ አደሮችን በመንደሮች ለማሰባሰብ መታቀዱን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ200ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች በመንደር መሰባሰባቸውንም አስታውሰዋል እንደ ዶክተር ሺፈራው ገለጻ በበጀት ዓመቱ በሶማሌበአፋርበኦሮሚያና በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚከናወኑት ፕሮጀክቶች የአርብቶ አደሮችን ኑሮ በማሻሻልና ለአደጋ ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው የማህበረሰብ ልማትየለውጥ ሠራዊት ግንባታ የግጭት መከላከልና አፈታት ሥራዎች በበጀት ዓመቱ የሚከናወኑ ሌሎች ተግባራት መሆናቸውን አስረድተዋል የምክር ቤቱ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ልጅዓለም ወልዴ በበኩላቸው ሚኒስቴሩ በሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነትበአካባቢ ጥበቃበኤች አይ ቪኤድስ መከላከል ረገድ ተጨማሪ ሥራዎችን ለማከናወን ዕቅድ ማውጣት እንዳለበት አሳስበዋል በተለይም በግጭት መከላከልና አፈታት ረገድ የሚታየውን የአመለካከት ክፍተት ለመሙላት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጭ ተግባራት መከናወን እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የምክር ቤቱን የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬትን ጠቅሶ የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው ,
በፕሮጀክቱ አካባቢ ለሚኖሩ አርብቶ አደሮች አገልግሎት መስጫና የመስኖ ልማት ተቋማት እየተገነቡላቸው ነው , - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አባባ ጥር 62005 ዋኢማ - በደቡብ ኦሞ ዞን በሚገነባው የኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት አካባቢ የሚኖሩ አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አገልግሎት መስጫና የመስኖ ልማት ተቋማት እየተገነቡ መሆኑን የስኳር ኮርፖሬሽን አስታወቀ በፕሮጀክቱ አካባቢ ከሚኖሩ አርብቶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በልማቱ ጥቅሞች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተካሄደው የምክክር መድረክ የማጠቃለያ ውይይት ዛሬ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል የኮርፖሬሽኑ የሕዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳመነ ዳሮታ በዚሁ ውቅት እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በአብዛኛው በሚካሄድበት በሳላማጎ ወረዳ በመንደሮች ለተሰባሰቡ 1ሺህ 430 የቦዲ ብሄረሰብ አባወራ አርብቶ አደሮች አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ግንባታ እየተካሄደ ነው እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ በሦስት መንደሮች ለተሰባሰቡት ለነዚሁ አርብቶ አደሮች ሦስት በየደረጃው የሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ሁለት ጤና ኬላዎች ተገንብተዋል በተጨማሪም ሁለት የእህል ወፍጮዎችሦስት መጋዘኖችና አንድ የእንስሳት ጤና ኬላ ተሰርተዋል እንዲሁም የቀበሌ ጽህፈት ቤትና የፖሊስ ጣቢያ ግንባታም መካሄዱን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል በፕሮጀክቱ ድጋፍ እየተካሄዱ ከሚገኙት ሥራዎች መካከል በኦሞ ወንዝ ላይ የሚገነባው ጊዜያዊ የውሃ መቀልበሻ ኮፈር ዳም ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም አስታውቀዋል ለመንደር አንድ አንድ መለስተኛ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩንና ለሌሎቹ ሁለት መንደሮች ደግሞ አንድ መለስተኛ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ መጀመሩን አቶ ዳመነ አመልክተዋል ለእርሻ ሥራ የሚሆን ከ4ሺህ500 ሄክታር በላይ መሬት ምንጣሮና ድልዳሎ ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑን ገልጸውበመስኖ የሚለማ ሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ለአርብቶ አደሮቹ በመከፋፈል ላይ እንደሚገኝም አቶ ዳመነ ተናግረዋል ስድስት ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬት የሚያለማው የ24 ኪሎ ሜትር ዋና የመስኖ ቦይ ግንባታም በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል በመንገድ ዘርፍ የ42 ኪሎ ሜትር መንገድ ከፈታና የ17ነጥብ3 ኪሎ ሜትር መንገድ ጠጠር ማልበስ ተግባራት መከናወናቸውንና ልማቱ በሚደርስባቸው የሙርሲ ጉራ መንደሮች በዚህ ዓመት ከሚሰራው መንገድ 12ነጥብ6 ኪሎ ሜትር ያህሉ መጠናቀቁን አብራርተዋል ፕሮጀክቱ ለችግርና ለረሃብ በሚያጋልጥ ሁኔታ ተበታትኖ የሚኖረውን አርብቶ አደር የመስኖ ልማትን በሚካሄድበት አካባቢ በማስፈር ቋሚና የተረጋጋ ሕይወት ለመምራት እንደሚያስችለውም አስረድተዋል የምክክር መድረኩ ዓላማም የአካባቢው አርብቶ አደሮችና ባለድርሻ አካላት በፕሮጀክቱ ላይ በቂ ግንዛቤ አግኝተው በባለቤትነትና በተጠቃሚነት ስሜት እንዲሳተፉ ለማድረግ መዘጋጀቱን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል ከታኅሣሥ 22 ቀን 2005 ጀምሮ የተካሄደው መድረክ ማጠቃለያ በሆነው ውይይት ላይ በልማቱ አካባቢ የሚገኙ አርብቶ አደሮችየብሄረሰቦች ተወካዮችየጎሣ መሪዎችየከተማ ነዋሪዎችበየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደር አካላት ተሳትፈዋል እንዲሁም የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተካፍለዋል ፕሮጀክቱ በ175ሺህ ሄክታር የሸንኮራ አገዳ በማልማት እያንዳንዳቸው በቀን 12ሺህ ቶን አገዳ የሚፈጩ ሦስት ፋብሪካዎችና እያንዳንዳቸው በቀን 24ሺህ ቶን አገዳ የሚፈጩ ሁለት ፋብሪካዎች እንደሚኖሩት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል እንደ ኢዜአ ዘገባ የኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት እየተገነባ ያለው በደቡብ ብሄሮችብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ውስጥ ነው ,
የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትና የመንደር ማሰባሰብ ተግባር ተጠናክረው እንዲከናወኑ አርብቶአደሮች ጠየቁ , - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 222005 ዋኢማ -የአርብቶ አደሩ የልማት ተጠቃሚነት ዘላቂና ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እና በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የመንደር ማሰባሰብ ተግባር ትኩረት እንዲሰጠው አርብቶ አደሮች ጠየቁ 14ኛው የአርብቶ አደሮች ቀን በዓል ማጠናቀቂያ ፕሮግራም ላይ በተደረገው ውይይት አርብቶ አደሮቹ ባወጡት የአቋም መግለጫ ላይ እኛም አርበቶ አደሮች ለፕሮግራም ምቹ ስኬት በባለቤትነት እና በቁርጠኝነት ለማከናወን ቃል እንገባለን ብለዋል አርብቶ አደሮቹ በአካባቢያቸው የሚታዩ የግጭት መንሰኤዎች በመለየት አለመግባባቶችን በውይይት የመፍታት ባህልን በማሳደግ በአካባቢው አስተማማኝ ሠላም እንዲፈጠር የድርሻቸውን እንደሚወጡም አስገንዝበዋል - ; የአየር ንብረት ለውጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ስጋት እየፈጠረ የመጣ ክስተት በመሆኑ በአርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እንክብካቤና የመሬት አጠቃቀም ላይ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ በአቋም መግለጫው ላይ አበክረው ጠይቀዋል - ; እንዲሁም በአርብቶአደር አካባቢ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የቅርብ ክትትል እየተደረገ በወቅቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ጥረት መደረግ እንዳለበት አስታውቀዋል አርብቶአደሮች ከእንስሳት ሃብትና ከግብርና ምርት ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የገበያ ማዕከላት ማስፋፋት የአገር ውስጥና የውጭ ገበያ ሰንሰለትና ስርዓት እንዲሁም የብድር አገልግሎት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል - ; የአጎራባች ክልሎች ትብብር ለአርብቶ አደሩ ዘላቂ ልማትና ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ባለፉት 14 ዓመታት የትምህርት የጤና የእንስሳት ኃብት የመሠረተ ልማት እና የገበያ ልማት ጥያቄዎች በመንግስት ከፍተኛ ትኩረት በማግኘታቸው ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸውን አርብቶአደሮች ገልፀዋል - ; ከበዓሉ ተሳታፊዎች ጋር የተደረገው ውይይት በአርብቶ አደሩ አከባቢዎች ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን የሚያሣይ አውደ ርዕይ የመስክ ጉብኝትና የመልካም ተሞክሮ ሲነሱ ለነበሩ ጥያቄዎችና የተቀመጡ ግቦች እየተሳካ ስለመሆናቸው አመላካች ናቸው ብለዋል - ; የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በውይይቱ ማጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት አርብቶ አደሮች በአካባቢያቸው እያከናወኑ ያሉት የልማት ተግባራት የሚያስመሰግን ነው ብለዋል የእድገትና ትራንስፎርሜሸን አቅድ ሊሳካ የሚችለው አርብቶ አደሩ በሚፈጥረው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አለመግባባቶችንና ግጭቶችን በመፍታት መሆኑንም ተናግረዋል በመሆኑም በአካባቢያችው በመደራጀትና በመረባረብ ውጤት ማምጣት እንደሚቻልም ጠቁመዋል,
በአፋር ክልል አርብቶአደሩን ለማሰፈር ከ10 ሺ በላይ ሔክታር የአርሻ መሬት ዝግጅት ተጠናቋል, .._2013. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ሐምሌ 82005 ዋኢማ - በአፋር ክልል በዱብቲ ወረዳ ከተንዳሆ ስኳር ልማት ፋብሪካ ጋር በተያያዘ ከቦታቸው ለተነሱ አርብቶአደሮችን ለማስፈር ከ10 ሺ በላይ ሔክታር የአርሻ መሬት ዝግጅቱ እየተፋጠነ ነው የክልሉ አርብቶአደርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል ሜኤስ እንደገለጹት በወረዳው በተመረጡ 10 ቦታዎች የማህበራዊ የልማት አገልግሎት መስጫ ተቋማትን በመገንባት አርብቶ አደሩን በቋሚነት ለማስፈር ዝግጀቱ ተጠናቋል በወረዳው ከተመረጡ የሠፈራ ጣቢያዎች መካከል አራቱ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ አምስት ቦታዎች የእርሻ መሬት ዝግጅትና ተያያዥ ሥራዎች 95 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል በተለይም በሁለቱ የሰፈራ ጣቢያዎች ካለፈው ዓመት ጀምሮ ከ1ሺ 500 በላይ አባወራዎች መሬት ተከፋፍለው ማምረት የጀመሩ መሆኑን ጠቁመዋል የእርሻ መሬትና ተያየዥ ሥራዎች የክልሉ መንግስት ከፌዴራል ውሃ ሃበት ሚኒስቴርና ከስኳር ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ከ2003 ጀምሮ እየተከናወነ ነው ብለዋል ለዚህም በአፋር ውሃ ሥራዎች ኮነስትራክሽን ድርጅት በመከላከያ ኢነጅነሪንግና በአዋሽ ተፋሰስ ድርጅት ተቋራጭነት እየተሠራ መሆኑን አመልክተዋል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እስማኤል አሊሴሮ በወረዳው እየተሠራ ያለውን የመንደር ማሰባሰብ ጣቢያዎች ተዘዋውረው ከጎበኙ በኋላ የክልሉን አርብቶአደር ችግር በዘላቂነተ ለመቅረፍ ህብረተሰቡ ወደ ዘመናዊ አርብቶአደርነት ለማሸጋገር በወረዳው እየተሠራ ያለው መንደር ማሰበሰብ ወሳኝ ነው ብለዋል ሠፈራው በተለይም በህብረተሰቡ ውስጥ ከፍተኛ የሥራ ጫና የነበረባቸውን የሴቶች ማሀበራዊ ችግሮች ከማቃለሉም በላይ የመሬት ማከፋፈሉ ሒደት የሴቶችን የንብረት ባለቤትነት መብት ባረጋገጠ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ በክልሉ ከ2003 ዓም ጀምሮ በተመረጡ ዘጠኝ ወረዳዎች በተከናወነው የመንደር ማባሰብ ፕሮግራም ከ8 ሺ በላይ አርብቶአደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው ታወቋል,
በመንደር የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮች የተረጋጋና ከግጭት ነፃ ህይወት እየመሩ ነው , ሐዋሳ ሚያዝያ32006 ዋኢማ ከ5ሺህ በላይ አርብቶ አደር አባወራዎችና እማወራዎች በመንደር ተሰባስበው የተረጋጋና ከግጭት ነፃ ህይወት መምራት መጀመራቸውን የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት አስታወቀ የክልሉ አርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኩሲያ ከዋልታ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት በክልሉ 5ሺህ160 አርብቶ አደር አባወራዎችና እማወራዎች በሶስት ዞኖች ላይ በመንደር ተሰባስበው ቋሚ የተረጋጋና ከግጭት ነፃ የሆነ ህይወት መምራት ጀምረዋል ክልሉ አርብቶ አደሮችን በመንደር እንዲሰባሰቡ ከማድረጉ በፊት ሰፊና ተደጋጋሚ ውይይት ከአርብቶ አደሮቹ ጋር ማድረጉን የገለፁት ቢሮ ኃላፊው አርብቶ አደሩም የመሰረተ ልማትና ማህበራዊ ግልጋሎት መስጫ ተቋማት በተሟሉባቸው አካባቢዎች መኖሩ ያለውን ፋይዳ በመረዳቱ በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ተግባር ማከናወን ተችሏል ብለዋል ከ2004 ጀምሮ በደቡብ ኦሞ ዞን ሰላማጎ ሀመር ዳሰነች ኛንጋቶና በናፀማይ ወረዳዎች በከፋ ዞን ዴቻ ወረዳ እንዲሁም በቤንች ማጂ ዞን በሱርማ ወረዳ አርብቶ አደሮችን በመንደር የማሰባሰብ ተግባር የተከናወነ ሲሆን አርብቶ አደሮቹን በመንደር ከማሰባሰብ በፊት የሚሰፍሩበትን አካባቢ በትምህርትና ጤና የማህበራዊ አገልግሎቶች በእህል ወፍጮና በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በመሰረተልማት የማሟላት ስራ እንደሚሰራ አቶ ዳዊት አስረድተዋል በተጨማሪም ከመሰባሰባቸው በፊት ለመኖሪያና ለእርሻ የሚሆን መሬት የመለካትና የመሸንሸን ስራ እንደተሰራ የተናገሩት አቶ ዳዊት ለመኖሪያ ግማሽ ሄክታር ለእርሻ አግልግሎት የሚውል ደግሞ እስከ አንድ ሄክታር መሬት ለአርብቶ አደሩ መታደሉን ገልፀዋል የቢሮ ኃላፊው በመንደር የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮች ከከብት ርቢ በተጨማሪ በዝናብና በመስኖ ውሃ በመጠቀም የእርሻ ምርቶችን ማምረት እንደጀመሩ ገልፀው የቴክኒክና የግብዓት አቅርቦት ድጋና ክትትሎችን የሚሰጡ ባለሙያዎች በየወረዳው እየደገፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል በሌሎችም አካባቢዎች አስፈላጊው የመሰረተ ልማትና ማህበራዊ ተቋማት ግንባታ ሲጠናቀቅ ሌሎች አርብቶ አደሮችን በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመንደር ማሰባሰብ ተግባር እንደሚከናወን የገለፁት አቶ ዳዊት በመንደር የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮችን የህይወት ለውጥ የተመለከቱ አርብቶ አደሮች ጥያቄ እያቀረቡ እንደሆነም ለዋልታ አስታውቀዋል በክልሉ 62ሺህ አርብቶ አደር አባወራዎችና እማወራዎች እንደሚገኙ ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል;
የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት ሶስተኛ ምዕራፍ በሚቀጥለው ወር ይጀመራል , - ; .._2014. 0 194 146 ; 5; አዲስ አበባ ሚያዚያ 17 2006ዋኢማ - የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጄክት ሶስተኛ ምዕራፍ ከ210 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ በሆን ወጪ በሚቀጥለው ወር እንደሚጀመር የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ የፕሮጄክቱ ተጠባባቂ አስተባባሪ አቶ ሰይድ ኡመር ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት ሶስተኛውን ምዕራፍ የፕሮጄክቱ የመጨረሻ ክፍል ሲሆን የሚካሄዳውም በሶማሌ አፋር ኦሮሚያና ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልሎች በሚገኙ የአርብቶ አደር አካባቢዎች ነው የፕሮጀክቱ ወጭ ከአለም ባንክ ከዓለም አቀፉ የግብርና ልማት ፈንድ በሚገኝ ብድር እንደሁም በኢትዮጵያ መንግስትና ከተጠቃሚው ማህበረሰብ ከሚገኝ መዋጮ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል እንደ አቶ ሰይድ ገለጻ በፕሮጄክቱ በአንደኛውና በሁለተኛው ምዕራፍ ትግበራ እንደየቅደም ተከተላቸው 600ሺህ እና 1 ነጥብ 8 ሚሊየን የሚሆኑ የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢ ሰዎች የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች ተጠቃሚ ሆነዋል በፕሮጄክቱ የሶስተኛ ምዕራፍ ደግሞ ከ2ነጥብ6 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አስተባባሪው ተናግረዋል የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጄክት መንግስት በአገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች ተመጣጣኝና ሁሉንም በየደረጃው ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያከናውነው ሰፊ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ,
ቢሮው በአርብቶ አደር አካባቢዎች መስኖን ማዕከል ያደረገ የግብርና ልማት በማካሄድ ላይ ነው , .._2011_5_. 0 326 158 ; 5; ሀዋሳ ህዳር 5 2004ዋኢማ- በደቡብ ክልል በሚገኙ የአርብቶ አደር አካባቢዎች መስኖን ማዕከል ያደረገ የግብርና ልማት በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ የክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ ቢሮው ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቀው በክልሉ የአርብቶ አደር አካባቢዎች ከተለመደው የእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን መስኖን መሠረት ያደረገ የእርሻ ሥራዎችን ለማስፋፋት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል እርሻን በመስኖ የማልማት ሥራዎች በመከናወን ላይ የሚገኙት በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን የኦሞ ወይጦና የሰገን ወንዞች በሚያልፉባቸው የሐመር የኤርቦሬ የሰላማጎ የዳሰነች እና የኛጋቶም አካባቢዎች ላይ መሆኑን የቢሮው የሕዝብ ግንኙነትና የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ጌቱ ዓለሙ ገልፀዋል በአሁኑ ወቅት ቢሮው 305 አነስተኛና 10 ትላልቅ የመስኖ ውሃ መሳቢያ ጀነሬተሮች ገዝቶ ለወረዳዎቹ በማቅረብ በሥራ ላይ እንዲውሉ ማድረጉን የሥራ ሂደቱ አስተባባሪ አስረድተዋል ጄኔሬተሮቹ በክረምትም ሆነ በበጋ ወራቶች 1ሺ 29 ሄክታር መሬት የማልማት አቅም እንዳላቸውና በዚህም ከ2ሺ በላይ አባወራ አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል በአሁኑ ወቅት አርብቶ አደሮቹን የእርሻ ሥራ ለማስተዋወቅ ሲባል ለጄኔሬተሮቹ የሚያስፈልጉ የቅባትና የናፍታ ወጪዎች ሙሉ በሙሉ በቢሮው እንደሚሸፈን ነው የገለፁት ቢሮው 838 ኩንታል የበቆሎ ስንዴ ሠሊጥና የተለያዩ የጓሮ አትክልት ዘሮችን ለተጠቃሚ አርብቶ አደሮች ማከፋፈሉን ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪው አመልክተዋል የደቡብ ክልል መንግሥት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በክልሉ በሚገኙ የአርብቶ አደር አካባቢዎች ውሃን ማዕከል ያደረገ ልማት በማካሄድ በአንድ ቦታ ተረጋግተው እንዲኖሩ ለማድረግ አቅዶ እየሠራ መሆኑን አስተባባሪው መግለፃቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
ሴት የምግብ ዋስትና አርሶና አርብቶ አደሮች ተሸለሙ , - ; .._2014. 0 260 169 ; 5; አዲስ አበባ ህዳር 262007ዋኢማ - የኦክስፋም አሜሪካ እና የግብርና ሚኒስቴር በጥምረት ባዘጋጁት የ2007 ብሔራዊ ሴት የምግብ ዋስትና አርሶ አርብቶ አደሮች ሽልማት ላይ ስምንት ሴት የምግብ ዋስትና አርሶና አርብቶ አደሮች የሜዳሊያና የ30ሺ ብር ተሸለሙ - ; በሽልማቱ ሥነሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኦክስፋም አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ዳይሬክተር ሚስ ሳራ ሙሳ ባሰሙት ንግግር ተሸላሚ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በተደረገላቸው ድጋፍና በራሳቸው ታታሪነት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያደረጉት ጥረት የሚደነቅ ነው - ; የግብርና ሚኒስቴር ባደረገው ከፍተኛ ድጋፍም የሴቶች ኑሮ መለወጡን ጠቁመው በ2020 አሁን ያለው የግብርና ምርትና ምርታማነትን በ20 በመቶ ሊያሳድግ እንደሚችልም ዳይሬክተሯ አመልክተዋል - ; ኦክስፋም አሜሪካ በቀጣይ መድረክ ለሴቶች የሚደረገው ድጋፍም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል - ; የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ገብረእግዚአብሔር ገብረማርያም በበኩላቸው የአገራችንን ኢኮኖሚ በግማሽ የሚመራው የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ያለ ሴቶች ተሳትፎ ከዳር ሊደርስ እንደማይችል አስረድተዋል - ; የአገራችን ኢኮኖሚ በድህነትና ረሃብ ቅነሳ ትኩረት በማድረግ ውጤታማ ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ጨምረው አመልክተዋል - ; መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በሚያደርጉት ድጋፍ ተሸላሚዎቹ ለአከባቢያቸው ለክልላቸውና ለአገራቸው የልማት አምባሳደሮች በመሆን ተሞክሯቸውን በማካፈል ሌሎች የልማት ጀግኖችን ለማፍራት እንዲንቀሳቀሱ አሳሰበው ሚኒስቴሩም የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀዋል - ; በሽልማት ሥነሥርዓቱ ላይ የኦክስፋም አሜሪካ የመልካም ሥራ አምባሳደር ድምፃዊት ሀመልማል አባተ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ከቤት ለቤት ሥራዎች ባሻገር በኢኮኖሚው ዘርፍ በመሳተፍ የሚያደርጉት ጥረት የሚያስደስታት በመሆኑ ለማበረታታትና ከጎናቸው ለመቆም ቃል ገብታለች - ; በሽልማቱ ሥነሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት የተሸላሚ ቤተሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ,
ሶስተኛው ምዕራፍ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት ተግባራዊ እየተደረገ ነው, - ; .._2014_2. 0 201 179 ; 5; አዲስ አበባ ታህሳስ 14 2007 ዋኢማ - ሶስተኛው ምዕራፍ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት በ210 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ - ; የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ወርቁ ለዋልታ እንደገለጹት ከባለፈው በጀት ዓመት አጋማሽ ጀምሮ ፕሮጄክቱ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው በሶማሌ አፋርኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች ነው - ; ፕሮጀክቱ ባጠቃላይ በ113 ወረዳዎች ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን በሶማሌ ክልል 54 ወረዳዎችበአፋር 23 ወረዳዎች በኦሮሚያ 26 ወረዳዎችና በደቡብ ደግሞ 10 ወረዳዎች ውስጥ ነዋሪ የሆኑ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል - ; እንደ አቶ አበበ ማብራሪያ ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡን ችግሮች መሠረት ያደረጉ የልማት ሥራዎች የገጠር ኑሮ ማሻሻያዎች የአቅም ግንባታና የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ያተኮረ ነው - ; ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከተመደበው 210 ነጥብ 2 የአሜሪካን ዶላር ውስጥ የዓለም አቀፉ የልማት ማህበር 110 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም የዓለም የግብርና ልማት ፈንድ ደግሞ 85 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ቀሪው በክልሎችና በተጠቃሚ ማህብረሰብ የሚሸፈን መሆኑን አቶ አበበ ተናግረዋል ,
ከ 1ነጥብ9 ሚሊዮን በላይ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ በመንደር ማሰባሰቡ ፕሮግራም ተጠቃሚ ሆኗል , - ; .._2015_4. 0 261 195 ; 5; አዲስ አበባ ነሐሴ 22007ዋኢማ- ባለፉት አምስት የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዕቅድ ዘመናት ከ 1ነጥብ9 ሚሊዮን በላይ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ በመንደር ማሰባሰቡ ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆን መቻሉን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ - ; በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ወርቁ ለዋልታ እንደገለጹት ባለፉት አምስት የዕቅድ ዘመናት 2ነጥብ14 ሚሊዮን የአርብቶ አደር ማህበረሰብን በመንደር በማሰባሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ከ1ነጥብ9 ሚሊዮን ወይም ከ88 በመቶ የሚሆነውን የተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል - ; የመንደር ማሰባሰቡ ፕሮግራም በአራቱ ታዳጊ ክልሎች በሆኑት በአፋር በሶማሌ በቤኒሻንጉልና በጋምቤላ ተግባራዊ የማድረጉ ዋነኛ ዓላማ በአገሪቱ ተመጣጣኝ ልማትን ለማረጋገጥ እንደሆነ ያብራሩት አቶ አበበ በአራቱ ክልሎች ከ546 በላይ የልማት ማዕከላት ተቋቁመው የአርብቶ አደሩን ህይወት ለማሻሻል ሲሠሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል - ; በአገሪቱ የአርብቶ አደሩ የህብረተሰብ ክፍል የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ከተፈለገ ለልማቱ ምቹ በሆነ ሥፍራ መሰባሰብ ነበረበት ያሉት አቶ አበበ ከ1ነጥብ9 በላይ የሚሆነውን በመንደር የተሰባሰበ አርብቶ አደር ተጠቃሚ ለማድረግ በአጠቃላይ 1ሺ 654 የውሃ ተቋማት 482 የጤና ኬላዎችና 645 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገንብተዋል - ; አርብቶ አደሩ እንስሳትን በማድለብ ከሚያገኘው ገቢ በተጨማሪ በግብርናው ዘርፍ በመሠማራት ከሰብል በማምረት ገቢውን ይብልጥ እንዲያሳድግ እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አበበ መንግሥት የገበያ ትስስርን በመፍጠር በኩል የበኩሉን ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል ብለዋል - ; የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የታዩን ክፍተቶች በመለየት በተመጣጣኝ ልማት የሰላምን እሴትን በማጎልበትና የፌደራል ሥርዓትን በማጠናከር በኩል ይበልጥ ትኩረት ሠጥቶ እንደሚንቀሳቀስ ገልጿል ,
በደቡብ ክልል ከ 20 ሺህ በላይ አባወራ አርብቶአደሮች በመንደር ሊሰባሰቡ ነው, .._2011__. 0 324 243 ; 5; ሀዋሳ ታህሳስ 162004 ዋኢማ -በደቡብ ክልል ከ 20 ሺህ በላይ አባወራ አርብቶአደሮችን በመንደር ለማሰባሰብ የሚያስችለውን መሰናዶ ማጠናቀቁን የክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነትና የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ጌቱ ዓለሙ ለዋልታ እንዳስታወቁት አርብቶአደሮችን በመንደር የማሰባሰቡ ሥራ የሚካሄደው በደቡብ ኦሞ እና በቤንች ማጂ ዞኖች ነው የመንደር ማሰባሰቡ የሚካሄደው በዞኖቹ በሚገኙ በዳሰነች በሐመር በኛንጋቶም በፀማይ በማሌ በሰላማጎ በቤሮ በማጂ በሜኒትሻሻ እና በሜኒትጎልዲያ ወረዳዎች መሆኑን ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪው አብራርተዋል ቢሮው ባለፉት ሦስት ወራት በሰፈራ ፕሮግራም ለመካተት ፍቃደኛ የሆኑ አባወራዎችን መለየቱን የገለጹት የሥራ ሂደቱ አስተባባሪ ከተያዘው የበጀት ዓመት አጋማሽ ጀምሮ አርብቶአደሮቹን የማስፈር ሥራ እንደሚጀመር ጠቁመዋል እንደ አቶ ጌቱ ማብራሪያ አርብቶአደሮቹ የሚሰባሰቡባቸው መንደሮች ተፋሰሶችን ተከትለው የተዘጋጁ በመሆናቸው ቀደም ባሉት ጊዜያት አርብቶአደሩ በዝናብ እጥረት ምክንያት ግጦሽ ፍለጋ ከቦታ ቦታ በመጓጓዝ ይደርስበት የነበረውን ድካም ያስቀራሉ በአንድ አካባቢ ተረጋግቶ የመኖር ባህልን እንድያዳብርም ያስችላል ለሠፈራ በተመረጡት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች የውሃና የጤና አገልገሎቶች የተዘጋጁ ሲሆን ቀሪ የመሠረተ ልማት ተቋማትን በሂደት የማሟላት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አመልክተዋል ከመሠረተ ልማት ሥራዎች በተጨማሪ ለሠፋሪ አባወራዎች በነፍስ ወከፍ ሁለት ነጥብ አምስት ሄክታር የእርሻ መሬት የግብርና መገልገያ ቁሳቁሶችና ግበዓቶች እንደሚቀርቡላቸው የሥራ ሂደት አስተባባሪው ገልጸዋል በደቡብ ክልል በ 2003 የበጀት ዓመት በመንደር የተሰባሰቡ 10 ሺህ 995 አባወራ አርብቶአደሮች በአሁኑ ወቅት የተረጋጋ ኑሮ በመምራት ላይ እንደሚገኙ ከሥራ ሂደት አስተባባሪው ገለጻ ለመረዳት ተችሏል ,
በአፋር በቀድሞ የመንግስት እርሻ ይዞታ አርብቶ አደሮችን ለማስፈር ትናት ተጠናቀቀ መርሀ-ግብሩን ለማስፈጸም 224ነጥብ8ሚሊየን ብር ያስፈልጋል በአፋር ክልል የቀድሞ የመንግስት እርሻ ይዞታ በነበረ 16ሺ547 ሄክታር መሬት ላይ አርብቶአደሮች ሰፍረው የተረጋጋ ኑሮ እንዲመሩ የሚያስችል ትናት መጠናቀቁን የክልሉ እንስሳትና እርሻ ልማት ቢሮ አስታወቀ በቢሮው የእርሻ ልማትና የሰብል ትበቃ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ መለስ ወርቅነህ ዛሬ ለዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት አርብቶአደሮቹን የማስፈር እንቅስቃሴ የሚከናወነው በዞን አንድ እና ሶስት በሰባት ወረዳዎች ትቅም ላይ ባልዋለው መሬት ነው የክልሉ መንግስት በመደበው ከ644ሺ ብር በላይ በአዋሽ ወንዝ ዙሪያ ከብት አርቢዎቹን ለማስፈር ባለፉት ሁለት አመታት የተካሄደው ትናት ነዋሪዎቹን ከእንስሳት እርባታ በተጨማሪ በመስኖ በዝናብ የእርሻ ስራን ለማካሄድ እንደሚያስችላቸው ባለሙያው ተናግረዋል በጥናቱ መሰረት ፈቃደኞችን በመለየት ለአርብቶአደሮቹ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሄክታር መሬት በመስጠት ለማስፈር መታቀዱንና በአካባቢውም የትምህርት የጤና የውሃ የመስኖና ሌሎች የመሰረተልማት አውታሮች እንደሚዘረጉ አስታውቀዋል መሬቱ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ በመሆኑ መርሀ-ግብሩ ከብት አርቢውን ቀደም ሲል ግጦሽና ውሃ ፍለጋ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አርብቶአደሮች በአንድ ቦታ ተረጋግተው እንዲኖሩ ከማስቻሉም በላይ የምግብ ዋስትናን እንደሚያረጋግጥላቸው አመልክተዋል የመርሀ-ግብሩን አፈጻጸም ለመከታተል በአይሳኢታ አሚባራና ገዋኔ ወረዳዎች ማስተባበሪያ የእርሻ ታቢያዎችና የፕሮጀክት ማእከሎች እንደሚቋቋሙና በክልል ደረጃም አስተባባሪ ቦርድ እንደሚኖር ገልጸዋል መርሀ-ግብሩን ተግባራዊ ለማድረግ በጉዳዩ ላይ የአርብቶአደሮቹን አስተያየት ለመሰብሰብ ለቦታ መረጣ አነስተኛ የሙከራ ስራዎችን ለማከናወንና ሌሎች ቅድመሁኔታዎችን ለማመቻቸት የክልሉ መንግስት በመደበው 100ሺ ብር በሚቀጥለው ወር እንቅስቃሴ እንደሚጀመር አስታውቀዋል በሚቀጥሉት አምስት አመታት ለሚካሄደው ለዚሁ መርሀ-ግብር ማስፈጸሚያ 224ሚሊየን807 ሺ 246 ብር እንደሚያስፈልግ ተቁመው ወጪው በመንግስት ብቻ ሊሸፈን ስለማይችል የጥናቱ ሰነድ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ቀርቦ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚጠየቅ አመልክተዋል
በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ያስችላሉ አቶ ጁነዲን ሳዶ, .._2012__. 0 195 146 ; 0; 5; አዲስ አበባ የካቲት 22 ቀን 2004 ዋኢማ - በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር አስታወቁ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲ ሳዶ 640 ሚሊዩን ብር በጀት ግንባታው በመፋጠን ላይ ያለውን የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ሰሞኑን ከጎበኙ በኋላ እንደተናገሩት በሃገሪቱ ሶስተኛ የሆነው ይኽው ፋብሪካ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር ሥራ አጥነትን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ያስችላልከፋብሪካው ግንባታ በተጓዳኝ የሚከናወነው የተንደሆ ወጣቶች ልማት ፕሮጀክትም የአካባቢው ህብረተሰብ የልማት ተጠቃሚነት የተረጋገጠበት ነው ብለዋልእንዲሁም በ40 ሚሊዩን ብር በጀት በመከናወን ላይ ያለው የአፋር ከተሞች የኤሌትሪክ ሃይል ፕሮጀክት የከተሞች የእድገት ፖኬጅ ለማፋጠን ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋልበተጨማሪ በ98 ነጥብ 7 ሚሊዩን ብር በጀት በመከናወን ላይ የሚገኘው የሰመራ ዩኒቨርስቲ የማስፋፊያ ሥራም ዩኒቨርስቲውን ተጠቃሽ የምርምርና ስርፀት ማእክል ለማድረግ ያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል ከዚህም ሌላ ከአዩዲን ጋር የተቀላቀለ ጨው ማምረት የጀመረው የአፍዴራ ጨው አምራች ኩባንያ የአርብቶ አደሩን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት የተሰጠበት መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል ንፁህ የመጠጥ ውሃ የጤና የመንገድና የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀሙን አበረታች መሆኑ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል በአፋር ክልል የሚከናወኑ ተቋማዊ የአቅም ግንባታ ተግባራት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ያስችላሉ አቶ ጁነዲን ሳዶ ,
አርብቶ አደሩን የዘላቂ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ክልል አስታወቀ, .._2012__. 0 307 230 ; 0; 5; አዲስ አበባሚያዚያ 192004 ዋኢማ - በደቡብ ብሔሮችብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አርብቶ አደሩንና ከፊል አርብቶ አደሩን የዘላቂ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ መሆኑን የክልሉ አርብቶ አደሮች ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ የክልሉ አርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅሩ ኛካል ለዋልታ እንደገለፁት ቢሮው አርብቶ አደሩም ሆነ ከፊል አርብቶ አደሩ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ከቦታ ቦታ በመዘዋወር የሚያጠፋውን ጊዜና ጉልበት በማስቀረት በአንድ ቦታ ተረጋግቶ እንዲኖር የማድረግ ሥራ እየሰራ ነው እንደ አቶ ፍቅሩ ማብራሪያ አርብቶ አደሩ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ሲንቀሳቀስ በውስጥም ሆነ ከውጭ ለተለያዩ ግጭቶች የመጋለጡ እድል የሰፋ ነበር ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የሚያጋጥሙትን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ድርጅትኢጋድ እና ከአዋሳኝ አገሮች ጋር በመተባበር አርብቶ አደሩን ያሳተፈ ጥናት ተከናውኗል በጥናቱም አርብቶ አደሩ በአንድ አካባቢ ተወስኖ የተረጋጋ ሕይወት በመምራት የዘላቂ ልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ ለመሆን ሙሉ ፍላጎቱን አሳይቷል ብለዋል የኢፌዲሪ መንግስትም ሆነ የክልሉ መንግስት የአርብቶ አደሩን ፍላጎትና አገሪቱ የነደፈቻቸውን የልማት ዕቅዶች መነሻ በማድረግ አርብቶ አደሩንና ከፍል አርብቶ አደሩን በልማት ለማሳተፍ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሩ ተናግረዋል በአሁኑ ወቅት በደቡብ ብሔሮችብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በተለይም በደቡብ ኦሞ ዞን የኩራዝ ስኳር ኮርፖሬሽን ወደ ሥራ መግባቱን ተከትሎ አርብቶ አደሩን የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል የኩራዝ ስኳር ኮርፖሬሽን መቋቋሙን ተከትሎ አርብቶ አደሩ በመስኖ በመታገዝ በሰብልና ቋሚ ተክሎች ልማት ላይ በመሳተፍ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ የድጋፍና ክትትል ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል እንደ አቶ ፍቅሩ ገለፃ አርብቶ አደሩ ቶሎ ወደ ልማቱ እንዲገባም የመስኖ ውሃና የእርሻ መሬት የሚያገኝበት ሁኔታ ተመቻችቷል በአካባቢው እየተስፋፋ ያለውን የመሠረተ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት በአግባቡ ከተጠቀመ አርብቶ አደሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ ወደ ባለሀብትነት እንደሚሸጋገርም አቶ ፍቅሩ ተናግረዋል በአሁኑ ሰዓት የክልሉ መንግስት አርብቶ አደሩን በመንደር በማሰባሰብ በመስኖ ውሃ በመታገዝ የሸንኮራ አገዳ አልምቶ ለፋብሪካው በማቅረብ ገቢ እንዲያገኝ ለማስቻል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል የኦሞ ወንዝን ተከትለው ለሚቋቋሙ ስድስት የስኳር ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግል የሸንኮራ አገዳ ተከላ ከተያዘው ዓመት መጀመሪያ አንስቶ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትን ጠቅሰን በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል የፕሮጀክቱ ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው በስኳር ፋብሪካዎቹ የግንባታ ሂደት የአካባቢው አርብቶ አደሮች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉ ፋብሪካዎቹ የምርት አገልግሎት ሲጀምሩ ደግሞ የሸንኮራ አገዳ ቅጠሎችን እና የሞላሰስ ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ሥራዎችን ማከናወን ይችላሉ ,
በኦሮሚያ በአርብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች አካባቢ እየተካሄዱ ያሉ የሰፈራ ፕሮግራሞች ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆኑ ተገለፀ , .._2012__19. 0 254 191 ; 5; አዲስ አበባ ግንቦት 12 2004 ዋኢማ - በኦሮሚያ ክልል በአርብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች አካባቢ እየተካሄዱ ያሉ የሰፈራ ፕሮግራሞች የማህበረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በምፍታት ተጨባጭ ለውጥ በማምጣት ላይ እንደሚገኙ የክልሉ አብቶአደሮችና ከፊል አርብቶአደሮች ልማት ኮሚሽን አስታወቀ የኦሮሚያ አርብቶአደሮችና ከፊልአርብቶ አደሮች ልማት ኮሚሽን የኮሚዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መገርሳ ቀነኒሳ ለዋልታ እንዳስታወቁት በክልሉ እየተካሄደ ያለው የሰፈራ ፕሮግራም የአርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን ማህበረሰብ የውሃ የመሰረተልማት አቅርቦት ችግሮችን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት እያስቻለ ነው እንደ ባለሙያው ማብራሪያ በክልሉ አርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን በማስፈር በርካታ የመስኖና የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተከናውኗልበፈንታሌ ወረዳ ብቻ የተከናወኑት የመስኖ ፕሮጀክቶች ከስምንት ሺ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ እንዳደረጉ የጠቆሙት ባለሙያው በወረዳው የተከናወኑ የትምህርት ቤቶች የጤና ማዕከላትና የእንስሳት ህክምና መስጫ ክሊኒኮች የንጹህ ውሃ የኤሌከትሪክና የስልክ መሠረተ ልማቶችም አርብቶአደሩንና ከፊል አርብቶአደሩን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል በወረዳው እየተካሄዱ ያሉ ፕሮጀክቶች አርብቶአደሩም ሆነ ከፊል አርብቶአደሩ በአንድ ቦታ ሰፍሮ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልክና ቀድሞ ውሃና ግጦሽ ፍለጋ የሚያባክነውን ጊዜና ጉልበት በልማት ሥራ ላይ እንዲያውል እንዳስቻሉትም አቶ መገርሳ ገልጸዋልእንደ አቶ መገርሳ ማብራሪያ በፈንታሌ ወረዳ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ዘርፍ ለአፈርና ውሃ እቀባ ለእርከን ሥራና ደንን መልሶ ለማልማት ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራው ሥራም በወረዳው በስድስት ቀበሌዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ አድርጓል የፈንታሌ ወረዳን ተሞክሮ በመወሰድ በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አቶ መገርሳ ጠቁመው በቦረና ዞን ድሬ ወረዳ የውሃ ጉድጓድ በማውጣት እንዲሁም በጉጂ ዞን የገናሌን ወንዝ ተፋሰስ ተከትሎ አርብቶአደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋልበአርብቶአደሩ አካባቢዎች ቀደም ሲል ከውሃና ከግጦሽ ቦታዎች እጥረት የተነሳ በተወሰኑ ቦታዎች ተደጋጋሚ ግጭቶች ይስተዋሉ እንደነበር ያሰታወሱት አቶ መገርሳ አሁን በሰፈራ ፕሮግራሙ ምክንያት ችግሩ መፈታቱን አብራርተዋል,
በክልሉ የአርብቶ አደሩን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ, መንግስት የአርብቶ አደሩን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶክተር የሱፍ መሀመድ ለዋልታ እንደገለጹት መንግስት በክልሉ ተራርቆ የሚኖረውን የአርብቶ አደር ማህበረሰብ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማሻሻል ባደረገው ጥረት የጤና ሽፋኑን 74 በመቶ ማድረስ ችሏል የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማረጋገጥ የጤና ኬላዎች ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎችን ከወትሮው በተሻለ መልኩ ማዳረስ መቻሉን ገልፀው በአሁኑ ወቅት 1ሺ 60 ጤና ኬላዎች 121 ጤና ጣቢያዎችና 8 ሆስፒታሎች በሙሉ አቅም አገልግሎት እየሰጡ ናቸው ብለዋል ቀደም ባሉት ዓመታት በክልሉ ገጠር አካባቢ የሚኖረው የአርብቶ አደር ማህበረሰብ ህክምና ለማግኘት ይደርስበት የነበረውን እንግልትና ሞት መቀነስ መቻሉን ጠቁመው የህክምና አገልግሎቱን በየአካባቢያቸው እንዲያገኙ በመደረጉም የክልሉን የጤና ሽፋን ወደ 74 በመቶ አሳድጎታል ብለዋል እንዲሁም ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ በተጀመረው የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም በርካታ አባውራዎች በመከላከል ላይ የተመሰረተ የጤና ዋስትናቸውን ማረጋገጥ እንዲችሉ መደረጉን የገለጹት ዶክተር የሱፍ በአሁኑ ወቅት 1ሺ 960 የሚሆኑ ባለሙያዎች አገልግሎቱን እየሰጡ ሲሆን ፕሮግራሙ በተለይም የእናቶችና ህጻናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል በተመሳሳይም ከ181 ሚሊየን ብር በላይ ውጭ የተደረገበት የጂጂጋ መለስ ዜናዊ ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ እየተጠናቀቀ በመሆኑ በዚህ ዓመት መጨረሻ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ጠቁመው ሆስፒታሉ የመድኃኒትና የህክምና ቁሰቁሶች በማሟላት በወቅቱ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ነው ብለዋል ,
በአፋር የአርብቶ-አደሩን ኑሮ ለመለወጥ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል -ርእሰመስተዳድሩ, በአፋር ብሄራዊ ክልል የሚገኘዉን የአርብቶ-አደር ኑሮ ለማሻሻል በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አካላት በቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አስገነዘቡ በክልሉ በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሳተፉበትና በ2005 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ የሚወያይ ሰብሰባ በሰመራ ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እስማኤል ዓሊሴሮ ስብሰባዉን ሲከፍቱ እንደተናገሩት ታላቁ መሪያችን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻልና ህይወቱን ለመቀየር ያስቀመጡትን ራእይ ከዳር በማድረስ ረገድ ሁሉም በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀስ ይገባል ለዘመናት የከብትን ጭራ ተከትሎ ውሃና ሳር ፍለጋ ከቦታ ቦታ ሲንከራተት የኖረዉ አርብቶ-አደር ህብረተሰብ በመንደር ተሰባስቦ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ታላቁ መሪያችን የነበራቸዉን ጽኑ ፍላጎትና እምነት ለማሳካት የእያንዳንዱ የክልሉ ህብረተሰብ ሃላፊነትና ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል የአርብቶ-አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመቀየር ብሎም ወደ ዘመናዊ አርብቶ-አደርነትና ግብርና እንዲሸጋገር በአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የተያዘዉ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አስገንዝበዋል በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በትምህርት በግብርናና ገጠር ልማት በጤናና ውሃ ሃብት ልማት በመንገድና በሌሎች የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ የተቀመጠዉን አቅጣጫ በመፈጸም የአርብቶ አደሩን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሌት ተቀን ተግቶ መስራት እንደሚገባም አቶ እስማኤል ተናግረዋል ከአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎሜሸን እቅድ አንፃር በያዝነው የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት የተመለከተ ሪፖርት በክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ቀርቦ ዉይይት ተካሄዶበታል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስብሰባው ላይ የ32ቱም የወረዳ መስተዳድር አመራሮች የአምስቱም የዞን መስተዳድር አመራሮችና በክልሉ የሁሉም የሴክተር እና ቢሮ ሃላፊዎችና የስራ ሂደት ባለቤቶች ተሳታፊ ሆነዋል ,
በአርብቶ አደር አካባቢዎች ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ እንደሚቻል ተገለጸ , - ; .._2012. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ታህሳስ 112005ዋኢማ - በአርብቶ አደሩ አካባቢዎች አስተማማኝ ገበያን ማስፋፋትና የእሴት ሰንሰለቱን ማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ጌታሁን ትናንት የአርብቶ አደር ተጋላጭነት የመቋቋም ብቃትን ለማሻሻልና ገበያውን ለማስፋፋት የሚያስችል የውይይት መድረክ ላይ እንደተናገሩት አስተማማኝ ገበያን ማስፋፋትና የእሴት ሰንሰለቱን ማጠናከር የአርብቶ አደሩን ምርታማነት ማሳደግና ኑሮውን ለመቀየር ያስችላል በአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ አካባቢ የእሴት ሰንሰለት የሚፈጥርና የአርብቶ አደሩን አቅም የሚያሳድግ አዲስ ፕሮግራም ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመው ይህም የአርብቶ አደሩን ህይወት በመቀየር በኩል ከፍተኛ ከመኖሩም ባሻገር ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል እንዲሁም ፕሮግራሙ በአየር ንብረት ምክንያት የሚከሰተውን የምግብ እጥረትና በእንስሳት ገበያው ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ችግሮችን በመቋቋም በኩል ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት ዳይሬክተር ዴኒስ ዌለር በበኩላቸው አዲሱ ፕሮግራም በኦሮሚያ በአፋርና በሶማሌ ክልሎች በሚገኙ 30 ወረዳዎች ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል ፕሮግራሙ ተግባራዊ ሲደረግም ከ250 ሺ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ሊያደርግ እንደሚችል ጠቁመው እንደ ዴኒስ ዌለር ገለፃ ድርጅታቸው የአርብቶ አደሩን አኗኗር ዘይቤ እንዲላቀቁ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ እንደነበር ተናግረዋል ፕሮግራሙ መነደፉ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው የጠቀሱት ዴኒስ ዌለር የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ኑሮ በማሻሻል የእንስስት ሃብቱን እንዲጠቀም ገበያውን በማስፋፋት የአምስት አመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀዋል ፕሮግራሙ መነደፉ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው የጠቀሱት ዴኒስ ዌለር አርብቶ አደሩ የእንስስት ሃብት ገበያውን በማስፋፋት ኑሮው እንዲሻሻል በማድረግ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ በማድረግ በኩል የተያዘውን የአምስት አመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀዋል ፕሮግራሙ ተግባራዊ የሚደረገው በ52 ሚሊየን ዶላር ሲሆን ከዚህ ውስጥም 4 ሚሊየን ዶላሩ ለአልሚ ምግብ አቅርቦት እንደሚውል ጠቁመው ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ፕሮግራሙ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል ,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
ክልሉ 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን አስታወቀ, .._2013_. 0 262 192 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 212005 ዋኢማ - የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አስታወቀ በክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት ኩይሳ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንደር ለተሰባሰቡት አርብቶ አደሮች አስፈላጊውን የማህበራዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ 83 ተቋማት በግንባታ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል የአገልግሎት መስጫ ተቋማቱ ትምህርት ቤቶች ጤና ኬላዎች የባለሙያ መኖሪያ ቤቶች የእህል ወፍጮዎች መጋዘኖች የቀበሌ ጽህፈት ቤቶችና የአርብቶ አደር ማሰልጠኛዎችን እንደሚያካትቱ ሃላፊው ተናግረዋል በክልሉ በሶስት ዞኖች በሚገኙ 12 ወረዳዎች የሚኖረው ግማሽ ሚሊየን አርብቶና ከፊል አርብቶ አደርን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የክልሉ መንግስት እየሰራ መሆኑንም ሃላፊው ተናግረዋል ያለፉት ስርዓታት ለአርብቶ አደሮቹ ምንም ዓይነት ትኩረት እንዳልሰጡ የጠቆሙት አቶ ዳዊት መንግስት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ የአርብቶ አደሮች የልማት ፓኬጅ ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር ከተወሰዱ እርምጃዎች አንዱ በሰፈር ማሰባሰብ መሆኑን የገለጹት አቶ ዳዊት በቀጣይ ዓመታትም በመንደር የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል አርብቶ አደሩ በመንደር ማስፈር ጋር ተያይዞ እየተነሳ ያለው አሉባልታ የአርብቶ አደሩ ህይወት እንዲቀየር በማይፈልጉ ግለሰቦች የመሚነዛ መሆኑን ሃላፊው ጠቁመው ፕሮግራመሙ እየተፈጸመ ያለው ፈቃደኝነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን አስረድተዋል ,
በቤንች ማጂ 22 ሺ አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የልማት ፕሮግራም እየተካሄደ ነው የቤንች ማጂ ዞን ግብርና መምሪያ ዘንድሮ በሁለት ወረዳዎች በ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ወጪ 22 ሺ አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የልማት ፕሮግራም በመካሄድ ላይ መሆኑ አስታወቀ በመምሪያው የኤክስቴንሽን ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ስማቸው ቸኮል ትላንት ለዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት ፕሮግራሙ በሱርማና ዲዚ ወረዳዎች ከቦታ ወደ ቦታ የሚዘዋወሩ አርብቶ አደሮችን በአንድ አካባቢ በማስፈር ከከብት እርባታው በተጓዳኝ መደበኛ የእርሻ ስራን እንዲለማመዱ የሚያደርግ ነው ከክልሉ መንግስት በተመደበው በዚሁ በጀት መምሪያው ከተያዘው አመት መግቢያ ጀምሮ 8 ሺ ሄክታር የእርሻ መሬት ጥናትን ጨምሮ በንብ እርባታና መኖ ልማት ሶስት ሰርቶ ማሳያዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት አስተባባሪው በቀጣይ ወራትም በአርብቶአደሩ ዘንድ የግብርና ዘዴ ለማስፋፋት የሚያስችሉ የሰብል ሙከራ ታቢያዎች ለማቋቋም መዘጋጀቱን አስታውቀዋል መምሪያው አምናም ለአርብቶ አደሮቹ በእንስሳት እርባታና መኖ ልማት በጤና አገልግሎት በሰብል ልማትና ትበቃ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠቱንና ሶስት የልማት ጣቢያ ሰራተኞች መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ በረቶች መገንባቱን አስተባባሪው አስታውሰዋል
በአምስት የሙያ ዘርፎች የሰለጠኑ አርብቶና አርሶ አደር ወጣቶች ተመረቁ, በኢትዮጵያ ስኳር ልማት ኮርፖሬሽን የበጀት ድጋፍ በጂንካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በአምስት የሙያ ዘርፎች በመጀመሪያ ዙር የሰለጠኑ 2 መቶ 2 አርብቶ አደርና አርሶ አደር ወጣቶች ተመረቁ ለተመራቂዎች በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት በተለያየ የስራ ዘርፍ እንዲያገለግሉ እንደሚደረግ በምረቃው ወቅት ተጠቁሟል በግምበኝነት አናጺነት ብረታ ብረት ብየዳ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ቀለም ቅብና በማስዋብ ሙያዎች ለ30 ቀናት ስልጠና የተሰጣቸው ወጣቶች ከደቡብ ኦሞ ዞን 9 ወረዳዎች የተውጣጡ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል ሰልጣኞቹ የደቡብ ኦሞ ዞን ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ባገኘው የግማሽ ሚሊየን ብር የገንዝብ ድጋፍ በሶስት ዙር በዘንድሮ በጀት ዓመት ሊያሰለጥን ካሰባቸው 6 መቶ 60 ወጣቶች መካከል የመጀመሪያዎቹ ናቸው የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞሉካ ውብነህ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ሁሉንም በየደረጃው ተጠቃሚ የሚያደርግ ትልቅ ሀገራዊ ልማት መሆኑን ገልጸው በተለይ የደቡብ ኦሞ ዞን ማህበረሰብን በላቀ ደረጃ ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል ስልጠናው ቀጣይነት እንደሚኖረው የተናገሩት በፌዴራል ስኳር ኮርፖሬሽን የህዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳመነ ዳሮታ በበኩላቸው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት የአካባቢውን ማህበረሰብ በተለይ ወጣት አርብቶና አርሶ አደሮች የፕሮጀክቱ ባለቤት በመሆናቸው የበለጠ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል ሎኮበር ታምራት ለዚህ ስልጠና ከዳሰነች ወረዳ የመጣ በአናጺነት ሙያ ስልጠናውን ከወሰዱ አርብቶ አደር ወጣቶች አንዱ ሲሆን የአናጺነት ሙያ ይመኘው የነበረ ቢሆንም በአቅም ማነስ ምክንያት ሳሰለጥን መቆየቱን ገልጾ አሁን እድሉን ባገኘው እድል የሙያ ባለቤት መሆን እንደቻለ ይናገራል ይህ ስልጠና የሙያው ባለቤት እንድሆን አድርጎኛል ለኦሞ ኩራዝ ስኳር ፕሮጀክት ብቻም ሳይሆን ለወደፊቱም የሚጠቅመኝን ሙያ አግኝቻለው ሲል ለዋልታ ገልጿል ኩራዝ ስኳር ልማት መንግስት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ማሳኪያ ትልቅ ፕሮጀክቶች ብሎ ከመደባቸው ልማቶች መካከል አንዱ ነው ግንባታቸው የተጀመረው ስድስት የስኳር ፋብሪካዎች ሲጠናቀቁ እስከ 4 መቶ ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ይፈጥራል ተብሎ ይታሰባል ከስድስቱም ፋብሪካዎች 106 ሚሊዮን ኩንታል ስኳር በቀን ማምረት ያስችላል በ175 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የሚካሄደው የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት በእያንዳንዱ ፋብሪካ ዙሪያ አንድ ዋና ከተማ ሁለት መለስተኛ ከተሞችና ስምንት የእርሻ መንደሮች ግንባታ ይከናወናል በአሁኑ ወቅትም የ7 መቶ 12 ቤቶች ግንባታን ጨምሮ የአንድ ዋና ከተማና የእርሻ መንደር ግንባታዎች እንዲሁም ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት የሚችል የመስኖ አውታር በመገንባት ላይ እንደሆነ የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኑረዲን አሳሮ በምረቃው ወቅት ተናግረዋል በጠቅላላው ከ20 ሺህ በላይ ቤቶች ይገነባሉ ያሉት ስራ አስኪያጁ ለዚህም መሳካት ስንፍናንና ድህነትን የሚጠሉ ችግር መቋቋም የሚችሉና ሰርተው መለወጥ የሚፈልጉ እጅግ ብዙ ወጣቶች ያስፈልጋሉ ብለዋል ,
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘው ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው, - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 122005 ዋኢማ - ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘዉ ጥረት በክልሉ ተስፋ ሰጪ ዉጤት እያስገኘ መሆኑን የሱማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አስታወቁ አስራ አራተኛዉ የአርብቶ አደር ቀን በክልል ደረጃ በጅጅጋ ከተማ ትላንት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ በበዓሉ ላይ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ዘጠና አንድ አርብቶ አደሮች ተሸላሚ ሆነዋል የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በተወካያቸው አማካኝነት ለበአሉ ታዳሚዎች ባስተላላፉት መልዕክት የክልሉን አርብቶ አደር ህይውት ለመለወጥ የተጀመሩ ጥረቶች አበረታች ውጤት እያሳዩ ነው በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አርብቶ አደሩ በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት እየጎለበተና እየዳበረ ለመምጣቱ አይነተኛ ማረጋገጫ መሆኑን አስታዉቀዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት በጋራ የአርብቶ አደሩን ህይውት ለማሻሻልና ለመለወጥ የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተስፋፋ መሆናቸዉን ርእሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸዉ ላይ ገልጠዉ በዚህም ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደሩ ልማት መፋጠን የነበራቸዉ በጎ ራአይ ስኬት እየተረጋገጠ ነዉ ብለዋል በክልሉ ከ2003 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ያለው የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር በተፋስስ ልማት በእድገትና ትራንስፎርሚሽን እቅዱ መሠረት በጥናት ተደግፎ እየተከናወነ መሆኑም የወደፊቱን የእድገት ተስፋ አመለካች እንደሆነ ገልጠዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት ለአርብቶ አደሩ ልማትና እድገት መፋጠን እና ለምዕተ አመቱ የልማት ግብ መሳካት በሰጡት ልዩ ትኩረት ከ2 ቢልየን ብር በላይ በጀት በመመደብ የከርስ ምድር ውሃ ልማትየመብራትየስልክና የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች በክልሉ በተለያዩ ዞኖች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተዉ የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር 138ሺህ 781 እማወራና አባወራ አርብቶ አደሮች በመንደር በማሰባሰብ በጥምር ግብርና ስራ እንዲሳተፉ በማድረግ በተለይ በመጀመሪያው አመት የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮች የምግብ ዋስትናቸውን ማረጋገጥ እንደቻሉም ርእሰ መስተዳደሩ አመልክተዋል እንዲሁም በ39 ወረዳዎች የሚካሄደዉ የሴፍትኔት ፕሮግራም ከ900 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮችን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋራ ተያይዞ ሊከሰቱ ከሚችሉ የድርቅ አደጋዎችና ሌሎች ችግሮች ለመጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑበት መሆኑን ገልጸዋል በባዓሉ ላይ ተሸላሚ ከነበሩት መካከል አቶ ጣሂር ዩሱፍ 80 ግመሎችን ማርባት በመቻላቸዉ በክልል አቀፍ ደረጃ ለሽልማት መብቃታቸዉን በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል ወይዝሮ አሻ አህመድና አቶ ሲራጅ ሼህ መሀመድ በበኩላቸው በማህበር በመደራጀት የወተት ልማት በማካሄድ በአመት ከ6ሺህ ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ ማግኘት በመቻላቸው ተሸላሚ መሆናቸውን ተናግረዋል በበዓሉ ላይ የተገኘ የአርብቶ አደር ተወካዩች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የአርብቶ አደር በዓል መከበሩ በአርብቶ አደሩ አከባቢ መልካም እስተዳደር በማስፈን ልማትን ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስነ ስርዓቱ ላይ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዩች የተገኙ ሲሆን በአመቱ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡና ከ68 ወረዳዎች የተውጣጡ አርብቶ አደቶሮች ማህበራትና ቡድኖች የተዘጋጀላቸው ሜዳሊያና ምስክር ወርቀት ከክልሉ ርእሰ መስተዳደር ተወካይ ከርእሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች እጅ ተቀብለዋል ,
የአርብቶ አደሩን ህይወት ለማሻሻል መንግስት በቀጣይነት እንደሚሰራ ጠሚ ኃይለማርያም ገለፁ , - ; .._2013. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 182005 ዋኢማ አርብቶ አደሮች በልማትና በመልካም አስተዳዳር ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ 14ኛው የአርብቶ አደር በዓልታላቁ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደር ህዝባችን የነበራቸው ራኢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እንረባረባለን በሚል መሪ ቃል በኦሮምያ ክልል ያቤሎ ከተማ ተከብሯል በበዓሉ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አርብቶ አደሩ የጀመራቸው የልማትና የሰላም እንቅሰቃሴ እውን መሆን ያሰጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመካካላችን ባይኖሩም ያስጀመሩት ስራ ሁላችን በመረባረብ ዳር ለማድረስ ቃላችን የምናድስበት ነው ብለዋል ባለፉት ዓመታት ያከበርናቸው በዓላት በአገራችን በተለያዩ አከባቢዎቸ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች መካከል ቅርብ ግኑኙነት በመፍጠር የጋራ ችግሮቻቸው በመመካር እንዲፈቱና ከመንግስትም ጋር በቀጣይነት በመወያየት አቅጣጫዎች ለማሳየት አግዘዋል ብለዋል አርብቶ አደሩ ህዝባችን ዘለቄታዊ ህይወቱን ለመቀየር በሰላምና በመልካም አስተዳደር የተሻለ እንዲሆን መንግሰት ይሰራል ብለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በበኩላቸው ከሀገሪቱ የህዝብ ብዛት 12 ከመቶ የሚሆነውና በተፈጥሮ ሀብት በእንስሳት በከርሰ ምድር ውሃ በታደለው አከባቢ የሚኖው አርብቶ አደር ያለፉት ስርአቶች ያራምዱት በነበረው ኢ-ፍትሃዊ አስተዳዳር ምክንያት በከፋ ድህነትና ኋላ ቀር አኗኗር ይኖር እነደነበር ጠቁመዋል - ; ይህን ሁኔታ ለመቀየርና አርብቶ አደሩ የተሻለ ህይወት እንዲኖረው መንግስት የጀመረውን ልዩ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል በተንቀሳቃሽ ኑሮ ሰላምና ልማት ማሟላት አይቻልም ያሉት ዶክተር ሽፈራው አርብቶ አደሩ በመንደር በማሰባሰብ ከእንስሳት እርባታ በተጨማሪ በጥምር የእርሻ ዘዴ በመጠቀም የተሻለ ውጤት እያገኘ እነደሆነ ገልፀዋል በማህበራዊና በመሰረተ ልማት ተቋሞችም ተጠቃሚ እየሆነ ነው ብለዋል - ; የኦሮምያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ አብዱልአዚዝ መሀመድም የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥና ከልማቱ ተጠቃሚ አንዲሆን መሰረተ ልማት በማስፋፋት ምቹ የገበያ ሁኔታ እንዲፈጠርለት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት - ; በበዓሉ ላይ ከተለያዩ የአርብቶ አደር አከባቢዎች በስራቸው ሞዴል የሆኑ 144 አርብቶ አደሮች ተሸልመዋል - ; በባዓሉ ላይ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት የክልል ርእሳነ መስተዳድሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ቀጣዩ 15ኛው የአርብቶ አደር በዓል በአፋር ክልል በ2007 ዓ.ም እንደሚከበርም ታውቋል;
762 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተሸለሙ, - ; .._2013. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ የካቲት 252005 ዋኢማ - በ6ኛዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል ላይ 762 አርዓያ የሆኑ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ዛሬ የካቲት 242005 ተሸልመዋል የታላቁ መሪ የክቡር አቶ መለስ ዜናዊን የግብርና ራዕይ ለማሳካት በላቀ ፅናትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በሚል መሪ ቃል በተከበረዉ በዓል ላይ ከተሸለሙት ዉስጥ 30 በመቶ ያክሉ ሴቶች ሲሆኑ 20 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ወጣቶች ናቸዉ ዘንድሮ ከተሸለሙት ዉስጥ 70 ከመቶ ያክሉ አዲስ ተሸላሚዎች ናቸዉ አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ለሽልማት የበቁት የተሻሻሉ የግብርና ግብዓቶችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነታቸዉን በማሳደጋቸዉ ነዉ ተሸላሚዎቹ በተፋሰስ ስራና በመስኖ ልማት እንደዚሁም በሌሎች የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም የሆኑ ናቸዉ ተሞክሯቸዉን ለሌሎች በማካፈልና መሰሎችን በማፍራትም ዉጤታማ እንደሆኑ በስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል በበዓሉ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርናዉ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል በላቀ ፅናት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል በዓሉን ስናከብርም በግብርና ምርታማነታችን ላይ እመርታ ለማምጣት ቃል በመግባት ሊሆን ይገባል ብለዋል የግብርና ሚንስትሩ አቶ ተፈራ ደርበዉ ደግሞ በአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መካከል የተሻለ የዉድድር መንፈስ በመፍጠርና የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ማሳካት ቁልፍ ተግባራችን ነዉ ብለዋል የበዓሉ አዘጋጅ የሆነዉ የአማራ ብሄራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌዉ ጎበዜ በበኩላቸዉ በግብርናዉ ዘርፍ ዉጤት ያመጣንዉ አመራሮች ባለሙያዎች አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮችና ባለሃብቶች ባደረጉት የተቀናጀ ርብርብ ነዉ ብለዋል ስለሆነም ለእነዚህ አካላት እዉቅና መስጠት ለቀጣይ ስኬታችን መሰረት ይሆናል ነዉ ያሉት ኢዜአ እንደ ዘገበው አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ከሜዳሊያ ባሻገር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ቦንድም ተሸልመዋል ከ1999 ጀምሮ እየተካሄደ ባለዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል እስካሁን 3709 አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮች አጋር አካላትና ድርጅቶች ተሸልመዋል,
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘው ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው, - ; ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘዉ ጥረት በክልሉ ተስፋ ሰጪ ዉጤት እያስገኘ መሆኑን የሱማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አስታወቁ አስራ አራተኛዉ የአርብቶ አደር ቀን በክልል ደረጃ በጅጅጋ ከተማ ትላንት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ በበዓሉ ላይ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ዘጠና አንድ አርብቶ አደሮች ተሸላሚ ሆነዋል የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በተወካያቸው አማካኝነት ለበአሉ ታዳሚዎች ባስተላላፉት መልዕክት የክልሉን አርብቶ አደር ህይውት ለመለወጥ የተጀመሩ ጥረቶች አበረታች ውጤት እያሳዩ ነው በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አርብቶ አደሩ በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት እየጎለበተና እየዳበረ ለመምጣቱ አይነተኛ ማረጋገጫ መሆኑን አስታዉቀዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት በጋራ የአርብቶ አደሩን ህይውት ለማሻሻልና ለመለወጥ የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተስፋፋ መሆናቸዉን ርእሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸዉ ላይ ገልጠዉ በዚህም ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደሩ ልማት መፋጠን የነበራቸዉ በጎ ራአይ ስኬት እየተረጋገጠ ነዉ ብለዋል በክልሉ ከ2003 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ያለው የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር በተፋስስ ልማት በእድገትና ትራንስፎርሚሽን እቅዱ መሠረት በጥናት ተደግፎ እየተከናወነ መሆኑም የወደፊቱን የእድገት ተስፋ አመለካች እንደሆነ ገልጠዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት ለአርብቶ አደሩ ልማትና እድገት መፋጠን እና ለምዕተ አመቱ የልማት ግብ መሳካት በሰጡት ልዩ ትኩረት ከ2 ቢልየን ብር በላይ በጀት በመመደብ የከርስ ምድር ውሃ ልማትየመብራትየስልክና የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች በክልሉ በተለያዩ ዞኖች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተዉ የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር 138ሺህ 781 እማወራና አባወራ አርብቶ አደሮች በመንደር በማሰባሰብ በጥምር ግብርና ስራ እንዲሳተፉ በማድረግ በተለይ በመጀመሪያው አመት የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮች የምግብ ዋስትናቸውን ማረጋገጥ እንደቻሉም ርእሰ መስተዳደሩ አመልክተዋል እንዲሁም በ39 ወረዳዎች የሚካሄደዉ የሴፍትኔት ፕሮግራም ከ900 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮችን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋራ ተያይዞ ሊከሰቱ ከሚችሉ የድርቅ አደጋዎችና ሌሎች ችግሮች ለመጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑበት መሆኑን ገልጸዋል በባዓሉ ላይ ተሸላሚ ከነበሩት መካከል አቶ ጣሂር ዩሱፍ 80 ግመሎችን ማርባት በመቻላቸዉ በክልል አቀፍ ደረጃ ለሽልማት መብቃታቸዉን በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል ወይዝሮ አሻ አህመድና አቶ ሲራጅ ሼህ መሀመድ በበኩላቸው በማህበር በመደራጀት የወተት ልማት በማካሄድ በአመት ከ6ሺህ ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ ማግኘት በመቻላቸው ተሸላሚ መሆናቸውን ተናግረዋል በበዓሉ ላይ የተገኘ የአርብቶ አደር ተወካዩች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የአርብቶ አደር በዓል መከበሩ በአርብቶ አደሩ አከባቢ መልካም እስተዳደር በማስፈን ልማትን ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስነ ስርዓቱ ላይ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዩች የተገኙ ሲሆን በአመቱ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡና ከ68 ወረዳዎች የተውጣጡ አርብቶ አደቶሮች ማህበራትና ቡድኖች የተዘጋጀላቸው ሜዳሊያና ምስክር ወርቀት ከክልሉ ርእሰ መስተዳደር ተወካይ ከርእሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች እጅ ተቀብለዋል ,
የአርብቶ አደሩን ህይወት ለማሻሻል መንግስት በቀጣይነት እንደሚሰራ ጠሚ ኃይለማርያም ገለፁ , አርብቶ አደሮች በልማትና በመልካም አስተዳዳር ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ 14ኛው የአርብቶ አደር በዓልታላቁ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደር ህዝባችን የነበራቸው ራኢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እንረባረባለን በሚል መሪ ቃል በኦሮምያ ክልል ያቤሎ ከተማ ተከብሯል በበዓሉ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አርብቶ አደሩ የጀመራቸው የልማትና የሰላም እንቅሰቃሴ እውን መሆን ያሰጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመካካላችን ባይኖሩም ያስጀመሩት ስራ ሁላችን በመረባረብ ዳር ለማድረስ ቃላችን የምናድስበት ነው ብለዋል ባለፉት ዓመታት ያከበርናቸው በዓላት በአገራችን በተለያዩ አከባቢዎቸ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች መካከል ቅርብ ግኑኙነት በመፍጠር የጋራ ችግሮቻቸው በመመካር እንዲፈቱና ከመንግስትም ጋር በቀጣይነት በመወያየት አቅጣጫዎች ለማሳየት አግዘዋል ብለዋል አርብቶ አደሩ ህዝባችን ዘለቄታዊ ህይወቱን ለመቀየር በሰላምና በመልካም አስተዳደር የተሻለ እንዲሆን መንግሰት ይሰራል ብለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በበኩላቸው ከሀገሪቱ የህዝብ ብዛት 12 ከመቶ የሚሆነውና በተፈጥሮ ሀብት በእንስሳት በከርሰ ምድር ውሃ በታደለው አከባቢ የሚኖው አርብቶ አደር ያለፉት ስርአቶች ያራምዱት በነበረው ኢ-ፍትሃዊ አስተዳዳር ምክንያት በከፋ ድህነትና ኋላ ቀር አኗኗር ይኖር እነደነበር ጠቁመዋል - ; ይህን ሁኔታ ለመቀየርና አርብቶ አደሩ የተሻለ ህይወት እንዲኖረው መንግስት የጀመረውን ልዩ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል በተንቀሳቃሽ ኑሮ ሰላምና ልማት ማሟላት አይቻልም ያሉት ዶክተር ሽፈራው አርብቶ አደሩ በመንደር በማሰባሰብ ከእንስሳት እርባታ በተጨማሪ በጥምር የእርሻ ዘዴ በመጠቀም የተሻለ ውጤት እያገኘ እነደሆነ ገልፀዋል በማህበራዊና በመሰረተ ልማት ተቋሞችም ተጠቃሚ እየሆነ ነው ብለዋል - ; የኦሮምያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ አብዱልአዚዝ መሀመድም የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥና ከልማቱ ተጠቃሚ አንዲሆን መሰረተ ልማት በማስፋፋት ምቹ የገበያ ሁኔታ እንዲፈጠርለት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት - ; በበዓሉ ላይ ከተለያዩ የአርብቶ አደር አከባቢዎች በስራቸው ሞዴል የሆኑ 144 አርብቶ አደሮች ተሸልመዋል - ; በባዓሉ ላይ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት የክልል ርእሳነ መስተዳድሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ቀጣዩ 15ኛው የአርብቶ አደር በዓል በአፋር ክልል በ2007 ዓ.ም እንደሚከበርም ታውቋል;
762 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተሸለሙ, በ6ኛዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል ላይ 762 አርዓያ የሆኑ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ዛሬ የካቲት 242005 ተሸልመዋል የታላቁ መሪ የክቡር አቶ መለስ ዜናዊን የግብርና ራዕይ ለማሳካት በላቀ ፅናትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በሚል መሪ ቃል በተከበረዉ በዓል ላይ ከተሸለሙት ዉስጥ 30 በመቶ ያክሉ ሴቶች ሲሆኑ 20 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ወጣቶች ናቸዉ ዘንድሮ ከተሸለሙት ዉስጥ 70 ከመቶ ያክሉ አዲስ ተሸላሚዎች ናቸዉ አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ለሽልማት የበቁት የተሻሻሉ የግብርና ግብዓቶችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነታቸዉን በማሳደጋቸዉ ነዉ ተሸላሚዎቹ በተፋሰስ ስራና በመስኖ ልማት እንደዚሁም በሌሎች የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም የሆኑ ናቸዉ ተሞክሯቸዉን ለሌሎች በማካፈልና መሰሎችን በማፍራትም ዉጤታማ እንደሆኑ በስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል በበዓሉ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርናዉ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል በላቀ ፅናት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል በዓሉን ስናከብርም በግብርና ምርታማነታችን ላይ እመርታ ለማምጣት ቃል በመግባት ሊሆን ይገባል ብለዋል የግብርና ሚንስትሩ አቶ ተፈራ ደርበዉ ደግሞ በአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መካከል የተሻለ የዉድድር መንፈስ በመፍጠርና የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ማሳካት ቁልፍ ተግባራችን ነዉ ብለዋል የበዓሉ አዘጋጅ የሆነዉ የአማራ ብሄራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌዉ ጎበዜ በበኩላቸዉ በግብርናዉ ዘርፍ ዉጤት ያመጣንዉ አመራሮች ባለሙያዎች አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮችና ባለሃብቶች ባደረጉት የተቀናጀ ርብርብ ነዉ ብለዋል ስለሆነም ለእነዚህ አካላት እዉቅና መስጠት ለቀጣይ ስኬታችን መሰረት ይሆናል ነዉ ያሉት ኢዜአ እንደ ዘገበው አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ከሜዳሊያ ባሻገር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ቦንድም ተሸልመዋል ከ1999 ጀምሮ እየተካሄደ ባለዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል እስካሁን 3709 አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮች አጋር አካላትና ድርጅቶች ተሸልመዋል,
በአፋር የአርብቶ-አደሩን ኑሮ ለመለወጥ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል -ርእሰመስተዳድሩ, .._2012. 0 260 195 ; 5; - ; አዲስ አበባ ጥቅምት 302005 ዋኢማ - በአፋር ብሄራዊ ክልል የሚገኘዉን የአርብቶ-አደር ኑሮ ለማሻሻል በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ የአመራር አካላት በቁርጠኝነት እንዲንቀሳቀሱ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አስገነዘቡ በክልሉ በየደረጃዉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሳተፉበትና በ2005 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ የሚወያይ ሰብሰባ በሰመራ ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እስማኤል ዓሊሴሮ ስብሰባዉን ሲከፍቱ እንደተናገሩት ታላቁ መሪያችን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻልና ህይወቱን ለመቀየር ያስቀመጡትን ራእይ ከዳር በማድረስ ረገድ ሁሉም በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀስ ይገባል ለዘመናት የከብትን ጭራ ተከትሎ ውሃና ሳር ፍለጋ ከቦታ ቦታ ሲንከራተት የኖረዉ አርብቶ-አደር ህብረተሰብ በመንደር ተሰባስቦ የተረጋጋ ህይወት እንዲመራ ታላቁ መሪያችን የነበራቸዉን ጽኑ ፍላጎትና እምነት ለማሳካት የእያንዳንዱ የክልሉ ህብረተሰብ ሃላፊነትና ግዴታ መሆኑን አስገንዝበዋል የአርብቶ-አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመቀየር ብሎም ወደ ዘመናዊ አርብቶ-አደርነትና ግብርና እንዲሸጋገር በአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የተያዘዉ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አስገንዝበዋል በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ በትምህርት በግብርናና ገጠር ልማት በጤናና ውሃ ሃብት ልማት በመንገድና በሌሎች የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ የተቀመጠዉን አቅጣጫ በመፈጸም የአርብቶ አደሩን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሌት ተቀን ተግቶ መስራት እንደሚገባም አቶ እስማኤል ተናግረዋል ከአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎሜሸን እቅድ አንፃር በያዝነው የመጀመሪያ ሩብ በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት የተመለከተ ሪፖርት በክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ቀርቦ ዉይይት ተካሄዶበታል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስብሰባው ላይ የ32ቱም የወረዳ መስተዳድር አመራሮች የአምስቱም የዞን መስተዳድር አመራሮችና በክልሉ የሁሉም የሴክተር እና ቢሮ ሃላፊዎችና የስራ ሂደት ባለቤቶች ተሳታፊ ሆነዋል ,
በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው, - ; .._2012. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ ህዳር 42005 ዋኢማ - በአገሪቱ አርብቶ አደር አካባቢዎች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የልማት ፕሮጀክቶች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትሩ አስታወቁ - ; ሚኒስትሩ ዶክተር ሺፈራው ተክለማርያም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአርብቶ አደሮች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የ2005 በጀት ዓመትን ዕቅድ በገመገመበት ወቅት እንዳስረዱት ፕሮጀክቶቹ የአርብቶ አደር ማህበረሰብ በሚኖርባቸው አራት ክልሎች እየተከናወኑ ነው በዚህም በክልሎቹ ተመጣጣኝ ልማት ለማምጣት በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራም በማካሄድየተፋሰስ ልማት በማከናወንየወረዳዎችን አቅም በመገንባትና በሌሎችም መስኮች ላይ ያተኮሩ ፕሮጀክቶች በመተግበር ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል በያዝነው ዓመት 98ሺህ አርብቶ አደሮችን በመንደሮች ለማሰባሰብ መታቀዱን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ200ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች በመንደር መሰባሰባቸውንም አስታውሰዋል እንደ ዶክተር ሺፈራው ገለጻ በበጀት ዓመቱ በሶማሌበአፋርበኦሮሚያና በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚከናወኑት ፕሮጀክቶች የአርብቶ አደሮችን ኑሮ በማሻሻልና ለአደጋ ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው የማህበረሰብ ልማትየለውጥ ሠራዊት ግንባታ የግጭት መከላከልና አፈታት ሥራዎች በበጀት ዓመቱ የሚከናወኑ ሌሎች ተግባራት መሆናቸውን አስረድተዋል የምክር ቤቱ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ልጅዓለም ወልዴ በበኩላቸው ሚኒስቴሩ በሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነትበአካባቢ ጥበቃበኤች አይ ቪኤድስ መከላከል ረገድ ተጨማሪ ሥራዎችን ለማከናወን ዕቅድ ማውጣት እንዳለበት አሳስበዋል በተለይም በግጭት መከላከልና አፈታት ረገድ የሚታየውን የአመለካከት ክፍተት ለመሙላት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጭ ተግባራት መከናወን እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የምክር ቤቱን የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬትን ጠቅሶ የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው ,
በይልማና ዴንሳ ወረዳ በእንስሳት ማድለብ ስራ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች ቁጥር እያደገ ነው, - ; .._2012. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ታሀሳስ 152005 ዋኢማ - በምዕራብ ጎጃም ዞን በይልማና ዴንሳ ወረዳ በእንስሳት ማድለብ ስራ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች ቁጥር በየአመቱ እያደገ መምጣቱን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ በያዝነው ዓመት አርሶ አደሮቹ 63 ሺህ እንስሳት አድልበው ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየሰሩ ነው የጽህፈት ቤቱ የእንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ቢያዝን አየለ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በወረዳው አርሶ አደሩ ከሚያደልባቸው እንስሳት በሚያገኘው ገቢ ኑሮውን እያሻሻለ ነው በያዝነው ዓመት ከ37ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮች 63 ሺህ እንስሳት አድልበው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ጽህፈት ቤቱ አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል ባለፉት አምስት ወራት ከ19 ሺህ የሚበልጡ እንስሳት ደልበው ለገበያ ሲቀርቡ በቀሪው በጀት ዓመት በዕቅድ የተያዙ እንስሳትን አርሶ አደሩ አድልቦ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆን ባለሙያውና አመራሩ ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙ ተናግረዋል በዓመቱ ይደልባል ተብሎ የሚጠበቀው እንስሳት ከቀዳሚው ዓመት ከአራት ሺህ በላይ ብልጫ እንዳለው አመልክተው በዓመቱ ከሚደልቡት እንስሳት መካከል ከ26ሺህ የሚበልጡ የዳልጋ ከብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል በወረዳው እንስሳት ማድለብ ስራ እየተሳተፉ የሚገኙ አርሶ አደሮች በበኩላቸው እንስሳት ማድለብ ከጀመሩ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ እስከ 10ሺህ ብር የተጣራ ትርፍ በማግኘት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ የማድለብ ስራውን ይበልጥ አስፋፍተው በመቀጠል በሚያገኙት ተጨማሪ ገቢ ተጠቃሚ መሆን የሚያስችላቸውን ስራ ከወዲሁ እየሰሩ እንደሚገኙ አርሶ አደሮቹ አስረድተዋል ባለፈው ዓመት በወረዳው በእንስሳት ማድለብ ስራ የተሳተፉ ከ35ሺህ 600 የሚበልጡ አርሶ አደሮች አድልበው ለገበያ ካቀረቧቸው እንስሳት ከ71 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውንም ገልጿል,
በፕሮጀክቱ አካባቢ ለሚኖሩ አርብቶ አደሮች አገልግሎት መስጫና የመስኖ ልማት ተቋማት እየተገነቡላቸው ነው , - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አባባ ጥር 62005 ዋኢማ - በደቡብ ኦሞ ዞን በሚገነባው የኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት አካባቢ የሚኖሩ አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አገልግሎት መስጫና የመስኖ ልማት ተቋማት እየተገነቡ መሆኑን የስኳር ኮርፖሬሽን አስታወቀ በፕሮጀክቱ አካባቢ ከሚኖሩ አርብቶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በልማቱ ጥቅሞች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተካሄደው የምክክር መድረክ የማጠቃለያ ውይይት ዛሬ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል የኮርፖሬሽኑ የሕዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳመነ ዳሮታ በዚሁ ውቅት እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በአብዛኛው በሚካሄድበት በሳላማጎ ወረዳ በመንደሮች ለተሰባሰቡ 1ሺህ 430 የቦዲ ብሄረሰብ አባወራ አርብቶ አደሮች አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ግንባታ እየተካሄደ ነው እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ በሦስት መንደሮች ለተሰባሰቡት ለነዚሁ አርብቶ አደሮች ሦስት በየደረጃው የሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ሁለት ጤና ኬላዎች ተገንብተዋል በተጨማሪም ሁለት የእህል ወፍጮዎችሦስት መጋዘኖችና አንድ የእንስሳት ጤና ኬላ ተሰርተዋል እንዲሁም የቀበሌ ጽህፈት ቤትና የፖሊስ ጣቢያ ግንባታም መካሄዱን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል በፕሮጀክቱ ድጋፍ እየተካሄዱ ከሚገኙት ሥራዎች መካከል በኦሞ ወንዝ ላይ የሚገነባው ጊዜያዊ የውሃ መቀልበሻ ኮፈር ዳም ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም አስታውቀዋል ለመንደር አንድ አንድ መለስተኛ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩንና ለሌሎቹ ሁለት መንደሮች ደግሞ አንድ መለስተኛ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ መጀመሩን አቶ ዳመነ አመልክተዋል ለእርሻ ሥራ የሚሆን ከ4ሺህ500 ሄክታር በላይ መሬት ምንጣሮና ድልዳሎ ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑን ገልጸውበመስኖ የሚለማ ሁለት ሺህ ሄክታር መሬት ለአርብቶ አደሮቹ በመከፋፈል ላይ እንደሚገኝም አቶ ዳመነ ተናግረዋል ስድስት ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬት የሚያለማው የ24 ኪሎ ሜትር ዋና የመስኖ ቦይ ግንባታም በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል በመንገድ ዘርፍ የ42 ኪሎ ሜትር መንገድ ከፈታና የ17ነጥብ3 ኪሎ ሜትር መንገድ ጠጠር ማልበስ ተግባራት መከናወናቸውንና ልማቱ በሚደርስባቸው የሙርሲ ጉራ መንደሮች በዚህ ዓመት ከሚሰራው መንገድ 12ነጥብ6 ኪሎ ሜትር ያህሉ መጠናቀቁን አብራርተዋል ፕሮጀክቱ ለችግርና ለረሃብ በሚያጋልጥ ሁኔታ ተበታትኖ የሚኖረውን አርብቶ አደር የመስኖ ልማትን በሚካሄድበት አካባቢ በማስፈር ቋሚና የተረጋጋ ሕይወት ለመምራት እንደሚያስችለውም አስረድተዋል የምክክር መድረኩ ዓላማም የአካባቢው አርብቶ አደሮችና ባለድርሻ አካላት በፕሮጀክቱ ላይ በቂ ግንዛቤ አግኝተው በባለቤትነትና በተጠቃሚነት ስሜት እንዲሳተፉ ለማድረግ መዘጋጀቱን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል ከታኅሣሥ 22 ቀን 2005 ጀምሮ የተካሄደው መድረክ ማጠቃለያ በሆነው ውይይት ላይ በልማቱ አካባቢ የሚገኙ አርብቶ አደሮችየብሄረሰቦች ተወካዮችየጎሣ መሪዎችየከተማ ነዋሪዎችበየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደር አካላት ተሳትፈዋል እንዲሁም የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተካፍለዋል ፕሮጀክቱ በ175ሺህ ሄክታር የሸንኮራ አገዳ በማልማት እያንዳንዳቸው በቀን 12ሺህ ቶን አገዳ የሚፈጩ ሦስት ፋብሪካዎችና እያንዳንዳቸው በቀን 24ሺህ ቶን አገዳ የሚፈጩ ሁለት ፋብሪካዎች እንደሚኖሩት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል እንደ ኢዜአ ዘገባ የኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት እየተገነባ ያለው በደቡብ ብሄሮችብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ውስጥ ነው ,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
በክልሉ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በተጀመረው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ተገኘ , .._2013. 0 260 196 ; 5; ጅጅጋ የካቲት 282005ዋኢማ - በሶማሌ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ በተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ የክልሉ ምክር ቤት ከትላንት በስቲያ ጀምሮ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችንም አጽድቋል የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር ለክልሉ ምክር ቤት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ባቀረቡት ወቅት እንደተናገሩት በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማሕበረሰብ የሰላም የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ባለፉት ስድስት ወራት አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት በተለይም በትምህርት ጤና እንስሳት ሃብት ልማትና በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ረገድ ከዚህ ቀደም ከነበረው አፈጻጸም የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ገልጸው በክልሉ በያዝነው ዓመት የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ከ85 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የጤና አገልግሎት ሽፋን 83 በመቶ የገጠር የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ደግሞ 57 በመቶ እንዲሁም የእንስሳት ህክምና አገልግሎት ሽፋን 71 በመቶ መድረሱን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል መንግስት የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በእንስሳት ሃብት ጤና አጠባበቅና በእንስሳት ግብይት ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ በግማሽ የበጀት ዓመቱ ከ5 ሚሊየን 700ሺ በላይ ለሚሆኑ እንስሳት ክትባት የተሰጠ ሲሆን ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ዘመናዊ የእንስሳት ገበያ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል እንዲሁም በያዝነው ዓመት በክልሉ 43ሺ አባወራዎችን በመንደር ለማሰባሰብ የተያዘው እቅድ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በመንደር ማሰባሰብ የአርብቶ አደሩን ህይወት በዘላቂነት ለመፍታት እየተካሄደ ባለው ፕሮግራም ባለፉት አራት ዓመታት በአጠቃላይ በ21 ወረዳዎች 150ሺ አባወራዎች መሰባሰባቸውን አስረድተዋል ምክር ቤቱ ባካሄደው 6ኛ መደበኛ ጉባኤ አምስት የተለያዩ አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን በሙስናና በስራ አፈጻጸማቸው ችግር አለባቸው ያላቸውን የክልሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት ከስልጣናቸው በማንሳት በምትካቸው መሾሙን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል,
ክልሉ 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን አስታወቀ, .._2013_. 0 262 192 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 212005 ዋኢማ - የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት 4 ሺሕ 90 አርብቶ አደሮችን በመንደር ማሰባሰቡን የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አስታወቀ በክልሉ የአርብቶ አደር ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት ኩይሳ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንደር ለተሰባሰቡት አርብቶ አደሮች አስፈላጊውን የማህበራዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ 83 ተቋማት በግንባታ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል የአገልግሎት መስጫ ተቋማቱ ትምህርት ቤቶች ጤና ኬላዎች የባለሙያ መኖሪያ ቤቶች የእህል ወፍጮዎች መጋዘኖች የቀበሌ ጽህፈት ቤቶችና የአርብቶ አደር ማሰልጠኛዎችን እንደሚያካትቱ ሃላፊው ተናግረዋል በክልሉ በሶስት ዞኖች በሚገኙ 12 ወረዳዎች የሚኖረው ግማሽ ሚሊየን አርብቶና ከፊል አርብቶ አደርን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የክልሉ መንግስት እየሰራ መሆኑንም ሃላፊው ተናግረዋል ያለፉት ስርዓታት ለአርብቶ አደሮቹ ምንም ዓይነት ትኩረት እንዳልሰጡ የጠቆሙት አቶ ዳዊት መንግስት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ የአርብቶ አደሮች የልማት ፓኬጅ ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመቀየር ከተወሰዱ እርምጃዎች አንዱ በሰፈር ማሰባሰብ መሆኑን የገለጹት አቶ ዳዊት በቀጣይ ዓመታትም በመንደር የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል አርብቶ አደሩ በመንደር ማስፈር ጋር ተያይዞ እየተነሳ ያለው አሉባልታ የአርብቶ አደሩ ህይወት እንዲቀየር በማይፈልጉ ግለሰቦች የመሚነዛ መሆኑን ሃላፊው ጠቁመው ፕሮግራመሙ እየተፈጸመ ያለው ፈቃደኝነትን መሰረት አድርጎ መሆኑን አስረድተዋል ,
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘው ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው, - ; .._2013. 0 260 197 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 122005 ዋኢማ - ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአርብቶ አደሩ ልማት እንዲፋጠን የነበራቸውን ራዕይ ለማሳካት የተያዘዉ ጥረት በክልሉ ተስፋ ሰጪ ዉጤት እያስገኘ መሆኑን የሱማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አስታወቁ አስራ አራተኛዉ የአርብቶ አደር ቀን በክልል ደረጃ በጅጅጋ ከተማ ትላንት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ በበዓሉ ላይ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ዘጠና አንድ አርብቶ አደሮች ተሸላሚ ሆነዋል የክልሉ ርእሰ መስተዳደር አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በተወካያቸው አማካኝነት ለበአሉ ታዳሚዎች ባስተላላፉት መልዕክት የክልሉን አርብቶ አደር ህይውት ለመለወጥ የተጀመሩ ጥረቶች አበረታች ውጤት እያሳዩ ነው በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አርብቶ አደሩ በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት እየጎለበተና እየዳበረ ለመምጣቱ አይነተኛ ማረጋገጫ መሆኑን አስታዉቀዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት በጋራ የአርብቶ አደሩን ህይውት ለማሻሻልና ለመለወጥ የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተስፋፋ መሆናቸዉን ርእሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸዉ ላይ ገልጠዉ በዚህም ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደሩ ልማት መፋጠን የነበራቸዉ በጎ ራአይ ስኬት እየተረጋገጠ ነዉ ብለዋል በክልሉ ከ2003 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ያለው የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር በተፋስስ ልማት በእድገትና ትራንስፎርሚሽን እቅዱ መሠረት በጥናት ተደግፎ እየተከናወነ መሆኑም የወደፊቱን የእድገት ተስፋ አመለካች እንደሆነ ገልጠዋል የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት ለአርብቶ አደሩ ልማትና እድገት መፋጠን እና ለምዕተ አመቱ የልማት ግብ መሳካት በሰጡት ልዩ ትኩረት ከ2 ቢልየን ብር በላይ በጀት በመመደብ የከርስ ምድር ውሃ ልማትየመብራትየስልክና የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች በክልሉ በተለያዩ ዞኖች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ ብለዋል በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተዉ የመንደር ማሰባሰብ መርሐ ግብር 138ሺህ 781 እማወራና አባወራ አርብቶ አደሮች በመንደር በማሰባሰብ በጥምር ግብርና ስራ እንዲሳተፉ በማድረግ በተለይ በመጀመሪያው አመት የተሰባሰቡ አርብቶ አደሮች የምግብ ዋስትናቸውን ማረጋገጥ እንደቻሉም ርእሰ መስተዳደሩ አመልክተዋል እንዲሁም በ39 ወረዳዎች የሚካሄደዉ የሴፍትኔት ፕሮግራም ከ900 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮችን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋራ ተያይዞ ሊከሰቱ ከሚችሉ የድርቅ አደጋዎችና ሌሎች ችግሮች ለመጠበቅ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑበት መሆኑን ገልጸዋል በባዓሉ ላይ ተሸላሚ ከነበሩት መካከል አቶ ጣሂር ዩሱፍ 80 ግመሎችን ማርባት በመቻላቸዉ በክልል አቀፍ ደረጃ ለሽልማት መብቃታቸዉን በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል ወይዝሮ አሻ አህመድና አቶ ሲራጅ ሼህ መሀመድ በበኩላቸው በማህበር በመደራጀት የወተት ልማት በማካሄድ በአመት ከ6ሺህ ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ የተሻለ ገቢ ማግኘት በመቻላቸው ተሸላሚ መሆናቸውን ተናግረዋል በበዓሉ ላይ የተገኘ የአርብቶ አደር ተወካዩች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የአርብቶ አደር በዓል መከበሩ በአርብቶ አደሩ አከባቢ መልካም እስተዳደር በማስፈን ልማትን ለማፋጠን አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል እንደ ኢዜአ ዘገባ በስነ ስርዓቱ ላይ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዩች የተገኙ ሲሆን በአመቱ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡና ከ68 ወረዳዎች የተውጣጡ አርብቶ አደቶሮች ማህበራትና ቡድኖች የተዘጋጀላቸው ሜዳሊያና ምስክር ወርቀት ከክልሉ ርእሰ መስተዳደር ተወካይ ከርእሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች እጅ ተቀብለዋል ,
የአርብቶ አደሩን ህይወት ለማሻሻል መንግስት በቀጣይነት እንደሚሰራ ጠሚ ኃይለማርያም ገለፁ , - ; .._2013. 0 260 195 ; 5; አዲስ አበባ ጥር 182005 ዋኢማ አርብቶ አደሮች በልማትና በመልካም አስተዳዳር ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ 14ኛው የአርብቶ አደር በዓልታላቁ መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ለአርብቶ አደር ህዝባችን የነበራቸው ራኢ ለማሳካት በቁርጠኝነት እንረባረባለን በሚል መሪ ቃል በኦሮምያ ክልል ያቤሎ ከተማ ተከብሯል በበዓሉ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አርብቶ አደሩ የጀመራቸው የልማትና የሰላም እንቅሰቃሴ እውን መሆን ያሰጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመካካላችን ባይኖሩም ያስጀመሩት ስራ ሁላችን በመረባረብ ዳር ለማድረስ ቃላችን የምናድስበት ነው ብለዋል ባለፉት ዓመታት ያከበርናቸው በዓላት በአገራችን በተለያዩ አከባቢዎቸ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች መካከል ቅርብ ግኑኙነት በመፍጠር የጋራ ችግሮቻቸው በመመካር እንዲፈቱና ከመንግስትም ጋር በቀጣይነት በመወያየት አቅጣጫዎች ለማሳየት አግዘዋል ብለዋል አርብቶ አደሩ ህዝባችን ዘለቄታዊ ህይወቱን ለመቀየር በሰላምና በመልካም አስተዳደር የተሻለ እንዲሆን መንግሰት ይሰራል ብለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በበኩላቸው ከሀገሪቱ የህዝብ ብዛት 12 ከመቶ የሚሆነውና በተፈጥሮ ሀብት በእንስሳት በከርሰ ምድር ውሃ በታደለው አከባቢ የሚኖው አርብቶ አደር ያለፉት ስርአቶች ያራምዱት በነበረው ኢ-ፍትሃዊ አስተዳዳር ምክንያት በከፋ ድህነትና ኋላ ቀር አኗኗር ይኖር እነደነበር ጠቁመዋል - ; ይህን ሁኔታ ለመቀየርና አርብቶ አደሩ የተሻለ ህይወት እንዲኖረው መንግስት የጀመረውን ልዩ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል በተንቀሳቃሽ ኑሮ ሰላምና ልማት ማሟላት አይቻልም ያሉት ዶክተር ሽፈራው አርብቶ አደሩ በመንደር በማሰባሰብ ከእንስሳት እርባታ በተጨማሪ በጥምር የእርሻ ዘዴ በመጠቀም የተሻለ ውጤት እያገኘ እነደሆነ ገልፀዋል በማህበራዊና በመሰረተ ልማት ተቋሞችም ተጠቃሚ እየሆነ ነው ብለዋል - ; የኦሮምያ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ አብዱልአዚዝ መሀመድም የአርብቶ አደሩን ህይወት ለመለወጥና ከልማቱ ተጠቃሚ አንዲሆን መሰረተ ልማት በማስፋፋት ምቹ የገበያ ሁኔታ እንዲፈጠርለት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናከረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት - ; በበዓሉ ላይ ከተለያዩ የአርብቶ አደር አከባቢዎች በስራቸው ሞዴል የሆኑ 144 አርብቶ አደሮች ተሸልመዋል - ; በባዓሉ ላይ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት የክልል ርእሳነ መስተዳድሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ቀጣዩ 15ኛው የአርብቶ አደር በዓል በአፋር ክልል በ2007 ዓ.ም እንደሚከበርም ታውቋል;
762 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተሸለሙ, - ; .._2013. 0 260 196 ; 5; አዲስ አበባ የካቲት 252005 ዋኢማ - በ6ኛዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል ላይ 762 አርዓያ የሆኑ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ዛሬ የካቲት 242005 ተሸልመዋል የታላቁ መሪ የክቡር አቶ መለስ ዜናዊን የግብርና ራዕይ ለማሳካት በላቀ ፅናትና ቁርጠኝነት እንሰራለን በሚል መሪ ቃል በተከበረዉ በዓል ላይ ከተሸለሙት ዉስጥ 30 በመቶ ያክሉ ሴቶች ሲሆኑ 20 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ወጣቶች ናቸዉ ዘንድሮ ከተሸለሙት ዉስጥ 70 ከመቶ ያክሉ አዲስ ተሸላሚዎች ናቸዉ አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ለሽልማት የበቁት የተሻሻሉ የግብርና ግብዓቶችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነታቸዉን በማሳደጋቸዉ ነዉ ተሸላሚዎቹ በተፋሰስ ስራና በመስኖ ልማት እንደዚሁም በሌሎች የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም የሆኑ ናቸዉ ተሞክሯቸዉን ለሌሎች በማካፈልና መሰሎችን በማፍራትም ዉጤታማ እንደሆኑ በስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል በበዓሉ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በግብርናዉ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠል በላቀ ፅናት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል በዓሉን ስናከብርም በግብርና ምርታማነታችን ላይ እመርታ ለማምጣት ቃል በመግባት ሊሆን ይገባል ብለዋል የግብርና ሚንስትሩ አቶ ተፈራ ደርበዉ ደግሞ በአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መካከል የተሻለ የዉድድር መንፈስ በመፍጠርና የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ማሳካት ቁልፍ ተግባራችን ነዉ ብለዋል የበዓሉ አዘጋጅ የሆነዉ የአማራ ብሄራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌዉ ጎበዜ በበኩላቸዉ በግብርናዉ ዘርፍ ዉጤት ያመጣንዉ አመራሮች ባለሙያዎች አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮችና ባለሃብቶች ባደረጉት የተቀናጀ ርብርብ ነዉ ብለዋል ስለሆነም ለእነዚህ አካላት እዉቅና መስጠት ለቀጣይ ስኬታችን መሰረት ይሆናል ነዉ ያሉት ኢዜአ እንደ ዘገበው አርሶ አደሮቹና ከፊል አርብቶ አደሮቹ ከሜዳሊያ ባሻገር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ቦንድም ተሸልመዋል ከ1999 ጀምሮ እየተካሄደ ባለዉ ሀገር አቀፍ የአርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በዓል እስካሁን 3709 አርሶ አደሮች ከፊል አርብቶ አደሮች አጋር አካላትና ድርጅቶች ተሸልመዋል,
የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር ውጤታማ እየሆነ ነው, - ; .._2014. 0 272 203 ; 5; አዲስ አበባ ሰኔ 12 2006 ዋኢማ - በአራት ክልሎች ተግባራዊ የተደረገው የአርብቶ አደር የልማት መርሐ ግብር እስከአሁን ያለው አፈጻጸም ስኬታማ እንደነበር የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ገለጸ - ; የመርሐ ግበሩ ሁለተኛ ምዕራፍ አጠቃላይ አፈጻጸም የሚገመግም ጉባኤ በአዳማ ሲካሄድ በመርሐ ግብሩ 2ኛ ምዕራፍ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል - ; የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው በጉባኤው ላይ በመርሐ ግብሩ ሁለተኛው ምዕራፍ የበርካታ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ሕይወት መቀየር መቻሉን ተናግረዋል - ; በጉባኤው ላይ የመርሐ ግብሩ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የመርሐ ግበሩ ተጠባባቂ አስተባባሪ አቶ ሰይድ ይመር በሁለተኛው ምዕራፍ የትግበራ ወቅት ለማከናወን ከታቀደው ውስጥ 99 በመቶውን መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል - ; የአርሶ አደሩን የኑሩ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የትምህርት የሰው እና የእንስሳት ጤና የመጠጥ ውሃ እና የአነስተኛ መስኖ ብሎም የማሕበረሰብ መንገድ ሥራዎች በመርሐ ግብሩ የተከናወኑ ናቸው - ; ይህም በሚሊየን ለሚቆጠሩ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደሮች የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ በጉባኤው ላይ ተነስቷል - ; በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ከክልሎች የመጡ የሥራ ኃላፊዎች ሁለተኛው ምዕራፍ መርሐ ግበሩ ሴቶችን ማሳተፉ ማህበራትን በማደራጀት የህብረተሰቡን ተሳትፎ ያማከለ መሆኑ ውጤታማ እንዳደረገው ተናግረዋል - ; መርሀ ግብሩ በአራቱ ክልሎች በሁለተኛው ምዕራፍ ከመንግስትና ከተለያዩ ለጋሽ አካለት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተሰራ ሲሆን ከ139 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጭ ተደርጓል - ; የአርብቶ አደር መርሀ ግብሩ በአፋር በኢትዮጵያ ሶማሌ በኦሮምያ እና በደቡብ ክልሎች የሚገኙ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮችን ኑሮ ማሻሻል የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን መሰረት አድርጎ የሚሰራው ነው - ; የ15 ዓመታት የቆይታ ጊዜ እንዲኖረው ተደርጎ የተቀረጸው መርሀ ግብሩ በየአምስት አመት ጊዜ ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን ሁለት ምዕራፎችን ተሻግሯል ,